ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Wednesday, December 30, 2020

እናት ፓርቲ የምርጫ ሰሌዳ አስመልክቶ የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተሞች ምርጫ ከሀገራዊ ምርጫው ጋር አብሮ እንዲደረግ የሚጠይቅ ደብዳቤ ለምርጫ ቦርድ መላኩን ጉዳያችን አውቃለች።

የተከበራችሁ የጉዳያችን ተከታታዮች፣ከእዚህ ደብዳቤ በተጨማሪ የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ምርጫ በተመለከተ ከሁለቱ ከተሞች ተፅዕኖ ፈጣሪነት አንፃር የተለያዩ ሃሳቦች ከተለያዩ ሰዎች እንደሚሰጡ ጉዳያችን ተገንዝባለች።ከእነኝህም ውስጥ የሚከተሉት ይገኙበታል።እነርሱም - 
1) የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተሞች ምርጫ ከሀገራዊ የተለየ ማድረጉ የሌሎቹ ውጤት ከታወቀ በኃላ የሁለቱን ከተሞች ብዙም አስፈላጊ እንዳይሆን ያደርገዋል፣
2) የለም፣የሁለቱ ከተሞች ምርጫ ውጤት የሌላውን ይወስናል፣
3) የሁለቱ ከተሞች ምርጫ ከሀገራዊው መለየቱ ሌላው ጋር የመረጡ መልሰው አዲስ አበባ እና ድረዳዋም መጥተው እንዲመርጡ ዕድል ይሰጣል።ይህም ለፅንፍ ኃይሎች የማጭበርበር በር ይከፍታል።
4) የሁለቱን ከተሞች ምርጫ መለየት ለፅንፍ ኃይሎች ዕድል ስለሚሰጥ ለሁከት በር ይከፍታል፣ወዘተ የሚሉ ሃሳቦች ይነሳሉ።
በመሆኑም የምርጫ ቦርድ ለእነኝህ ጉዳዮች በቂ ምላሽ ከወዲሁ በመስጠት ጉዳዩን ማጥራቱ ሃገራዊ ጥቅም አለውም።
ከእዚህ በላይ ያለው ጉዳያችን ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሰማችው ነጥቦች ናቸው እንጂ የእናት ፓርቲ ደብዳቤ ጋር ግንኙነት የለውም።
===========
ከእዚህ በታች የእናት ፓርቲ ለምርጫ ቦርድ የፃፈው ሙሉ ደብዳቤ ነው።



Friday, December 25, 2020

207 አስከሬን በግሬደር ጠርጎ በጅምላ መቅበር ፋሺሽታዊ ተግባር ብቻ ሳይሆን ድርጊቱ የስነልቦና ጦርነትም በህዝቡ ላይ ለመክፈት ያለመ ይመስላል።




  • ድርጊቱን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን፣የእስልምና እና ሌሎች ቤተ እምነቶች  አጥብቀው ማውገዝ አለባቸው።
  • የአስከሬን አቀባበር ስህተቱን  ለማረም አሁንም  መንግስት ሶስት የመፍትሄ አማራጮች አሉት።
በቤንሻንጉል፣መተከል  በቡለን ወረዳ በኩጅ ቀበሌ ከትናንት በስቲያ ማንነትን መሰረት ባደረገ በአራት አቅጣጫ በታጠቁ ኃይሎች በደረሰ ጥቃት እስከዛሬ ምሽት ድረስ ከቀይ መስቀል ምንጮች በተገኘው መረጃ  መሰረት 222 ኢትዮጵያውያን ከዓማራ፣ሽናሻ፣አገው እና ኦሮሞ ተወላጆች በአሰቃቂ ደረጃ ህይወታቸውን አጥተዋል።ግድያው በክልሉ ልዩ ኃይል ጭምር መከናወኑን የአይን ምስክሮች ገልጠዋል።በግድያው ላይ አንድ አባት ዘጠኝ ልጆቻቸውን ካጡት ጀምሮ በአንድ ቤተሰብ እስከ 12 የሚደርሱ የቤተሰብ አባላት ተገድለዋል።

ግድያው ከተፈፀመ በኃላም አሁን ውጥረቱ እንዳለ መሆኑ እየተነገረ ሲሆን በመንግስት በኩል ክልሉን ተከትሎ የተወሰደ እርምጃ ገና አልተሰማም። በዛሬው ዕለት በሌ/ጄኔራል አስራት ድኒሮ የሚመራ ከፍተኛ የመከላከያ ባለስልጣን የተመራ ልዑክ ወደ መተከል ተጉዞ በዝግ ስብሰባ የወንጀሉ ተባባሪ እንደሆኑ ከሚታሙት ከክልሉ ፕሬዝዳንት እና ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ስብሰባ ተቀምጠው እንደነበር  ተነግሯል።

ይህ በእንዲህ እያለ በግፍ የተገደሉት ኢትዮጵያውያንን አስከሬን ክልሉ ለጅምላ መቃብር በተቆፈረ መቃብር እና በግሬደር ከአፈር ጋር እየለወሰ እንዲቀበሩ ሲያደርግ የሚያሳዩ ፎቶዎች በማኅበራዊ ሚድያ ሲዘዋወር ታይቷል።ድርጊቱን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ከፍተኛ ባለሙያ በኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥን አዲስ አበባ ዜና እወጃ ላይ ቀርበው የተሰራው ከሰብዓዊ መብት ጥሰት በላይ መሆኑን ገልጠዋል።በእዚህ የጅምላ ቀብር 207 ኢትዮጵያን በአንድ ላይ በግሬደር እየተጠረጉ መቀበራቸውን በመቃብራቸው ላይ እንደዋዛ በብጣሽ ወረቀት የተፃፈው ፅሁፍ ያሳያል (ከላይ የምትመለከቱት ፎቶ በመቃብራቸው ላይ የተፃፈው ጽሁፍ ነው)።የጅምላ አቀባበሩ በራሱ ከኢትዮጵያዊነት ሃይማኖታዊ እና ባህላዊ ስርዓት የወጣ ከመሆኑም በላይ የቤተሰቦችን እርማቸውን አውጥተው የመቅበር  መብት የተጋፋ፣ጥላቻ እና ዘረኝነት የተንፀባረቀበት እና በፋሺዝም ዘመን የነበረውን ድርጊት የሚያስታውስ ነው።ይህንን የፈፀሙ የክልሉ ባለስልጣናት ላይም ሆነ አስፈፃሚዎቹ ሊመረመሩ ይገባል።

የጅምላ መቃብሩ ሌላው የሚያሳየው ጉዳይ ሆን ብሎ ከግድያው በተጨማሪ የስነ ልቦና ተፅኖ በሟች ቤተሰቦች እና ኢትዮጵያውያን ላይ ለመፍጠር የታሰበ ይመስላል።የግድያው ሃዘን በራሱ የሚፈጥረው የስነ ልቦና ተፅዕኖ እንዳለ ሆኖ፣በግሬደር አስከሬን እየገፉ በጅምላ መቅበር ይህንንም በፎቶ አንስቶ ማሰራጨት ሌላው የስነ ልቦና ጦርነት በሕዝቡ ላይ የመክፈት ዓላማ ያዘለ ይመስላል።ስለሆነም ከድርጊቱ ጀርባ ከክልሉ ባለስልጣናት ሌላ እነማን አሉ? ለምን ለቤተሰብ አስከሬን እንዲሰጥ አልተደርገም? በጅምላ ቢቀበሩስ ለምን ስርዓት በያዘ መልክ ቢያንስ የቤተሰብ ወኪል እንዲገኝ እና እንደ እየእምነታቸው እንዲቀበሩ ለምን አልተደረገም? ቀብር የኢትዮጵያውያን ማኅበራዊ ጉዳይ አንዱ እና ዋናው ክንውኖች ውስጥ ነው።ይህ ማለት ሁሉም የሚተባበርበት ጉዳይ ነው።ስለሆነም ለምን በተቻለ መጠን ህዝቡ ተረባርቦ እንዲቀብር አልተደረገም?

በመጨረሻም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን፣የእስልምና እምነት እና ሌሎች የዕምነት አካላት ሁሉ ግድያውን ከማውገዝ በላይ የጅምላ አቀባበሩ ኢትዮጵያዊ ብቻ ሳይሆን ሰውኛ መልክ የሌለው በመሆኑ ድርጊቱን አውግዘው መግለጫ መስጠት እና ተመሳሳይ ድርጊት እንዳይፈፀም ማሳሰቢያ መስጠት አለባቸው።አሁንም የተፈፀመውን ስህተት ለማረም መንግስት  ሶስት አማራጭ መንገዶች ሊኖሩት ይችላሉ። እነርሱም -

1) ኬሚካል እረጭቶ እንደገያ የቀብር ስርዓቱን የሚያስተካክልበት መንገድ ካለ ማስተካከል እና በየቤተ ዕምነታቸው አስከሬናቸው ተልኮ ቤተሰብ እንዲቀብር ማድረግ፣

2) ይህ ካልተቻለ በተቀበሩበት ቦታ ላይ ቤተ ዕምነት መትከል እና ቦታውን አጥሮ ማክበር በቦታው ላይ ቤተሰብ እርም የሚያወጣበት የሃይማኖት አባቶች ተገኝተው በፀሎት የሚሳተፉበት መርሃግብር በቶሎ ማዘጋጀት ወይንም 

3) እነኝህ ሁሉ ካልሆኑ ግን የቀብር ቦታው አሁንም በሥርዓት ታጥሮ እና ልዩ የማስታወሻ የቀብር ምልክት ከተደረገ በኃላ የክልሉ መንግስት በቀጥታ ስርጭት ስለ ድርጊቱ ስህተቱን አምኖ ሕዝብን ይቅርታ እንዲጠይቅ ማድረግ ያስፈልጋል።
ይህንን ሁሉ የማድረግ ፍላጎት ከሌለ ግን በኢትዮጵያ ሕግ ለአስከሬን የሚሰጠው ክብር አንፃር አቃቢ ሕግ ከገዳዮቹ ጋር ከሚከፈተው የክስ ቻርጅ ጋር ክስ መመስረት አለበት።

==============================///============
ማስታወቂያ 
============
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ የሚችሉበት አዲስ ቴክኖሎጂ ጉዳያችን ማስተዋወቅ ጀምራለች።
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Thursday, December 24, 2020

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዓቢይ አህመድ የጎሳ ፖለቲካን ለማገድ ከሕገ መንግሥቱም አንፃር ያለውን ቀዳዳ በሙሉ ተጠቅመው በተግባር ላይ የሚያውሉበት ወርቃማ ጊዜ አሁን ነው።






ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዓቢይ አሕመድ 

  • ኢትዮጵያ ከእዚህ በላይ የጎሳ ፖለቲካ የመሸከም አቅም የላትም።በአሁኑ ሰዓት  የጎሳ ፌድራሊዝምን ለማገድ ሀገራዊም ሆነ ዓለም አቀፋዊ ሁኔታም ይፈቅድላታል።

ኢትዮጵያ የሕዝቧን ባሕል፣ታሪክ እና ማንነትን ያማከለ የመንግስት ስርዓት ከመመስረት ይልቅ ተለማምዳው የማታውቀው  የጎሳ ፖለቲካ ታውጆባት ወደ ጥፋት እንደሚወስዳት እያወቀች ዛሬ ላይ ደርሳለች።የጎሳ ፖለቲካውን በህወሓት ተፅዕኖ ስር በሚገኘው  በኢህአዴግ ስብስብ ላለፉት ሠላሳ ዓመታት ያህል ታውጆ ኢትዮጵያን ለመበጣጠስ የደረሰ ብዙ መከራ በሕዝቧ ላይ አስከትሎ ከዛሬ ደርሷል።

የጎሳ ፖለቲካው በዋናነት የኢትዮጵያን ሕዝብ እንደ ሕዝብ፣አንድ ዜጋን እንደዜጋ የማያውቀው ህገ መንግስት ዋና ማጠንጠኛው ነው።ህገ መንግስት መግቢያው ሲጀምር 
''  እኛ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች፣ ሕዝቦች፡በሀገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ ዘላቂ ሰላም፣ ዋስትና ያለው ዴሞክራሲ እንዲሰፍን፣ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ እድገታችን እንዲፋጠን፣ የራሳችንን ዕድል በራሳችን የመወሰን መብታችንን ተጠቅመን፣...''
በሚሉ ዓረፍተ ነገሮች ይጀምራል።ይህ ማለት ህገ መንግስቱ ከመነሻው ለኢትዮጵያዊነት በወልም ሆነ በግል እውቅና አይሰጥም።

የጎሳ ፌድራሊዝም ማለት በራሱ የፌድራል አስተዳደር ብቸኛ መንገድ ማለት አይደለም።ጎሳን መሰረት ያደረገ ፌድራሊዝም አንዱ መገለጫው ጎሳን መሰረት ያደረገ የክልሎች አከላለል አንዱ መነሻው ነው።የጎሳ ፖለቲካ እና የጎሳ ፌደራሊዝም በኢትዮጵያ ስላስከተለው ጥፋት የተለየ ጥናት ማድረግ የሚጠይቅ አይደለም።ከእዚህ ሳምንቱ የመተከል ጭፍጨፋ እስከ ሐረር እና አርሲ፣ከሻሸመኔ እስከ ማይካድራ የደረሱትን ጥፋቶች ብቻ መጥቀስ ይበቃል።አሁን ጥያቄው የጎሳ ፖለቲካንም ሆነ የጎሳ ፌዴራሊዝምን ኢትዮጵያ ከእዚህ በኃላ ልትሸከምበት የምትችለው ትከሻ አላት ወይ? የሚለው ነው።

በአሁኑ ጊዜ ለኢትዮጵያ ጎሳ ፖለቲካ እና ለጎሳ ፌድራሊዝም ጠበቃ የሚቆም የሀገር ውስጥ ወይንም የውጭ አካል አለ? 

በሀገር ውስጥ የጎሳ ፖለቲካ ዋና አቀንቃኝ የነበረው የቀድሞው የፅንፈኛው ህወሓት በዋና ሞተርነት ስያንቀሳቅሰው ሌሎች ላለፉት አርባ ዓመታት በላይ በየጎሳቸው ሲያቀነቅኑ የነበሩ በዋናነት ከኦሮሞ፣ኡጋዴን፣ሲዳማ እና በቅርብ ደግሞ ከዓማራ አጋዦች አላጣም።ሆኖም ግን በኢትዮጵያ ሕዝብ ማኅበራዊ፣ታሪካዊ እና ፖለቲካዊ ታሪክ አንፃር ያልተለመደ እና ወደ ህዝቡ ለመስረፅ ከሃያ አመታት በላይ ፈጅቶበታል። ይህም ሆኖ ግን አሁንም በሕዝብ ውስጥ ሰርፆአል ማለት የሚቻልበት ደረጃ አይደለም።ይልቁንም ዘመን በሄደ ቁጥር ከህዝብ እየተነጠለ የጥቂት ጥቅመኞች ስብስቦች ዙርያ እየቀረ የመጣ እና በተቀረው ሕዝብ ዘንድ ግን እጅግ የሚጠላ እና ለሞት እና ለግጭት የሚዳርገው ዋነኛ ጠላቱ ሆኗል።ስለሆነም በሀገር ውስጥ ለጎሳ ፖለቲካ እና ለጎሳ ፈድራሊዝም ዘብ የሚቆሙ አካላት ከሕወሓት መደምሰስ በኃላ የቀሩት አቀንቃኞቹ በክልል ደረጃ በኦሮምያ፣በዓማራ እና በቤንሻንጉል ፅንፍ በያዙ አካሎች ዙርያ ተኮልኩሎ እና ተነጥሎ ብቻውን መንምኖ ቆሟል።

የኢትዮጵያን የጎሳ ፖለቲካ እና ይህንኑ መሰረት አድርጎ የተመሰረተው የክልሎች አመሰረታተት በውጭ አካላትም ሆነ በዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ዘንድም አድናቆት አላገኘም።በእርግጥ በኢትዮጵያ ጠላቶች በኩል ኢትዮጵያን ይበትናል ከሚል ምኞት ህወሓትን ሲያደንቁ እና ሲያበረታቱ ታይተዋል።ከእዚህ በተለየ የአፍሪካ ሀገሮች የኢትዮጵያን አካሄድ በፍርሃት ሲመለከቱት ኖረዋል።ለእዚህም ምክንያቱ የኢትዮጵያ አካሄድ ወደ ሀገራቸው እንዳይመጣ ከመፍራት የመነጨ ነው።የቀረው ዓለም ግን ቢያንስ የጎሳ ፖለቲካን አላደነቀም።ይህ ማለት ኢትዮጵያ የጎሳ ፖለቲካዋን ሙሉ በሙሉ ብታግድ በተለይ በእዚህ ህወሓት በተወገደበት ጊዜ እና ሕዝቡም በጎጥ ልዩነት የሚነሱ ግድያዎች ባንገሸገሹት ጊዜ ከኢትዮጵያ መንግስት የጎሳ ፖለቲካን የሚያግድበትን አንዳች ዓይነት መንገድ መቀየስ እና ተግባራዊ ማድረግ አለበት።

የኢትዮጵያ ፌዴራሊዝም አከላለል አንዱ እና ዋናው ችግር ጎሳን መሰረት ማድረጉ ነው።ይህ ደግሞ ክልሎች የተካለሉበት መንገድ አስተዳደራዊ አመችነቱን ሳይሆን ጎሳን እና ቋንቋን መሰረት ያደረጉ ናቸው።በኢትዮጵያ ህገ መንግስት አንቀፅ 48 ቁጥር 1 ላይ ''ክልሎች በመካከላቸው የሚነሳ አለመግባባት በተመለከተ የፌድሬሽን ምክር ቤት የህዝብ አሰፋፈርና ፍላጎት መሰረት በማድረግ ይወስናል'' ይላል።ይህ ማለት ግጭት ሳይፈጠር የህዝብ አሰፋፈርና ፍላጎትን መሰረት የማያደርግ እና ጎሳን መሰረት የሚያደርግ።ክልሎቹ ሲጋጩ ግን ፈድሬሽን ምክር በት የህዝብ አሰፋፈርና ፍላጎት መሰረት ያደርጋል ማለቱ በራሱ ግራ የሚያጋባ ነው።ክልሎች በሕዝቡ ፍላጎት መሰረት ለመከለል መጋጨት ያለባቸው ይመስላል።

የጎሳ ፖለቲካ እና ጎሳን መሰረት ያደረገው ፖለቲካ ለማስተካከል አንዱ የሚነሳው ጉዳይ የሕገ መንግስቱ መሻሻል ነው።ሕገ መንግስቱ አንቀጽ 105 ሕገ መንግሥቱን ስለማሻሻል የሚከተሉትን ነጥቦች ያስቀምጣል።

1 በዚህ ሕገ መንግሥት ምዕራፍ ሦስት የተዘረዘሩት መብቶችና ነጻነቶች በሙሉ፣ይህ አንቀጽ፣ እንዲሁም አንቀጽ 104 ሊሻሻሉ የሚችሉት በሚከተለው አኳሁአን ብቻ ይሆናል፡፡ 

ሀ/ ሁሉም የክልል ምክር ቤቶች የቀረበውን ማሻሻያ በድምጽ ብልጫ ሲያጸድቁት፣ 
ለ/ የፌዴራሉ መንግሥት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሁለት ሦስተኛ ድምጽ የቀረበውን ማሻሻያ ሲያጸድቀው፣ እና 
ሐ/ የፌዴሬሽኑ ምክር ቤት በሁለት ሦስተኛ ድምጽ ማሻሻያውን ሲያጸድቀው ነው፡፡ 

2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 ከተዘረዘሩት ውጭ ያሉት የሕገ መንግሥቱ ድንጋጌዎች ሊሻሻሉ የሚችሉት በሚከተለው አኳኊን ብቻ ይሆናል፤ 
ሀ/ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽኑ ምክር ቤት በጋራ ስብሰባ በሁለት ሦስተኛ ድምጽ የቀረበውን ማሻሻያ ሲያጸድቁት፣ እና 
ለ/ ከፌዴሬሽኑ አባል ክልሎቸ ምክር ቤቶች ውስጥ የሁለት ሦስተኛ ክልሎች ምክር ቤቶች በድምጽ ብልጫ የቀረበውን ማሻሻያ ሲያጸድቁት ነው፡፡ ይላል።

ለማጠቃለል ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት  የጎሳ ፌድራሊዝምን ለማገድ ሀገራዊም ሆነ ዓለም አቀፋዊ ሁኔታም ይፈቅድላታል።በሀገር ውስጥ የጎሳ ጠበቃው እና ትርምስ ለመፍጠር በብዙ ወንጀሎች የጠነከረው የፅንፈኛው የህወሓት ቡድን በኢትዮጵያ ጦር ሰራዊት መደምሰሱ፣በኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ የጎሳ ፖለቲካ የመሰደዱ፣የመገደሉ፣የእርስ በርስ ግጭት እና አጠቃላይ መጪውን ጊዜ የሚያጨልም ብቻ ሳይሆን ወደ አደገኛ የጥፋት መንገድ የሚወስድ መሆኑን ከምንጊዜውም በላይ በተግባር ያረጋገጠበት መሆኑ፣የአፍሪካ ሀገሮች በተለይ ከሳሃራ በታች ያሉ ሀገሮች የኢትዮጵያ የጎሳ ፖለቲካ ወደ ሀገራቸው የውስጥ የጎሳ ቁርሾ ተምሳሌት እንዳይሆን ብቻ ሳይሆን አዳዲስ ጥያቄ ይዞ እንዳይመጣ በስጋት ሲያዩት የነበረ መሆኑ እና የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ በመተከል ሰሞኑን የተፈፀመው እልቂት ተከትሎ ኢትዮጵያ በጎሳ ፖለቲካ ላይ የምትወስደው እርምጃ ተደማጭ ነቱን ይጨምረዋል ብቻ ሳይሆን እርምጃውን ለመውቀስ ሊያነሱት የሚችሉት የሞራል ጥያቄ ሊኖር አይችልም።ስለሆነም የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ የጎሳ ፖለቲካን ለማገድ ከሕገ መንግሥቱም አንፃር ያለውን ቀዳዳ በሙሉ ተጠቅመው በተግባር ላይ የሚያውሉበት ወርቃማ ጊዜ አሁን ነው።
===========================
ማስታወቂያ 
============
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ የሚችሉበት አዲስ ቴክኖሎጂ ጉዳያችን ማስተዋወቅ ጀምራለች።
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 


የኢትዮጵያ ''የዱላ እና ካሮት'' ፖሊሲ ሱዳንን ከጎረቤት ጋር እንዴት እንደሚኖር ሳያስተምራት አይቀርም።ኢትዮጵያ ዛሬ ሱዳንን በሚገባት መንገድ አናግራታለች!



ጉዳያችን አጭር ልዩ ዘገባ /Gudayachn

ሱዳን እና ግብፅ  በህወሓት መደምሰስ የሆነ የተደበላለቀ እና የተደናበረ ስሜት ውስጥ ገብተዋል።ሱዳን እና ግብፅ ብቻ ሳይሆኑ በኢትዮጵያ ላይ የነበራቸውን እኩይ ዓላማ ለማስፈፀመ የሚያልሙ ኃይሎች ሁሉ አብረው ''እንባ እንባ ይለኛል'' ዓይነት ስሜት ውስጥ ገብተዋል።በመጀመርያ ኢትዮጵያ አበቃላት እያሉ ይናገሩ የነበሩ ሁሉ የሕግ ማስከበሩ ተግባር ከሰብዓዊ ከፍተኛ ጥፋት በራቀ መልኩ ሲጠናቀቅ እራሳቸው ገብተው ሊያቦኩ የሸሚዛቸው እጅጌ ሲሰበስቡ መመልከት አስገራሚ ሆኗል።

ይህ በእንዲህ እያለ ሱዳን ከግብፅ ጋር ወታደራዊ ልምምድ በሰሜናዊ ካርቱም ግዛት በህዳር ወር መጨረሻ ጀምሮ ሲያደርጉ ነበር።የወታደራዊ ልምምዱ ዓላማ ግልጥ ባይሆንም በዋናነት በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ላይ ያነጣጠረ ለመሆኑ ግን አያጠራጥርም።የሱዳን እና የግብፅ ፖለቲካም ሆነ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ሁሉ በራሱ በሁለት እግሩ ያልቆመ ነገር ግን ከመካከለኛው ምስራቅ የትርምስ የፖለቲካ ኮተቱን በአፍሪካ ላይ ለማራገፍ የሚጥር የተሳከረ የአጉል ጀብደኝነት ሁሉ ውጤት ነው።

ከሰሞኑ ሱዳን የኢትዮጵያን የድንበር ቦታዎች እየጣሰች ጥቃት ስትፈፅም የአካባቢው የሚልሻ እና የፋኖ ኃይል በከባድ የአፀፋ ምት መልሷት ነበር።በመቀጠል ግን የሱዳን ወታደራዊ ኃላፊዎች የተሰማቸውን እፍረት ለመመለስ ተጨማሪ ጦር ከተሽከርካሪዎች ጋር  ወደ ቦታው ላኩ።ከፍተኛ አመራሮችም ወደ ድንበሩ ወርደው እስከ ሶስት ቀኖች የሚቆይ ቆይታ እያደረጉ  ግፋ በለው ሲሉ ከረሙ።በሌላ በኩል የኢትዮጵያ መንግስት ጉዳዩን ለማብረድ በመጀመርያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ጉዳዩ የሁለቱን መንግሥታት እና ሕዝብ የማይወክል እና ሁለቱን ሀገሮች ወደ ግጭት የሚያመራ አይደለም የሚል ማብራርያ በማኅበራዊ ሚድያ ከመልቀቅ ጀምሮ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ  ደመቀ መኮንን የተመራ ከፍተኛ የመንግስት ልዑክ እስከ ትናንት ድረስ በካርቱም ከሱዳን ባለስልጣናት ጋር ውይይት ሲያደርግ ቆይቶ ካለአመርቂ ውጤት ተመልሷል።

እስከ ውይይቱ ድረስ ግን የሱዳን ወታደሮች እስከ 25 ኪሎ ሜትር ድረስ የኢትዮጵያን ድንበር አልፈው መግባታቸው እና የኢትዮጵያውያን ባለሀብቶችን ንብረት ማውደማቸው ተሰምቷል።ከሱዳን ጋር ትናንት በተደረገው ውይይት የውጭ ጉዳይ ምኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ የተደረገው ውይይት የመጀመርያ ደረጃ እና ዝርዝሩ በቀጣይ የሚደረግ ነው የሁለቱ ሀገሮችን ወደ ግጭት መግባት ላይ የሚሰሩ ሀገሮች አሉ በማለት የተናገሩ ሲሆን፣በሌላ በኩል ግን ሌሎች መገናኛ ብዙሃን ኢትዮጵያ ሱዳን ከአላስፈላጊ የግጭት ሂደቶች እንድትታቀብ አስጠንቅቃለች በማለት ዘግበዋል።

በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ ማስጠንቀቅያ ተራ ንግግር አለመሆኑን ሱዳኖች  የተረዱት ይመስላል።ካርቱምን ከማሳሰቢያ ጋር ለቆ የወጣው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን አዲስ አበባ እንደገባ ሱዳንን በሚገባት መንገድ እያናገራት ነው።ይህንን ደግሞ ራሷ ሱዳን አምናለች።ሱዳን ትሪቡን ስሜን አትጥቀሱ አለኝ በማለት የሱዳን ወታደራዊ ባለስልጣን ጠቅሶ ኢትዮጵያ ''ጃባል አቡ ታዩር'' የሚገኘው ጦሯ በኢትዮጵያ ጦር ኃይል በከባድ መሳርያ መደብደቡን አምናለች።ሱዳን ይህንን የምትለው ኢትዮጵያን የፀብጫሪ አድርጎ ለማቅረብ ሊሆን እንደሚችል ግምታቸውን የሚሰጡ አሉ።የዛሬው ዘገባ ግን ከእዚህም ያለፈ ነው።ሱዳን በዛሬው የኢትዮጵያን ክንድ የቀመሰችበት መንገድ በአንድ በኩል ብቻ አለመሆኑን ጨምራ ነው የገለጠችው ።ግንባሩ በሁለት በኩል እንደነበር ዜናው ያትታል።ሁለተኛው ግንባር በወዲቃሊ በኩል ያለው ግንባር እንደሆነ የሚያትተው ዜና በሁሉም ግንባሮች በኢትዮጵያ መደበኛ ሰራዊት ጋር ሃገሩን እየተከላከለ ያለው የአማራ ፋኖ እንደሆነ የሱዳኑ ጋዜጣ ሱዳን ትሪቡን ያትታል።

በመጨረሻም ሱዳን ትሪቡን በኢትዮጵያ እና በሱዳን በኩል ያለው ድርድር ዋና ነጥብ።በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ የተመራው የኢትዮጵያ ልዑክ ጥያቄ ሱዳን ወርራ ከያዘችው የኢትዮጵያውያን የእርሻ ቦታዎች ለቃ እንድትወጣ እና ወታደሮቿ ላደረሱት ጥፋት ካሳ እንድትከፍል ሲሆን፣ሱዳን ደግሞ የድንበር መካለሉ አሁኑኑ ይፈፀም ባይ ነች።የኢትዮጵያ እና የሱዳን ድንበር የማቃለል ሥራ ጥናት ከንጉሡ ጊዜ ጀምሮ የነበረ ሲሆን ስራው ረዘም ያለ ጊዜ የሚወስድ እና የምድር ላይ ምልክቶች ሙሉ  በሙሉ ለማድረግ  ጊዜ እንደሚጠይቅ እያወቀች ኢትዮጵያ በተወጠረችበት ሰዓት ዛሬውኑ ማለቷ በግርግር እና በችኮላ የማይገባትን መሬት ለመውሰድ እንደሆነ ማንም የሚረዳው ነው።ለማንኛውም የኢትዮጵያ ''የዱላ እና ካሮት'' ፖሊሲ ሱዳንን ከጎረቤት ጋር እንዴት እንደሚኖር ሳያስተምራት አይቀርም።

Monday, December 21, 2020

አማርኛ መናገር፣ጃኖ መልበስ የሚያስገድልበት ሀገር (ቪድዮ)

ኢትዮጵያ ትልቅ ዲፕሎማሲያዊ ድል አግኝታለች! በእዚህም የተሸረበባት ትልቅ ተንኮል ከሽፏል።ተንኮሉ ምን ነበር?



ጉዳያችን/Gudayachn

ኢትዮጵያ በህወሓት ፅንፈኛ ቡድን ላይ የወሰደችው የሕግ ማስከበር እርምጃ ተከትሎ በኢትዮጵያ ላይ የሐሰት ዜና ከማሰራጨት ጀምሮ እስከ የውጭ ባለስልጣናት ጉትጎታ ድረስ የፅንፍ ኃይሎች ከውጭ ሀገር ተወላጆች ጋር በመጣመር ዘመቻ ሲያደረጉ ሰንብተዋል።ዘመቻው ከትዊተር እስከ ፔቲሽን ማስፈረም ሲቀጥል ዋና ዓላማው የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ በተለይ የምዕራቡ ዓለም እና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች በዋናነት የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት በጉዳዩ እንዲገባ የተደረገ ቅስቀሳን ሁሉ ያካተተ ነበር።

የተባበሩት መንግሥታትም ሁለት ጊዜ ''መደበኛ ያልሆነ'' የተባለ ንግግር አደረገ የሚል ዜናም ተለቆ ነበር።በእነኝህ የተባበሩት መንግሥታት መደበኛ ያልሆኑ ስብሰባዎች በተመለከተ የአፍሪካ ዲፕሎማቶችም ሆኑ የራሱ የድርጅቱ የዓለም አቀፍ ሕግ ባለሙያዎች የተባበሩት መንግሥታት አካሄድ ትክክል አለመሆኑን ተናግረዋል።ይሄውም የአንድ ሀገር ጉዳይ ወደ ተባበሩት መንግሥታት አጀንዳነት ከመሄዱ በፊት በአህጉራዊ ድርጅት ችግሩ መፍትሄ ለማግኘት ጥረት ተደርጎ ካልተሳካ መሆን አለበት የሚለው ሃሳብ ነው።በእዚህ መሰረት የተባበሩት መንግስታትን መቆምያ እና መቀመጫ አሳጥተው የነበሩ መንግሥታት አይናቸውን ወደ አፍሪካ ሕብረት እና ኢጋድ ላይ ጥለው በተስፋ ሲጠብቁ ቆዩ።

ይህ በእንዲህ እያለ የኢትዮጵያ ጦር ኃይል የሰላም ማስከበር ስራውን አጠናቆ ቀንደኞቹን ማደን ላይ አተኮረ።ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ ደግሞ የአፍሪካ ሕብረት ''ኢትዮጵያ በትግራይ የወሰደችው የሕግ ማስከበር ተግባር ሕጋዊ ነው'' ማለቱ እና በሳምንቱ መጨረሻ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ በጅቡቲ የአፍሪካ ቀንድ በየነመንግሥታት ሀገሮች (ኢጋድ) ስብሰባ ላይ ከተገኙ በኃላ የኢጋድ ሀገሮች የኢትዮጵያን ሕግ ማስከበር ሂደት መረዳታቸው እና መደገፋቸውን ያመሰገኑበት መልዕክት እና ኢጋድም በራሱ የሕግ ማስከበር ሂደቱን መደገፉ የተባበሩት መንግስታትን ሲጎተጉቱ የነበሩትን ሁሉ ከመንገድ ያጨናገፈ ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያ ትልቅ ዲፕሎማሲያዊ ድል ያስመዘገበ ነው።
====================

ማስታወቂያ 

============

በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ የሚችሉበት አዲስ ቴክኖሎጂ ጉዳያችን ማስተዋወቅ ጀምራለች።

አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

https://www.fetantopup.com/#gudayachn 



Sunday, December 20, 2020

ወቅቱ ሁሉም ኢትዮጵያን ሊጠነቀቅላት እና ሊጠብቃት የሚገባበት ጊዜ ነው።


  • ኢትዮጵያ እና ሱዳን በድንበር ጉዳይ ላይ ለመወያየት ለመጪው ማክሰኞ መቀጣጠራቸው ተሰምቷል።

ወቅቱ 

በሀገር ውስጥ -

- መንግስት በትግራይ የሕግ ማስከበር ተግባሩን በማገባደድ ላይ ያለበት፣
- የህወሓት ፅንፍ አመራሮች ገና ያልተያዙበት እና እየታደኑ ያለበት፣
- በትግራይ አስፈላጊ ለሆኑ መሰረተ ልማት ወጪዎች የሚያስፈልጉበት፣
- ብልጥግና ፓርቲ በውስጡ ያሉትን የፅንፍ  የጎሳ ኃይሎች በተለይ በኦሮምያ እና ቤንሻንጉል አለመረጋጋት እንዲፈጠር የበለጠ የሚጥሩበት እና በተለይ በኦሮምያ  ያሉ የፅንፍ ኃይሎች የመንግስትን መወጠር እንደ መልካም አጋጣሚ በመቁጠር እንደ አሜባ ለመስፋፋት የሚጥሩበት፣
- በአንፃሩ በፅንፍ ኃይሎች ላይ ለመዝመት እና ሰላሙን ለማስከበር በኦሮምያ በተለይ በወለጋ ህዝቡ ከምንጊዜውም በላይ አምርሮ የተነሳበት፣
- ኢኮኖሚው አነሰም በዛ በአጭር ጊዜ ጦርነት ሳብያ እና በህወሓት እና በርሱ ዙርያ በነበረው መረብ የሚንቀሳቀሱ የንግድ ድርቶች ገንዘብ እንዳይንቀሳቀስ ከመደረጉ አንፃር ለጊዜውም ቢሆን የሚፈጥረው ተፅኖ በስራቸው በያዙት የሰው ኃይል ሳብያ ክፍተት የሚያሳይበት፣
- ኢትዮጵያ ምርጫ ለማድረግ የምትዘጋጅበት፣
- በኮቪድ ምክንያት የተቀዛቀዘው ምጣኔ ሀብት ድጋፍ የሚሻበት እና በቶሎ ለማገገም የቱሪዝሙን ዘርፍ ለማንቀሳቀስ በጉጉት የሚጠበቅበት፣
- የፀጥታ ችግር ለመፍጠር የሚፈልጉ ተረፈ-ጁንታ እና የስልጣን ጥመኞችን ለመጠበቅ መንግስት ለፀጥታው ዘርፍ ዳጎስ ያለ በጀት ለመመደብ የተገደደበት ጊዜ ነው።

ከውጭ 

- የአፍሪካ ቀንድ ጂኦ-ፖለቲካ ከምንጊዜውም በላይ የጦዘበት፣
- በአፍሪካ ቀንድ ሀገሮች መሃል ለምሳሌ በኬንያ እና ሱማሌ፣በኢትዮጵያ እና ሱዳን መካከል ውጥረቶች ከድንበር ጋር በተያያዘ ውጥረቶች የታየበት፣
- በጅቡቲ የውጭ ወታደራዊ ጦር ሰፈሮች  ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ የመጡበት፣
- ሩስያ በያዝነው ሳምንት በአፍሪካ የመጀመርያዋ የሆነው የባህር ኃይል ጦር ሰፈር በሱዳን የመሰረተችበት እና ሶስት መርከቦች ከ 300  ወታደሮች ጋር ያሰፈረችበት፣በእዚህም መሰረት ውሉ እስከ 25 ዓመታት እንደሚቆይ የተነገረበት፣
- ሱዳን የኢትዮጵያ ለም መሬቶችን ለመውረር እና እስካሁን ግቡ ያልታወቀ የጦር ኃይሏን ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ያስጠጋችበት፣ 
- ሱዳን የጦር ኃይሏ ሙሉ በሙሉ በአንድ ዕዝ ስር ነው ለማለት የሚያስቸግር  በመሆኑ የህወሓት ተረፈ-ጁንታም ሆነ የጠገበ ነጋዴ በገንዘብ እንደፈለገ የሚመራው ጦር መሆኑ እና የጦሩ ሂደት የሱዳን የውስጥ መከፋፈል ነፀብራቅ መሆኑ የታየበት፣
- የምዕራቡ የዜና ማሰራጫዎች ከምንጊዜውም በላይ የፀረ-ኢትዮጵያ ዜናዎችን በተጋነነ መልኩ እያቀረቡ ያለበት እና የኢትዮጵያን ገፅታ ለማጠልሸት እየጣሩ ያለበት እና 
- የተረፈ-ጁንታ ቡድኖች በውጭ ሀገር የኢትዮጵያን ገፅታ ለማጠልሸት እና የዲፕሎማሲ መስመሯን ለማበላሸት ከፔቲሽን እስከ ስም ማጥፋት  ዘመቻ የተሰማሩበት ጊዜ ነው።

ለኢትዮጵያ መጠንቀቅ እና መጠበቅ የሁሉም ግዴታ ነው

ኢትዮጵያ አሁን የምትገኝበት ወሳኝ ከሆኑ ታሪካዊ ወቅቶች ውስጥ በአንዱ ላይ ነች።በቅርብ ታሪካችን ውስጥ ኢትዮጵያ ሳትጠቀምባቸው ያለፉት ነገር ግን ወደፊት ሊያስፈነጥሯት የሚችሉ ዕድሎች ሲመክኑባት ኖረዋል።የ1967 ዓም  እና የ1983 ዓም ለውጦች መጠለፋቸው እና አስፈላጊውን ለውጥ ሳያመጡ መምለጣቸው እና የ1997 ዓም ምርጫ ውጤት በህወሓት/ኢህአዴግ መካዱ  ኢትዮጵያን ዋጋ አስቀፍሏታል።አሁን ያለውም የለውጥ ሂደት በውጭም ሆነ በውስጥ አደናቃፊ እንዳይሰናከል የሁሉም ትጋት እና ንቃት ያስፈልጋል።በተለይ የአሁኑ የለውጥ ሂደት ላይ የሚደርስ እንቅፋት በቀላሉ በእንቅፋትነት ብቻ ተወስቶ የሚያልፍ ሳይሆን ካልወጣንበት መርዛማ የጎሳ ፖለቲካ አንፃር ለውጭ ተጋላጭነት ስለሚያጋልጥ 
በመንግስት ላይ የሚደረጉ ጥቃቅን ጫናዎች ሀገርን የሚጎዳ መሆኑን በመረዳት መንግስትን ማገዝ ሀገርን ማገዝ መሆኑን መረዳት ያስፈልግል።
በመጨረሻም ይህ በእንዲህ እያለ አሁን ዘግይቶ ከጅቡቲ እንደተሰማው ኢትዮጵያ እና ሱዳን በድንበር ጉዳይ ላይ ለመወያየት ለመጪው ማክሰኞ መቀጣጠራቸው ተሰምቷል።

 =============================

ማስታወቂያ 

============

በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ የሚችሉበት አዲስ ቴክኖሎጂ ጉዳያችን ማስተዋወቅ ጀምራለች።

አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

https://www.fetantopup.com/#gudayachn 


Friday, December 18, 2020

በኢትዮጵያ የገንዘብ ተቋማት ላይ ዓመታዊ ግምገማ የአይ ኤም ኤፍ አዲስ ሪፖርት Latest IMF Report on Financial Soundness of Ethiopia



The Federal Democratic Republic of Ethiopia : Technical Assistance Report-Financial Soundness Indicators Mission  

Author/Editor:

International Monetary Fund. Statistics Dept.

Publication Date:

December 18, 2020

Electronic Access:

Free Download. Use the free Adobe Acrobat Reader to view this PDF file

Summary:

The International Monetary Fund’s (IMF’s) Statistics Department (STA) provided technical assistance (TA) on financial soundness indicators (FSI) to the National Bank of Ethiopia (NBE) during June 15-July 10, 2020. The TA mission took place in response to a request from the authorities, with the support of the IMF’s African Department (AFR). Due to the COVID-19 pandemic and travel restrictions, the mission was conducted remotely via video conferences. The mission worked with the staff of the NBE on the development of FSIs that are in line with the IMF’s 2019 FSI Guide.1 The main objectives of the mission were to: (i) review the source data, institutional coverage, and accounting and regulatory frameworks supporting the compilation of FSIs; (ii) provide guidance for mapping source data for the banking sector to the FSI reporting templates FS2 and FSD as well as preparing the metadata; and (iii) agree with the authorities on the timeline to begin regular reporting of the FSIs for deposit-takers to STA. The mission also provided technical assistance to the NBE on the compilation of net open positions in foreign currencies.

Series:

Country Report No. 2020/323

Frequency:

regular

Publication Date:

December 18, 2020

ISBN/ISSN:

9781513564876/1934-7685

Stock No:

1ETHEA2020003

Format:

Paper

Pages:

38

To read the whole Report  click the link and then click at Free download.

===================

ማስታወቂያ 

============

በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ የሚችሉበት አዲስ ቴክኖሎጂ ጉዳያችን ማስተዋወቅ ጀምራለች።

አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

https://www.fetantopup.com/#gudayachn 




የሆለታ ገነት የጦር አካዳሚን ስም ማን ሰወረው?


ማስታወቂያ 
============
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ የሚችሉበት አዲስ ቴክኖሎጂ ጉዳያችን ማስተዋወቅ ጀምራለች።
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 


Wednesday, December 16, 2020

የእጅ አዙር ቅኝ አገዛዝ አጥብቀው የሚቃወሙት እና ሀገር ወዳዱ ሻምበል ፍቅረስላሴ ወግደረስ ሲታወሱ - ልዩ ጥንቅር...


ማስታወቂያ 
============
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ የሚችሉበት አዲስ ቴክኖሎጂ ጉዳያችን ማስተዋወቅ ጀምራለች።
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Tuesday, December 15, 2020

ኢትዮጵያ በያዝነው ዓመት የምታደርገው የምርጫ ቀን መቼ መሆን አለበት? ለቀኑ መመረጥ 3ቱ ምክንያቶች ታሳቢ ቢሆኑ


ምርጫ በኢትዮጵያ (ፎቶ ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ድረ ገፅ የተወሰደ)
  
ጉዳያችን/Gudayachn

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ክልሎችን እና የምርጫ ጣቢያዎችን በመላው  ሀገሪቱ እንዲያቋቁም በአዋጅ ቁጥር 1133/2011 አንቀፅ 7 ሥልጣን ተሰጥቶታል፡፡ በዚህ መሠረት የተቋቋሙ የምርጫ ክልሎች በአዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 14 መሠረት  አንድ የምርጫ ክልል ቦርዱ በሚያወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት፦የምርጫ ቁሳቁሶችን ለምርጫ ጣቢያዎች ያሰራጫል፣ ዕጩዎችን ይመዘግባል፣ መስፈርቱን ለሚያሟሉ ዕጩዎች የመታወቂያ ካርድ ይሰጣል። 

በያዝነው ዓመት እንደሚደረግ የሚጠበቀው የኢትዮጵያ ምርጫ አሁን እየተጠበቀ  ያለው የጊዜ ሰሌዳው ነው።ምናልባት ከምርጫው በፊት መንግስት የህዝብ ቆጠራ ማድረግ ይችላል ወይ? የሚሉ ጥያቄዎች እዚህም እዚያም ይነሳሉ።በተለይ የህዝብ ቆጠራ ለማድረግም ሆነ ምርጫውን ለማድረግ አብዛኛው ዝግጅቶች በመጠናቀቃቸው ሁለቱንም በአንድ ዓመት ሊያከናውን ቢያስብ ይችላል።የሚሉ የመኖራቸውን ያህል አሁን ምርጫው ላይ ነው በቀዳሚነት ማተኮር ያለበት የሚሉ ሃሳቦች የሚሰጡም አሉ። 

ምርጫው በእዚህ ዓመት መደረግ እንዳለበት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይም ምርጫውን ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ላይ በቅርቡም ደግመው ተናግረዋል።አሁን ጥያቄው አዲሱ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ እና ዋናው የምርጫ ጊዜ መቼ ቢሆን ይሻላል? የሚለው ጥያቄ ነው። አንዳንድ ጊዜ የሚወሰኑት የጊዜ ሰሌዳዎች የህዝቡን ማኅበራዊ ጉዳዮች ያላገናዘቡ መሆናቸው በራሱ ችግር ስለሚፈጥር ከአሁኑ ጥንቃቄ የሚፈልግ መሆኑን ካለፈው ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ መቀየር መረዳት ይገባል።ለምሳሌ ባለፈው የጊዜ ሰሌዳ በኮቪድ ምክንያት ከመቀየሩ በፊት መጀመርያ ነሐሴ የመጀመርያ ሳምንት ውስጥ ሆኖ በኃላ ወቅቱ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተከታዮች የፆም እና ሱባኤ ወቅት መሆኑ ተገልጦ በማኅበራዊ ሚድያ ተቃውሞ ከተሰማ በኃላ ወደ ነሐሴ ሶስተኛ ሳምንት መዞሩ ይታወሳል።በመጪው ምርጫ ላይም ታሳቢ የሚሆኑ ጉዳዮች ከአሁኑ ቀድሞ መጠቆሙ አስፈላጊ ያደርገዋል።

የዘንድሮው ምርጫ መቼ ይሁን? ለቀኑ መመረጥ ሶስቱ ምክንያቶች

የዘንድሮው ምርጫ ወደ ክረምቱ ባይገባ፣ከግንቦት የመጀመርያ ሳምንት ባይቀድም ነገር ግን በግንቦት ወር አጋማሽ የተሻለ ጊዜ ይመስላል።ምክንያቶቹ ሶስት ናቸው። እነርሱም -

1) በመጪው ክረምት ኢትዮጵያ የዓባይን ግድብ የምትሞላበት ጊዜ ነው።ይህ ጊዜ ደግሞ ካለፈው ዓመት ተሞክሮ እንደምንማረው የግብፅ ብቻ ሳይሆን የእርሷ ደጋፊዎች የሆኑ የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ጫና የሚበዛበት ነው።ስለሆነም ኢትዮጵያ ምርጫዋን በጊዜ አጠናቃ ወደ ውሃ ሙሌቱ  መሄዱ ከውስጥ ጥንካሬ አንፃር አስፈላጊ ነው።

2) ሚያዝያ 24/2013 ዓም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የትንሣኤ በዓል ነው።ይህ ማለት ከበዓሉ በፊት ያለው ሳምንት የሰሞነ ሕማማት ሳምንት ነው።ይህ ማለት በኢትዮጵያ በርካታ ከተሞች እና ገጠሮች ብዙ ሕዝብ በነቃ ሁኔታ የማይሳተፍበት ሁኔታ አለ ማለ ትነው ።

3) ግንቦት 5/2013 ዓም የኢትዮጵያ እስልምና ዕምነት ተከታዮች የረመዳን ፆም የሚፈታበት ጊዜ ነው።በመሆኑም ከግንቦት 5 በፊት ያለው አንድ ወር የፆም ወቅት በመሆኑ አሁንም በርካታ ኢትዮጵያውያን በእዚህ ወቅት በተገቢ መልክ በምርጫው ሂደት ሊሳተፉ አይችሉም ማለት ነው።

በመሆኑም የዘንድሮው ምርጫ ቀን ከተወሰነ በኃላ የማኅበራዊ ሚድያውም ሆነ ህዝቡ ቅሬታ እንዳያቀርብ ከላይ የተጠቀሱት ሶስት ሁኔታዎች ከግንዛቤ ውስጥ መግባታቸው እንደ ሀገር ጠቃሚ ነው።
================
ማስታወቂያ 
============
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ የሚችሉበት አዲስ ቴክኖሎጂ ጉዳያችን ማስተዋወቅ ጀምራለች።
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Sunday, December 13, 2020

እንዳንረሳ! ኢትዮጵያን እግዚአብሔር ከአቅም በላይ የሆኑባትን ፈተናዎች እያሻገረ እዚህ አድርሷታል።እናመስግነው!!!


ማስታወቂያ 
============
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ የሚችሉበት አዲስ ቴክኖሎጂ ጉዳያችን ማስተዋወቅ ጀምራለች።
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 



Saturday, December 12, 2020

ትግራይ ወደ አዲስ እና የተሻለ ሕይወት ጉዞ ጀምራለች።የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ካቤኔ በ24 ሰዓት ውስጥ ወደ ሥራ ይገባል።በትግራይ የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞችም ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ ሥራ ይጀምራሉ።



In Ethiopia,Tigray region interim Government Cabinet will start its function within 24 hours.On Monday all civil servants of the region will be back to work.Government office will be open. 
------------------------------------
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ካቤኔ ከነገ ጀምሮ ወደ ስራ እንደሚገባ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ አስታወቁ።የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ በትግራይ ክልል ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክተው ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም በትግራይ ክልል ሁሉም የመንግስት መስሪያ ቤቶችና የንግድ ድርጅቶች አገልግሎት መስጠት እንዲጀምሩ ከሚለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ የአገልግሎት መስጫ ተቋማት ለህዝብ ክፍት እንዲሆኑና ነዋሪዎች ደህንነታቸው ተጠብቆ ወደ እለት ተለት እንቅስቃሴያቸው እንዲመለሱ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ የክልሉን ካቤኔ ማዋቀሩን የገለጹት ዶክተር ሙሉ፤ ካቤኔው ከነገ ጀምሮ ወደ ስራ እንደሚገባ አረጋግጠዋል።

በህወሃት ጁንታ ተግባር ተደናግጠው ስራ ያቆሙ የመንግስት ሰራተኞችም ከፊታችን ሰኞ ጀምረው ወደ ስራ ገበታቸው እንዲመለሱ ዶክተር ሙሉ አሳስበዋል።

በተጠቀሰው ቀን ወደ ስራ ገበታው የማይመለስ የመንግስት ሰራተኛ ካለ በገዛ ፈቃዱ ስራውን እንደለቀቀ ተደርጎ እንደሚወሰድም አስገንዝበዋል።

“የመንግስት ሰራተኞች የህዝብ አገልጋይ እንጂ የፖለቲካ ፓርቲ አጀንዳ አስፈጻሚ አይደሉም” ያሉት ዶክተር ሙሉ፤ ሰራተኞች ይህን ተገንዝበው ሙያዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

መቐለን ጨምሮ አብዛኛው የክልሉ ከተሞች ላይ ሰላምና መራጋጋት መፈጠሩን ጠቁመው፤ “የንግድ ድርጅቶች ከነገ ጀምሮ ወደ መደበኛ ስራቸው መመለስ አለባቸው” ብለዋል።

በተጨማሪም በህጋዊም ሆነ በህገ ወጥ መንገድ የጦር መሳሪያ የታጠቀ ማንኛውም ግለሰብ እስከማክሰኞ ታህሳስ 6 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ ትጥቁን በአቅራቢያው ለሚገኝ የጸጥታ አካል እንዲያስረክብ ዶክተር ሙሉ ማሳሰባቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

“ከማክሰኞ በኋላ የቤት ለቤት ፍተሻ እንደሚደረግ ጠቁመው፤ በፍተሻው ትጥቅ የተገኘበት ግለሰብ ሲያጋጥም ተጠያቂ ይሆናል” ብለዋል።

ጊዜያዊ አስተዳዳሩ ክልሉን ወደ ሰላምና መረጋጋት ለመመለስ በሚያደርገው ጥረት ላይ የክልሉ ነዋሪዎች የተለመደ ትብብራቸውን እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርበዋል።

ምንጭ - ዋልታ 




ማስታወቂያ 
============
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ የሚችሉበት አዲስ ቴክኖሎጂ ጉዳያችን ማስተዋወቅ ጀምራለች።
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Thursday, December 10, 2020

ለአንድ ወር የሚቆይ በሁሉም የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን በቀጥታ የሚተላለፍ፣ሁሉም ቤተ ዕምነቶች የሚሳተፉበት የጸሎት እና የትምህርት መርሐ ግብር ስለ ሶስት ምክንያት ያስፈልጋል።

 

ባለፈው ዓመት የኮቪድ 19 ወረርሽኝ እንደጀመረ መላው ዓለም በተጨነቀበት ጊዜ በኢትዮጵያም ከፍተኛ መረበሽ ይታይ ነበር።በወቅቱ ጉዳያችን ቤተ ዕምነቶች በወረርሽኙ ከተዘጉ የመንግስት ሚድያዎች የቀጥታ የጸሎት እና ትምህርት መርሃ ግብር አስፈላጊነት ላይ ፅፋ ነበር።የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤም ከመንግስት ጋር ተነጋግሮ ሁሉም ቤተ ዕምነቶች የቴሌቭዥን የአየር ጊዜ አግኝተው መርሃ ግብሩ በሚገባ ተከናውኖ ነበር።በእዚህም ህዝቡ ከአምላኩ ጋር የተገናኘበት ጊዜ ብቻ ሳይሆን ዕምነቱን የዘነጋውም ጭምር ወደ ቀልቡ እንዲመለስ አድርጎ አልፏል።በእዚህ ጸሎት ጭምር ነው ኮቪድ 19 በኢትዮጵያ ብዙ የተያዘ ሰው ቢኖርም ነገር ግን  ሕይወት እስክያገድ ድረስ የማይደርስ ደረጃ ደርሶ ይሄው ክትባቱ መገኘቱ የተሰማበት ዘመን ደርሰናል።

አሁን ባለንበት ጊዜም ይሄው ተመሳሳይ አገልግሎት ሕዝብ ማግኘት ያለበት ጊዜ ነው። ለእዚህም ሶስት ምክንያቶች መጥቀስ ይቻላል። እነርሱም።

1) ክፉ ሲሰማ የሰነበተ አዕምሮ እንዲረጋጋ እና የስነ ልቦና ፈውስ እንዲያገኝ 

ሕዝብ በትግራይ ሲደረግ በነበረው የሕግ ማስከበር ዘመቻ ተከትሎ ስለ ማይካድራ የዘር ፍጅት፣በህወሓት የፅንፍ ኃይል በወታደሮች ላይ ስለተፈፀመ አሰቃቂ ስቃይ፣ሲሰማ የከረመ ሕዝብ ነው ያለው።ከድርጊቱ አሰቃቂነት፣ከክህደቱ ግዝፈት እና ሌሎችም አንፃር የብዙ ሰው ልቦና አዝኗል።ስለሆነም ይህ የጸሎት መርሐ ግብር መኖሩ ሕዝብ ያፅናናል፣ተስፋ ያለመልማል፣ሕዝብ ለሕዝብ ያቀራርባል፣በሕዝብ ውስጥ ያለ የቁጣ ስሜት ያበርዳል።

2) ምስጋና ስለሚያስፈልግ 

ምስጋናው ሀ) ኢትዮጵያን ሊያፈርስ ጫፍ ከደረሰ አደጋ ሀገሪቱን መታደግ በመቻሉ ምስጋና ስለሚያስፈልግ፣

            ለ )የኮቪድ ወረርሽኝ በተፈራው መጠን ባለመሆኑ ምስጋና  ስለሚያስፈልግ እና 

            ሐ) ኢትዮጵያ ዓለም ሁሉ ጥርስ ነክሶባት የዓባይ ግድብን የመሙላት የመጀመርያ ደረጃ በሰላም በመሳካቱ የሚሉት ተጠቃሽ ምክንያቶች ይሆናሉ።

3)   ስለመጪው ሁለት ወሳኝ ጉዳዮች ለመፀለይ።መጪዎቹ ሁለት ሃገራዊ ወሳኝ ጉዳዮች አንዱ  የአባይ ግድብ ቀሪ የመሙላት ተግባር ማከናወን ሃገራዊ ምርጫ የሚሉት ይጠቀሳሉ። 

ስለሆነም የመንግስት ሚድያዎች የአየር ሰዓት ለሁሉም ቤተ ዕምነቶች ሰጥተው፣ባለፈው የታዩት ችግሮች አርመው ለአንድ ወር የሚቆይ የፀሎት እና ትምህርት የቀጥታ ስርጭት መፈቀዱ የህዝብ አዕምሮ ከማነቃቃቱ በላይ ትልቅ ሀገራዊ መረጋጋት እና በረከት ያወርዳል።
====================
ማስታወቂያ 
============
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ የሚችሉበት አዲስ ቴክኖሎጂ ጉዳያችን ማስተዋወቅ ጀምራለች።
ማሳሰቢያ ለጥቂት ቀናት የሚቆይ 50%ጭማሪ ጉርሻ አለዎት። ይህ ማለት እርስዎ የ100 ብር ካርድ ቢልኩ ተቀባዩ 150 ብር ካርድ ያገኛል።
የ200 ብር ካርድ ከላኩ ተቀባይ ወዳጅዎ ወይንም ቤተሰብ 300 ብር ካርድ ያገኛል እንዲህ እያለ ይቀጥላል።ይህ ጉርሻ ለጥቂት ቀናት የሚቆይ ስለሆነ በዕድሉ ይጠቀሙ 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Monday, December 7, 2020

ኢትዮጵያ እነኝህ ሶስቱን ግዙፍ አደገኛ ፈንጆች ካላመከነች መልሳ ፈተና ውስጥ ትገባለች።መንግስት ካለምንም ማወላወል...


ማስታወቂያ 
============
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ የሚችሉበት አዲስ ቴክኖሎጂ ጉዳያችን ማስተዋወቅ ጀምራለች።
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ በኬንያ ጉብኝት ያደርጋሉ።Gudayachn Exclusive - In this week,Ethiopian PM Abiy Ahmed will visit Kenya.

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ እና ፕሬዝዳንት ኡሁሩ 


ጉዳያችን ዜና - 
ኅዳር 28/2013 ዓም (ደሴምበር 7/2020 ዓም)
=======
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አሕመድ በያዝነው ሳምንት አጋማሽ ማለትም በመጪው ረቡዕ ወደ ኬንያ እንደሚሄዱ እና ጉብኝት እንደሚያደርጉ ጉዳያችን ሰምታለች።ይህ ጉብኝት በትግራይ የሕግ ማስከበር እርምጃ ከተጀመረ ወዲህ የመጀመርያው የውጪ ጉዞ ነው የሚሆነው።በእዚህ ጉዞ ላይ ከኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር በመሆን ሁለቱ መሪዎች በሞያሌ  የተከፈተውን አዲሱን የሁለቱን ሀገሮች መንገድ ይመርቃሉ።መንገዱ በኢትዮጵያ እና በኬንያ መካከል በሚኖረው የመሬት ላይ ጉዞ አንድ ቦታ ብቻ የሚቆምበት እና ከእዚህ በፊት ከነበራቸው ግንኙነት በተሻለ መንገድ የሁለቱንም ሀገሮች ህዝቦች ግንኙነት እንደሚያቀላጥፍ ታምኖበታል።

በሌላ በኩል ሁለቱ መሪዎች በእዚህ ግንኙነታቸው በገንባት ላይ ያለውን ለኢትዮጵያ እና ለደቡብ ሱዳን አገልግሎት እንዲሰጥ የታሰበውን የላሙ ወደብ ሥራ ይጎበኛሉ።የላሙ ወደብ የኬንያ የባህር ዳር ወደብ ስትሆን ከሞምባሳ ወደብ በተሻለ ለኢትዮጵያ እና ለደቡብ ሱዳን ቅርበት ያላት ወደብ ነች።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አሕመድ በመጪው ረብዕ በቀጥታ የሚሄዱት ወደ ሞያሌ ሲሆን፣የኬንያው ፕሬዝዳንትም አቀባበል የሚያደርጉላቸው በእዚችው በመርሳ ቤት ክፍለሀገር ውስጥ በምትገኘው የኬንያ ዝነኛ የወደብ ከተማ ነው።

ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ልማት ባንክ የ1ነጥብ 2 ሚልዮን ዶላር ገንዘብ ድጋፍ ወደ አዲሱ የኬንያ ወደብ እና ወደ ደቡብ ሱዳን እንደሚዘረጋ በሚጠበቀው የባቡር መስመር ግንባታ የመጀመርያ ጥናት የሚውል አግኝታለች።የአሁኑ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉዞ የወደቡን ሁኔታ ለመገምገም አንዱ አጋጣሚ እንደሚሆን ታምኖበታል።ኢትዮጵያ እና ኬንያ በአሁኑ ጊዜ እጅግ የሰመረ ግንኙነት ካላቸው ሀገሮች ውስጥ የሚመደቡ ሀገሮች ናቸው።በህወሓት ዘመን ኬንያን ጨምሮ የብዙ ጎረቤት ሀገሮች ጭንቀት ከምር የማያምኗቸው ባለስልጣናት በአዲስ አበባ ቤተ መንግስት መኖር ነበር።

ጉዳያችን 
===========================
ማስታወቂያ 
============
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ የሚችሉበት አዲስ ቴክኖሎጂ ጉዳያችን ማስተዋወቅ ጀምራለች።
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Sunday, December 6, 2020

አስደሳች ዜና! በፈጣን ቶፕ አፕ ስልክ ካርድ ለወዳጅ፣ቤተሰብ ይላኩ!





አስደሳች ዜና 
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ እና ኢንተርኔት ሂሳብ ሊሞሉ የሚችሉበት አዲስ ቴክኖሎጂ ተጀምሯል።
ይፍጠኑ! ይጠቀሙበት! ወዳጅ ዘመዶችዎን አሁኑኑ ያስደስቷቸው።
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ የሚችሉበት አዲስ ቴክኖሎጂ ጉዳያችን ማስተዋወቅ ጀምራለች።
ከእርስዎ የሚፈለገው የስልክ ሂሳቡን ለመሙላት የሚፈልጉት  የቤተሰብዎን ወይንም ወዳጅዎን ስልክ ማወቅ እና በሚፈልጉት የክፍያ መልክ ክፍያውን መፈፀም ነው።
አሁን ባለው ደረጃ በአንድ ጊዜ ከ 100 እስከ 3000 የኢትዮጵያ ብር ሀገር ቤት መላክ ይችላሉ።
ሀገር ቤት ለሚገኝ ቤተሰብ ወይንም ወዳጅ ስልክ በሞሉ ቁጥር የሀገር ቤት ተቀባይ የስልክ አገልግሎቱን ብቻ ሳይሆን የኢንተርኔት የመጠቀሚያ ጊዜውን አንድ ላይ እያሳደጉ መሆኑን ይወቁ።
ክፍያውን እንደፈፀሙለት በሀገር ቤት የሚገኘው ተጠቃሚ ወዲያውኑ ከኢትዮጵያ ቴሌኮምኒኬሽን የስልክ እና ኢንተርኔት ገንዘቡ በላኩት የገንዘብ መጠን ወደ ብር ቀይሮ የስልክ ሂሳቡ  ማደጉን የሚገልጥ መልዕክት ይደርሰዋል።
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Wednesday, December 2, 2020

ማሳሰቢያ ለማኅበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች በሙሉ!



>> ትዕግስት፣አስተዋይነት እና ንቃት! ይፈለጋል።
>> ሶስት ዓይነት ወገኖችን የማኅበራዊ ሚድያን ለማተራመስ እንደሚሰሩ በቀጣይ ቀናት ጠብቁ።
=================
በሀገር ውስጥ የሚገኙ የማኅበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎችም ሆኑ በአውሮፓ፣አሜሪካ እና በተለይ መካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ የማኅበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች ከምንጊዜውም በላይ ትዕግስት፣አስተዋይነት እና ንቃት! ሊኖራቸው ይገባል።ይሄውም በኢትዮጵያ ካለው ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ለውጦች እና ሰሞናዊ ሁኔታዎች እየተከተለ የማኅበራዊ ሚድያውንም አንዱ ሕዝብ የማወኪያ መንገድ እንዳይሆን ጥንቃቄ ከወዲሁ ማድረጉ ተገቢ ነው። 

ስለሆነም በቀጣይ ጊዜዎች ውስጥ ሶስት  ዓይነት ወገኖች የበዛ የዘረኝነት ንግግሮች የሚለቁ ሊኖሩ ይችላሉ። እነርሱም- 

1) በሰሞኑ የኢትዮጵያ ሁኔታ ስሜት ውስጥ የገቡ -

የሕግ ማስከበሩ ሂደት ውጤት የሚፈጥረው ስሜታዊ ሁኔታዎች ይኖራሉ።እነኝህን ስሜታዊ ሁኔታዎች በጊዜ እስኪሰክኑ ማሳለፍ ያስፈልጋል።በሂደት ነገሮች በአንድ ጊዜ ግልብጥ ሲሉ የሚፈጠሩ ስሜቶች የሚፈሩት ጉዳይ አለመሆኑን ወይንም ይልቁንም የተሻለ ሁኔታ መኖሩን ሲረዱ የቀደመውን ስህተት ያርማሉ።

2) የራሳቸው ወገን በዘረኝነት አልነሳ ያላቸው ሌላውን በመተንኮስ ለመቀስቀስ የሚፈልጉ -

እነኝህ ወገኖች የበዛ የዘረኝነት ቪድዮዎች የሚለቁበት ዋና ዓላማቸው የሚሰድቡት አካል ከእዚህ የበለጠ የዘረኝነት ቀስቃሽ ቪድዮ እንዲለቅ ለመቀስቀስ  እና በውጤቱም የራሳቸውን ጎሳ አበሳጭተው 'ይሄው እነእንቶኔ እንዲህ እያሉህ ነው' ብለው  መልሰው ለማነሳሳት ነው።ስለሆነም ከፍተኛ ትዕግስት፣አስተዋይነት እና ንቃት ያስፈልጋል።እነኝህ ለረጅም ጊዜ በእዚሁ ተግባራቸው ተሰማርተው መገኘታቸውን ካወቅን በፍጥነት ባሉበት ሀገር  ላለው የፀጥታ አካል ማሳወቅ ያስፈልጋል።ምክንያቱም እነኝህ በጊዜያዊ ስሜት ወይንም ካለማወቅ ሳይሆን ስራዬ ብለው እየሰሩ ስለሆነ ለሕዝብ አደገኞች ናቸው።

3) አማርኛ፣ኦሮምኛ ወይንም ትግርኛ እና ሌሎች ሀገርኛ መግባብያዎች ተናጋሪ ባዕዳን 

በማኅበራዊ ሚድያ ላይ ብዙ ሰው በአማርኛ፣ኦሮምኛ ወይንም ትግርኛ ወይንም ሌሎች ሀገርኛ መግባቢያ በመፃፉ ብቻ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ወይንም ኢትዮጵያዊ ነው ብሎ የማመን ችግር አለ።በአሁኑ ጊዜ አንድ ሀገር ለማተራመስ እንደ ማኅበራዊ ሚድያ አመቺ የሆነ ቀላል ግን ትልቅ ትርምስ የሚፈጥር ጉዳይ የለም።ስለሆነም ኢትዮጵያን የማይፈልጉ እና በውስጥ ሀገር ለማተራመስ የሚፈልገውን አካል ለመርዳት የሚያስቡ ባዕዳን በከፍተኛ በጀት የሚንቀሳቀሱበት እና የሚሰሩበት ጉዳይ የማኅበራዊ ሚድያ ነው።ስለሆነም እጅግ የከፉ ከፋፋይ የዘርኝነት መርዞች የሚረጩት፣ሃሳቡ የሚመነጨው ኢትዮጵያን በሚገባ ባጠኑ ከፍተኛ ባለሙያዎች ሁሉ እንደሆነ መረዳት ያስፈልጋል።

በመሆኑም የማኅበራዊ ሚድያው የኢንተርኔት አገልግሎት ቆሞባቸው የነበሩ የሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች ሲለቀቁ  የሚኖሩትን ሁኔታዎች በመረዳት የሚከተሉትን ሶስት ተግባራት በመተግበር ሕዝብን ማረጋጋት ያስፈልጋል።እነርሱም -

1) የዘረኝነት መልዕክቶችን ለሌላው ባለማካፈል፣

2) ለረጅም ጊዜ በእዚህ እኩይ ተግባር የተሰማሩትን ለሕግ አስከባሪ አካላት በማቅረብ እና 

3) የሕዝቡን የእርስ በርስ መቀራረቦች የሚያሳዩ ቪድዮዎች፣ዜናዎች እና የኪነ ጥበብ ትዕይንቶችን በማካፈል ተግባር ላይ ማትኮር ይገባል።

ባጠቃላይ የማኅበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች እነኝህን ሁኔታዎች ከግንዛቤ አስገብተው እራሳቸውን፣ቤተሰባቸውን እና ማኅበረሰባቸውን መጠበቅ ያስፈልጋቸዋል።


Saturday, November 28, 2020

የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እና የትግራይ ሕዝብ ታሪክ ሰርተዋል! አሁን ርዝራዥ ህወሓት ማኅበራዊ ሚድያው ላይ ሊያስነሳቸው የሚችላቸውን ሶስት ቀዳዳዎች ቀድመን እንወቅ!

ዛሬ ህዳር 19/2013 ዓም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ከ600 ኪሎሜትር በላይ በእግሩ ተጉዞ የመቀሌ ከተማ እና የትግራይ ክልልን ከህወሓት ነፃ አውጥቷል።ይህ ድል የትግራይ ሕዝብ ህወሓት እንደሚለው ሳይሆን ለዲሞክራሲ፣ለፍትሕ እና ለእኩልነት ያለውን ፅኑ ፍላጎት የመከላከያ ሰራዊቱን በማክበር አሳይቷል።በእዚህም የትግራይ ሕዝብ ባለፉት 25 የዘመቻ ቀናት ውስጥ ድምፁን ከፍ አድርጎ ለኢትዮጵያ ሕዝብ አሰምቷል።ከሁሉም ደግሞ ነፃነቱ  በነፃ አውጪ የመጣ ሳይሆን የሁሉም የጋራ በሆነው በመከላከያ ኃይል መምጣቱ እንደሀገር ትልቅ ቁም ነገር አለው።በእርግጥ በእዚህ ዘመቻ ላይ የዓማራ እና የአፋር ልዩ ኃይሎች ቢካፈሉም በዋናነት የመከላከያ ሰራዊት የመራው እና ያጠናቀቀው መሆኑ እንደ ሀገር ትልቅ መልዕክት አለው።ይህንን ለመዘርዘር ብዙ ማለት ይችላል።አሁን ጊዜ ስለሌለ አልፈዋለሁ።

አሁን ርዝራዥ ህወሓት ማኅበራዊ ሚድያው ላይ ሊያስነሳቸው የሚችላቸውን ሶስት ቀዳዳዎች ቀድመን እንወቅ! እነርሱም 

1ኛ) በዓማራ ስም የማኅበራዊ ሚድያ በመክፈት ዓማራ አሸነፈ በሚል የሚፎክሩ ድምፆች በማብዛት የትግራይን ሕዝብ ለማበሳጨት መሞከር፣

2ኛ) በኦሮሞ ስም በተከፈቱ ማኅበራዊ ሚድያዎች ስም በዓማራ ላይ የሚፎክሩ ድምፆች ማብዛት እና 

3ኛ) በመንግስት ባለስልጣናት በተለይ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ ከቀድሞ የበለጠ ዘመቻ ማካሄድ የሚሉት ናቸው።

ስለሆነም ከላይ የተጠቀሱትን ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ሁሉም ጥንቃቄ ከማድረግ ባለፈ መሬት ላይ መሰራት ያለባቸው፣የሕዝብ ስሜት፣ሃዘን፣መቃቃርን የሚያርቁ ስራዎች ላይ በቶሎ መሰማራት አስፈላጊ ነው።

ይህ በእንዲህ እያለ  ለኢትዮጵያ ብዙ የመሰከሩ፣የተሰደዱ እና የተሰዉላት ምስጋና እንደሚገባቸው ሳንረሳ፣ዛሬ  ኢትዮጵያ ባለችበት ፈታኝ ጊዜ ለሰጡት ብቃት ላለው አመራር ለጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ታላቅ ምስጋና ይገባቸዋል። 

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ 







Thursday, November 26, 2020

Ethiopian Government has already started to provide humanitarian aid to internally displaced people in Tigray Region

Gudayachn News

Ethiopian Government today announces providing Humanitarian aid to the Tigray region under the control of the National army, has already started.The latest press release from the Prime Minister, Abiy Ahmed's office explained that the emergency food,drinking water, medicines and other non-foodstaf items are also providing to internally displaced people in the region.


The  PM press release  in Amharic also elaborated, the special committee from different Federal offices is currently on action and as the result four refugee camps are establishing.


The latest press release concluded its statement by emphasizing  as the government is highly interested to cooperate and coordinate its humanitarian works with all aid organizations including the United Nations agencies.



በትግራይ ክልል የመከላከያ ሠራዊቱ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች የሰብአዊ እርዳታ እየቀረበ ነው፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት
*************

በትግራይ ክልል የመከላከያ ሠራዊቱ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች የሰብአዊ እርዳታ እየቀረበ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት አስታወቀ።

የፌዴራል መንግስት በትግራይ ክልል ለሚገኙ ዜጎች የሚያስፈልገውን የሰብአዊ እርዳታ ለማድረስ ትኩረቱን ሰጥቶ እንደሚሰራም አስታውቋል።

መንግስት በቀጣይም ከአጋር ለጋሽ ድርጅቶች ጋር በመተባበር የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው ያስታወቀው።

በክልሉ በተለይ ከመኖሪያቸው ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚያስፈልጋቸውን ድጋፍ በአፋጣኝ ለማድረስ የሰላም ሚኒስቴር ከሌሎች የፌዴራል ተቋማት ጋር በጋራ እየሰሩ መሆኑ ተገልጿል።

በዚህም የምግብ፣ የመጠጥ ውሃ፣ መድሀኒት እና ሌሎች ምግብ ነክ ያልሆኑ አቅርቦቶችን የፌዴራል መንግስቱ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች በመጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ ለሚገኙ ተፈናቃዮች ማቅረብ ተጀምሯል።

በስፍራው በአሁኑ ወቅት ስደተኞችን ተቀብሎ ለማስተናገድ የሚሆኑ አራት መጠለያ ጣቢያዎች ለማቋቋም እየተሰራ ሲሆን ይህን ለማስተባበር የተቋቋመው ኮሚቴም ዜጎችን በፍቃዳቸው መልሶ ለማቋቋም እንደሚሰራ ተገልጿል።

መንግስት የተሰደዱ ኢትዮጵያውያንን መልሶ ለማቋቋም እና የተባበሩት መንግስታት ኤጀንሲዎችን ጨምሮ ከሁሉም ዓለም አቀፍ የተራድኦ ድርጅቶች ጋር በጥምረት ለመስራት ያለውን ቁርጠኝነት አረጋግጧል።

Wednesday, November 25, 2020

ቢቢሲ እንግሊዝኛ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ያላሉትን ለጥፎ የኢትዮጵያ የመረጃ ማጣርያ ያዘው Ethiopian Gov't Fact-Checker Accuses BBC of Disinformation for Misquoting Prime Minister

Please find the English version under the Amharic.

ቢቢሲ እንግሊዝኛ  ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ያላሉትን ለጥፎ የኢትዮጵያ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ማጣርያ ያዘው።ቢቢሲ ከየት እንዳመጣው ባልታወቀ ፅሁፍ ላይ በገፁ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ''የፈለገው ይሙት'' አሉ የሚለውን የውሸት ዜና ጨምሮ በገፁ ላይ ለጥፎ የነበረ ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስት መረጃ ማጣርያ ከደረሰበት እና ውሸቱን ካጋለጠ በኃላ ከገፁ ላይ ማንሳቱ ለማወቅ ተችሏል።ለንፅፅር ቀደም ብሎ ተለጥፎ የነበረው ዜና እና የመንግስት መረጃ ማጣርያ ሐሰት መሆኑን ጠቅሶ የፃፈውን ከስር ይመልከቱ።

The Ethiopia State of Emergency fact-checker today accused BBC’s Monitoring service for spreading disinformation for statements to Prime Minister Abiy Ahmed.The fact-checker said that the PM has never uttered such statement.

BBC monitored news was posted as if the PM said the war in Tigray region will go on regardless of civilian casualties which has never said by the PM.

Late after hours, Gudayach could realized as the BBC monitored news was deleted.But the matter is so serious and many African countries are watching the action seriously.For your easy information, please find both posts here below. 

* The new development is that BBC monitoring excuses for the mistake (please find the excuse tweeter also here below)

Add caption





Saturday, November 21, 2020

The operation to maintain law and order will have a positive effect on future horn stability

The Ethiopian Herald Newspaper,Addis Ababa, Ethiopia

November 18/2020

BY GETACHEW BEKELE DAMTEW

The Ethiopian government’s operation to maintain law and order has continued for the second week. Government sources, quoted by Reuters, disclosed that when the TPLF (Tigray People’s Liberation Front) junta fled from Alamata town, they have taken 10,000 prisoners with them to an unknown place. Shockingly, last week, the junta committed ethnic mass killing on 500 innocent Amharas in Mai-Kadra town as has confirmed by Amnesty International and the UN called the incident an international war crime.

On the other hand, some local and international media outlets in the west are trying to mislead their followers regarding the situation. However, to clearly understand the situation, it is quite important to understand the background of the real political, social and economic situations of Ethiopia for the past three decades and the recent reform taking place in the country since Prime Minister Abiy Ahmed came to power some two and half years ago.

The Background of TPLF

It was in 1991 that TPLF changed itself from a rebel group to the leader of one of the ancient countries in Africa, Ethiopia. For long, the TPLF dominated the now-dissolved ruling coalition, the Ethiopian Peoples’ Revolutionary Democratic Front (EPRDF) and as soon as they grabbed state power, they tried to divide Ethiopia by supporting the establishment of ethnocentric political parties and ideology. The EPRDF is a coalition of pseudo ethnic parties that represent Amhara, Oromo and southern nations and nationalities, their establishment was meant to aid TPLF’s objectives and goals.

During those turbulent times, almost all genuine opposition parties and independent media outlets were banned as they were labeled ‘terrorists’ by parliament and judicial body. The reports of international human rights groups and journalists’ associations including Amnesty International and International Association of Journalists as well as the US government’s annual reports repeatedly published the grave human and democratic rights violations in Ethiopia under the TPLF.

TPLF’s 27 years rule can be characterized by ethnic hatred, divisions, clashes and intimidations. As a result, thousands were displaced, killed and sent to prison only for their views.

The miserable situation did not manifest in political and social life only. The country’s economy was almost fully under the control of a few ethnocentric pro-TPLF groups. Endowment Fund for the Rehabilitation of Tigray (EFORT) was one of the giant ethnocentric business organizations in Africa according to its former Managing Director Sibhat Nega’s interview with Voice of America’s Amharic Service. Here we should note that the rehabilitation fund has not been rehabilitating the people of Tigray. Rather, its sole purpose has been strengthening the financial muscle of the clique in the TPLF.

The injustice and the oppression gave birth to rebellion movements and uprising within the youth in Amhara, Oromia and Southern Nations, Somali and other nations in Ethiopia. The youth started to protest against injustice and systematic marginalization. Strong but peaceful protests in Oromia state, peaceful demonstration and armed movements in Amhara state combined with the strong resistant movement in the Diaspora brought about change in Ethiopia. That is why former Prime Minister Hailemariam Desalegn resigned on March 27, 2018, opening the door for the coming to power of Abiy Ahmed and the introduction of an overall reform in the country.

The journey in the last two years

Since March 2018, Ethiopia has experienced dramatic political, economic and social changes. Almost all political prisoners were released; all exiled political parties came back home. Previously banned newspapers, television stations and even blogs were allowed to legally operate in Ethiopia. Restrictive laws and regulations that dealt with Non-Governmental Organizations (NGOs), charities and civil societies were amended to give more space for freedom. The country is also opening up its door for privatization. On top of all these, the country has made peace with Eritrea, ending its two decades of hostile relations. As a result of his peace initiatives, PM Abiy won the 2019’s Nobel Peace Prize.

TPLF’s defiance to accept the change, conspiracy to destabilize Ethiopia and the Horn

Being a legally registered political party, TPLF has not chosen a legal path. Rather, it continued to engage in a conspiracy to destabilize the country as a response to losing power. In the past two years, it has become a major security threat to Ethiopia and the Horn of Africa region as a whole. It has been conspiring to instigate ethnic

 clashes in different parts of the country particularly in the western and southern parts. It has also allocated a huge amount of fund for its anti-peace activities.

With a view to instigate protests, the junta even sponsored the assassination of prominent individuals, including that of Ethiopian Afan Oromo singer Hachalu Hundessa last June. But the government tried to exercise patience in dealing with the junta. However, TPLF continues to violate the constitutional order as well as the basic legal, political and military rules of the nation.

We can mention so many incidents where the TPLF junta violated the law of the land. And it is possible to mention here a few instances where the junta totally violated the constitution and the law of the land. First of all, back in August, it conducted a sham regional election without the consent of the National Electoral Board, an institution constitutionally mandated with dealing with such issues. In fact, the government postponed the elections due to be held back in May/June at both the federal and state/regional level to prevent the spread of COVID-19.

Secondly, in addition to its massive negative propaganda against the central government, TPLF started to threaten sovereign neighbouring countries like Eritrea and Sudan. As a result, the Eritrean President Isayas Afeworki’s government discussed the issue repeatedly with its Ethiopian counterpart and the Intergovernmental Organization of the Horn of Africa (IGAD) has been following the situation seriously.

The TPLF junta has been trying to destabilize the region by interfering and undermining the activities of Ethiopia’s federal government which has a long reputation of playing a constructive role in the region. For instance, trespassing the federal government’s and the Ministry of Foreign Affairs’ authority, the junta tried to write letters to neighbouring countries and other the international partners of Ethiopia.

The Premier tried to tolerate all these with the intention of not disturbing national and regional peace. But, the junta interpreted the patience the other way round and once again engaged in a barbaric act. In an act of betrayal, the junta recently orchestrated an attack against the North Command base of the Ethiopian Army in Mekelle. As the Prime Minister put it, with this action, the TPLF crossed the last point of redline.

Hence, the operation to maintain law and order in Tigray region should be seen as an effort from the government’s side to ensure regional stability in the Horn of Africa.

The past week has shown us what the TPLF could do to destabilize the region if the government remained patient and reluctant to enforce rule of law. Its rocket attack towards Gondar city and Bahir Dar, the latter of which is the regional capital of Amhara state, as well as Asmara, the capital of Eritrea clearly demonstrate how the TPLF is a threat of regional stability.

The Ethiopian Herald November 18/2020

https://www.press.et/english/?p=30621# 


ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...