ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Saturday, June 30, 2018

ሰበር ዜና በጋምቤላ ክልል ሜጢ ከተማ እና ዙርያዋ በአማራ ተወላጆች ላይ እልቂት ሊፈፀም ነው መንግስት እንዲደርስ እየተጣሩ ነው (ጉዳያችን ልዩ ዜና Gudayachn Exclusive News)



ጋምቤላ ክልል
ጉዳያችን ልዩ ዜና (Gudayachn Exclusive Breaking News) 
ሰኔ 23፣2010 ዓም (ጁን 30፣2018 ዓም)

  • አሁን ያንዣበበው የሞት አደጋ እንዲቀረፍ አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጥ ለሚጠይቀው ሕዝብ መንግስት በሰዓታት ውስጥ እንዲደርስለት ተማፅኖ እየቀረበ ነው።
  • በአካባቢው ያሉ በኢንቨስተርነት የቡና እርሻዎችን የተቆጣጠሩ የቀድሞ የህወሓት ታጋዮች በአማራ እና መዥንገር መሃል ጠብ በመዝራት ነዋሪዎች እየከሰሷቸው ነው።
  • ለልዩ ልዩ ሥራ የሄዱ የትግራይ ተወላጆች በኢንቬስተር ስም ወደ ስፍራው የመጡ የህወሓት የቀድሞ ታጋዮች ከተግባራቸው እንዲታቀቡ አሳስበዋል።
  • የቀድሞ ታጋዮች ከአማራ ተወላጆች ተደብቀው የመዥንገር ተወላጆችን ጠርተው ያደረጉት ምስጢራዊ ስብሰባ ተደርሶበታል።

ሰላማዊው ክልል እንዴት ታመሰ?

የምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ከሃያ ሰባት አመታት በፊት ሰላማዊ ብቻ ሳይሆን ደርግ በ1977 ዓም በሀገራችን በተከሰተው ድርቅ ሳብያ ከወሎ እና ትግራይ ሰፋሪዎች በማምጣት ያሰፍርበት የነበረ ቦታ ነው።ላለፉት ሃያ ሰባት አመታት ግን አካባቢው በጎሳ ፖለቲካ ሆን ተብሎ እንዲታመስ በህወሓት እና ኢህአዴግ ተፈርዶበታል።ጉዳዩ መልኩን ቀይሮ ፖለቲካዊ ኢኮኖሚ ግጭት መነሻ እንዲሆን ያደረገው አንዱ እና አይነተኛ ምክንያት የቡና አምራች አካባቢዎችን ለመቆጣጠር የህወሓት የቀድሞ ታጋዮች መሬት በመውሰድ እና በመንጠቅ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ የኖሩ የአማራ ተወላጆችን ለዘመናት አብረው ከኖሩት ከመጀንገር እና ሸኮ ብሔር ጋር ግጭት እንዲፈጠር ሆን ተብለው መሰራታቸው ይታወሳል።በእዚህም ሳብያ እስከ አለፈው ዓመት ድረስ ሶስት ያህል አሰቃቂ ግጭቶች ተፈጥረዋል።በሁሉም ግጭቶች ላይ መፍትሄ ከመስጠት ይልቅ የህወሓት ኢህአዴግ ባለስልጣናት በባህላዊ መልክ የታረቀውን ማኅበረሰብ ሁሉ መልሰው ወደግጭት እንደመሩት ከቦታው የተገኘው መረጃ ይጠቁማል።

ለጉዳያችን ከታማኝ ምንጭ የደረሳት ዛሬ ያኮበኮበው የሞት አደጋ

ሰሞኑን  በእሊባቦር፣ሜጢ ከተማ በኢንቨስተርነት ስም የመጡ የቀድሞ የህወሓት ታጋዮች (ባብዛኛው ነዋሪውን የአማራ የቡና እርሻ ከመዠንገር ጋር እያጋጩ የነጠቁት ናቸው) ሚስጥራዊ ስብሰባ ከመዥንገር ጋር መደረጉ የተሰማው ስብሰባው እንዳለቀ ነበር።ቀደም ብሎ እነኝሁ ኢንቨስተር ተብዬ የቀድሞ ታጋዮች በቦቴ ነዳጅ ጫኝ መኪና ውስጥ እየደበቁ  ክላሽ እንዲታጠቅ ያደረጉት የመዥንገር ተወላጅ ስብሰባው ላይ የተነገረው ''አማራ ሊወረው እንደሆነ፣በያዘው መሳርያ እንዲፈጀው'' የሚል ማሳሰብያ እንደነበር ከስብሰባው የወጡ መረጃዎች ለአማራ ተወላጆች ይደርሳል።ይሄንኑ እኩይ ተግባር ከአማራው ጋር አብረው በጉርብትና እና ተባብረው የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆችም በሃዘን ይሰማሉ።ጉዳይ የአማራ ተወላጆች ጋር እንደደረሰ በሁሉም በኩል የትጥቅ ዝግጅት ተደረገ።ልብ በሉ በእዚህ ሁሉ መሃል በግጭቱ የሚያተርፉ የመሰላቸው በኢንቨስተርነት የመጡ የቀድሞ ታጋይ የህወሓት አባላት ናቸው።

ከእዚህ በፊት በቦታው ላይ በርካታ የአማራ የቡና እርሻ ባለይዞታዎችን ምንም  በማያውቁት ጉዳይ ግንቦት 7 ወዘተ እያሉ እስከ ቂልንጦ ድረስ ያሳሰሯቸው ግለሰቦች የቡና እርሻቸውን ተነጥቀው ባዶ እጃቸውን እንደቀሩ ዜናው ያብራራል።ሰሞኑን ይህ ውጥረት ከመፈጠሩ በፊት የተከሰተው ጉዳይ ቢኖር እነኝህ በግፍ የታሰሩ የአማራ እና በግጭት አሉበት ተብለው የታሰሩ የመዥንገር ብሔር ተወላጆች በዶ/ር አብይ የምህረት አዋጅ ብዙዎች እየተፈቱ ግፍ ወደ ተሰራባቸው አካባቢዎች መመለሳቸው ነበር።የቀድሞ የህወሓት ታጋዮች ይህንን ግጭት ያቀናበሩትም ከሰሩት ግፍ ስጋት እና የለውጥ ሂደቱን እንዲያደናቅፉ ከተሰጣቸው መመርያ አንፃር እንደሆነ የአካባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ።

ወደ ስብሰባው ጉዳይ እንመለስ እና በእዚህ ሳምንት የተደረገው ምስጢራዊ ስብሰባ በኢንቨስተር ስም ባሉት የህወሓት የቀድሞ ታጋዮች እና በመዥንገር መሃል የተደረገው ሚስጥር ከወጣ በኃላ እና በቦቴ እየተደበቀ ለመዥንገር መሳርያ ከታደለ በኃላ ዛሬ ቅዳሜ ጦርነቱ ሊከፈት ቀጠሮ ተይዞ እያለ የመከላከያ ሰራዊት እና ልዩ ኃይል ቀድሞ ሜጢ ከተማ ገቡ።ዛሬ የነበረው የቅዳሜ ገበያም ሳይደረግ ህዝቡ እንደጠፋጠጠ እንደሚገኝ እና ሌሊትም ውጥረቱ እንዳለ ለጉዳያችን ከታማኝ ምንጭ የደረሰው ልዩ ዜና ያብራራል።

መፍትሄው

ከላይ በጥቂቱ ለመግለጥ እንደተሞከረው የአካባቢው ግጭት ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ መልክ ከመያዝ አልፎ በሰሞኑ በሀገራችን ያለው የለውጥ ማዕበል ያላስደሰታቸው ወገኖች ደም እንደ ጎርፍ የሚፈስበት አንዱ የጥፋት ግንባር ለማድረግ አሰፍስፈዋል።ስለሆነም መግስት የሚከተሉትን ተግባራት በአፋጣኝ መውሰድ አለበት። እነርሱም : -
1ኛ) የደረሰው የመከላከያ ሰራዊት እና ልዩ ኃይል ቶሎ ለቆ እንዳይሄድ እና ለረጅም ጊዜ በከተማዋ እና በአካባቢው እንዲቆይ እንዲደረግ፣
2ኛ) በአካባቢው ግጭት የሚፈጥሩት በኢንቨስተር ስም የመጡ የቀድሞ የህወሓት ታጋዮች እና በስልጣን ላይ ያሉ የአካባቢው ባለስልጣናት  ውስጥ በግጭቱ ላይ እጃቸው ያለበት በቶሎ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ እና
3ኛ) በአማራ፣በመዥንገር እና ሸኮ ሽማግሌዎች መሃል የሚያጋጩትን ባልጨመረ መልኩ ልዩ ውይይት እንዲደረግ ፖለቲካዊ ኢኮኖሚ ጥቅምን ባማከለ መልክ እንዲፈቱ ሆኖ በባህላዊ እርቅ እንዲፈፀም ላለፈውም የካሳ ክፍያ እንዲፈፀም ማድረግ ይገባል።
ለማጠቃለል ግን አሁን ያንዣበበው የሞት አደጋ እንዲቀረፍ አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጥ ለሚጠይቀው ሕዝብ መንግስት በሰዓታት ውስጥ እንዲደርስለት ተማፅኖ እየቀረበ ነው።



ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

ኑ! ክፉውን ዘመን ኢትዮጵያ ጥላ ውስጥ ሆኖ ያሳለፈውን ክቡሩ ድምፃዊ ፀሐዬ ዮሐንስን እናክብር! (ቪድዮዎች)

ጉዳያችን/ Gudayachn
ሰኔ 23/2010 ዓም (ጁን 30/2018 ዓም)
ድምፃዊ ፀሐዬ ዮሐንስ 

ኢትዮጵያውያን እባካችሁ ፀሐዬ ዮሐንስን አግኑንልን።ፀሐዬ ኢትዮጵያን እንዳለ የኖረ የኢትዮጵያ ልጅ።
ክብር ዘመን ለማይቀይረው የኢትዮጵያ ልጅ ለድምፃዊ ፀሐዬ ዮሐንስ።
እናመሰግንሃለን! እንወድሃለን! ፀሐዬ ዮሐንስ።
ከእዚህ በታች የፀሐዬ ዮሐንስ ኢትዮጵያን ያገነነባቸው ቪድዮዎች ይመልከቱ።
ድምፃዊ ፀሐዬ ዮሐንስ ሩቅ አይደለም ቅርብ ነው ደሞ አይቀርም መድረሱ 
ያ!ገናናው ያ!ገናናው ስሟ ዳግም መመለሱ 

ትኑርልን ከነክብሯ ኢትዮጵያ የእኛ ናት 

ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Tuesday, June 26, 2018

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከሁለት ወደ አንድ ሲኖዶስ እንድትመለስ በቀጣይ ቀናት ውስጥ ምእመናን ማድረግ እና አለማድረግ ያሉባቸው ጉዳዮች

ጉዳያችን/ Gudayachn
ሰኔ 20/2010 ዓም (ጁን 27/2018 ዓም)

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ላለፉት ሃያ ስድስት ዓመታት ቅዱስ ሲኖዶስ ለሁለት ተከፍሎ፣በመንበራቸው የነበሩት ፓትርያርክ አቡነ መርቆርዮስ እና ሊቃነ ጳጳሳት ከሀገረ ስብከታቸው ተሰደው በውጭ ሀገር እየኖሩ እንደሆነ ይታወቃል።የቅዱስ ሲኖዶስ በሀገር ቤት እና በውጭ መኖር የቤተ ክርስቲያኒቱን አንድነት ብቻ ሳይሆን የተፈታተነው፣የምእመናንን መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ ግንኙነት በእጅጉ ጎድቶታል።ምዕመናን በተለያየ ፍረጃ ሳብያ እርስ በርስ ተቃቅረዋል።በተለይ ይህ ሁኔታ ፖለቲካዊ ቃና እየተሰጠው በርካቶች በሌሉበት ፖለቲካ እየተፈረጁ ከቤተሰባቸው ጭምር ስነ ልቦናዊ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በሀገር ውስጥ እና ውጭ በሚል መከፈል የቤተ ክርስቲያኒቱ ምእመናን ብቻ ሳይሆኑ አጠቃላይ የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሀብታዊ ጤናማ ግንኙነትን አዛብቶ ቆይቷል።ለእዚህም አንዱ ማሳያ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ከውጭ ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ጋር ያላትን ግንኙነት አዛብቶ ቆይቷል።ለምሳሌ የግብፅ ኮፕቲክ ቤተ ክርስቲያን እና በአውሮፓ እና አሜሪካ የሚገኙ የበርካታ ሀገሮች አብያተ ክርስቲያናት ከኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጋር የሚኖራቸው ግንኙነት ከውጭ ወይንስ ከሀገር ውስጥ ሲኖዶስ ጋር መሆን አለበት? የሚለው ጥያቄ አንፃር ከፍተኛ ውዝግብ ሲፈጠር ቆይቷል። በእዚህም ሳብያ ጉዳዩ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ግንኙነት አንፃር ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ በነበራት የዲፕሎማሲ ግንኙነት አንፃርም የእራሱን የሆነ ጥላ እንዳጠላ የሚታወቅ ነው።ከእዚህ ሁሉ ውጣ ውረድ በኃላ በቅርቡ ምናልባትም በሳምንታት ውስጥ በውጭም ሆነ በሀገር ውስጥ የሚገኙ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ለእርቅ እንደሚገናኙ መሰማቱ ይታወቃል።በእዚህ የእርቅ ሂደት ላይ የምእመናን ሚና ምን መሆን አለበት? የሚለው ጥያቄ መመለስ አስፈላጊ ነው።

ምእመናን ማድረግ የሌለባቸው 
  • በአባቶች እና በሊቃውንት ጉባኤ መታየት የሚገባቸው የሥርዓት (ቀኖና) ሂደቶች ላይ አባቶችን ተክቶ ሃሳብ በመስጠት ሌላ ንትርክ አለመፍጠር፣
  • የቅዱስ ሲኖዶስ በሁለት መከፈል ሂደት ላይ ዛሬ እያነሱ (ቢያንስ የእርቅ ሂደቱ እስኪያልቅ ድረስ) የታሪክ ንትርክ አለመፍጠር፣
  • በውጭም ሆነ በሀገር ቤት የሚገኙ አባቶችን የአንዳቸውንም እያነሱ የመደገፍ እና የማጥላላት ፅሁፎች አለመፃፍ እና 
  • ማናቸውም ልዩነቶችን የሚያሳዩ ጉዳዮች ላይ ምንም አይነት ንግግር፣ፅሁፍ እና አገላለጦችን ፈፅሞ ከመጠቀም መቆጠብ የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
ምእመናን ማድረግ የሚገባቸው  
  • አባቶች በምንም አይነት መልኩ የአሁኑን የእርቅ ዕድል እንዳያልፍ እንዲያደርጉ ደጋግሞ ማሳሰብ፣
  • የእርቅ ሂደቱ እንዲሳካ እና ምንም አይነት ከእርቅ ያለፈ ጉዳይ ምእመናን መስማት እንደማይፈልጉ አበክረው ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ለብፁዓን አባቶች በቃል፣በፅሁፍ እና ፔቲሽን በማዘጋጀት ጭምር ማሳሰብ እና 
  • ለእርቅ ሂደቱ የሚያስፈልገውን የሞራል እና የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
ከላይ የተጠቀሱትን ተግባራት ምእመናን እንዲያግዙ የተከፈቱ የፌስ ቡክ ገፅ እና የፔትሽን ማስፈንጠርያዎች ለእርቁ በጎ እሳቤ ይዘው በተነሱ ምእመናን ተከፍተው ሥራ ላይ ውለዋል።ምእመናን ይህንኑ አውቀው የፌስ ቡክ ገፁን ''ላይክ'' በማለት እና ፔቲሺኑን በመፈረም እንዲሳተፉ ጥሪያቸውን እያስተላለፉ ይገኛሉ።በእዚህም መሰረት  
የተከፈተው የፈስ ቡክ ገፅ ማስፈንጠርያ ለመክፈት የፌስ ቡክ ገፅ የሚለውን በመጫን መክፈት ሲችሉ፣ የፐቲሽኑ ማስፈንጠርያ ለመክፈት ደግሞ ፔትሽን የሚለውን በመጫን መክፈት ይቻላል።  

ባጠቃላይ ይህ ወቅት ወሳኝ ተግባራት የሚከወንበት እና የሁሉም ትኩረት በቤተ ክርስቲያኒቱ አንድነትና የአባቶች እርቅ ጉዳይ ከሁሉም በቀደመ መልኩ የምእመናን ተሳትፎ በእርቁ ሂደት ላይ የሚኖራቸው ድጋፍ መጎልበት እና አባቶች ከእርቅ ውጭ ምንም አይነት አማራጭ አለመኖሩን ደግሞ ማሳሰብ ባጠቃላይ ከሁሉም የሚጠበቅ የጋራ ተግባር ነው።
አበው ፀልዩ (የይልማ ኃይሉ) መዝሙር 



ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Wednesday, June 20, 2018

ኢትዮጵያ ሆይ እግዚአብሔርን አመስግኚ (ዘማሪ ይልማ ኃይሉ ቪድዮ)

ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com


ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com

Tuesday, June 19, 2018

ግዙፍ የድጋፍ ሰልፍ ቅዳሜ ሰኔ 16/2010 ዓም በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ይደረጋል።የሰልፉ አዘጋጅ ኮሚቴ ጋዜጣዊ መግለጫ ይከታተሉ።

  • ሰልፉ በዘጠና ቀናት ውስጥ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዓብይ ላከናወኑት እና ለርዕያቸው ያለውን ድጋፍ ሕዝብ ይገልጣል፣
  • ዲሞክራሲያዊ ለውጥ ይሞገሳል፣ ይህንን የለውጥ ሂደት ለማደናቀፍ የሚሞክሩ እንዳያስቡት ሕዝብ ማስጠንቀቅያ ይሰጣል፣
  • ኢትዮጵያዊነት፣ፍቅር እና መደመር ይሞገሳል።

ኮሚቴው ዛሬ ሰኔ 12/2010 ዓም የሰጠው መግለጫ 




ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Monday, June 18, 2018

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዓብይ በምክርቤት ቀርበው የተናገሩት (ቪድዮ)

=======================
ጉዳያችን/Gudayachn
ሰኔ 11/2010 ዓም (ጁን 19/2018 ዓም) ዛሬ  
===============
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዓብይ ሰኔ 11/2010 ዓም ፓርላማ ቀርበው የተናገሩት እና ያቀረቡት ሪፖርት።
ከስር የሚገኙት ቪድዮዎች  ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተናገሯቸው ርዕሶች በሶስት የተለያዩ ቪድዮዎች የተከፈሉ ናቸው። እነርሱም : -
  • ቪድዮ 1 ስለ ባድማ፣ስለ ኤርትራ የተናገሩት (20 ደቂቃ) 
  • ቪድዮ 2 ስለ ሙስና፣ የፍትህ ስርዓቱ እና የአፍሪካ ቀንድ ዙርያ ስለሰፈሩ የባዕዳን ጦር ጉዳይ (13 ደቂቃ)
  • ቪድዮ 3 የጠቅላይ ሚኒስትሩ ለምክር ቤቱ ያቀረቡት ሪፖርት እና ሙሉ በምክር ቤቱ የተነሱ ጥያቄዎች የመለሱበት ሙሉ ቪድዮ  
==============================
ቪድዮ 1 ስለ ባድማ፣ስለ ኤርትራ የተናገሩት (20 ደቂቃ)

ቪድዮ 2 ስለ ሙስና፣ የፍትህ ስርዓቱ እና የአፍሪካ ቀንድ ዙርያ ስለሰፈሩ የባዕዳን ጦር ጉዳይ (13 ደቂቃ)

ቪድዮ 3 የጠቅላይ ሚኒስትሩ ለምክር ቤቱ ያቀረቡት ሪፖርት እና ሙሉ በምክር ቤቱ የተነሱ ጥያቄዎች የመለሱበት ሙሉ ቪድዮ



ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Friday, June 15, 2018

ላለፉት 27 ዓመታት የሄድንበት የክልል ወሰን አቀማመጥ ጉዳይ ያስገኘውን ጥቅምና ጉዳት የሚመረምር ከሁሉም ወገን የተውጣጣ ጠንካራ ኮሚሽን ለመመስረት መታቀዱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዓብይ አስታወቁ (ቪድዮ)

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዓብይ ዛሬ ምሽት ሰኔ 8/2010 ዓም ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ባስተላለፉት መልዕክት በኢትዮጵያ ውስጥ አንዱን ከአንዱ የሚለይ ድንበር ሳይሆን ለአስተዳደራዊ ሥራ ብቻ ሲባል የተቀመጠ የአስተዳደር አከላለል መኖሩን አስታውቀው ላለፉት 27 ዓመታት የሄድንበት የክልል ወሰን አቀማመጥ ጉዳይ ያስገኘውን ጥቅምና ጉዳት የሚመረምር ከሁሉም ወገን የተውጣጣ ጠንካራ ኮሚሽን ለምመስረት መታቀዱን አስታውቀዋል። ሙሉ መልዕክቱን ከስር ከሚገኘው ቪድዮ ይመልከቱ።


ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Wednesday, June 13, 2018

የኢትዮጵያ ሕዝብ በመጪው ዕሁድ የህወሓትን መግለጫ ተቃውሞ በመላው የኢትዮጵያ ከተሞች ሰልፍ በመውጣት ህወሓትን ማስጠንቀቅ አለበት። መቶ ሚልዮን ሕዝብ ዲሞክራሲ ወይንም ሞት! ብሎ ለመፋለም መነሳት አለበት።(የጉዳያችን መልዕክት)


ጉዳያችን/ Gudayachn
ሰኔ 7/2010 ዓም (ጁን 14/2018)
  • የኢትዮጵያ ሕዝብ ሰኔ 9/2010 ዓም ቅዳሜ የመቀሌ ሰልፍ በተደረገ ማግስት ሰኔ 10/2010 ዓም ዕሁድ በአዲስ አበባ፣ሐዋሳ፣አዳማ፣ባህርዳር፣ጎንደር፣ደሴ፣ሐረር፣ነቀምት፣ወዘተ ዲሞክራሲ ወይንም ሞት! የሚል አስገራሚ ሰልፍ በማድረግ ለሕወሐትም ሆነ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ከዶ/ር ዓብይ የለውጥ ሂደት ጋር አብሮ መቆሙን ማሳየት አለበት።
  • ህወሓት ወጣቱ የዓለም ዋንጫ በሚመለከጥበት ሰሞን ተቃውሞው ይቀንሳል የሚል የተሳሳተ እሳቤ ይዟል።
  • ለእዚህ አይነቱ የህወሓት  ትዕቢት የኢትዮጵያ ሕዝብ የትዕግሥቱ ልክ እንዳበቃ ማሳየት ያለበት ጊዜ አሁን ነው።

ኢትዮጵያውያን አሁን ያለንበት የእስረኞች መፈታት፣ስለ ኢትዮጵያዊነታችን በነፃነት ለመናገር፣ኢትዮጵያውያንን የሚያከብር ጠቅላይ ሚኒስትር ለማግኘት መስዋዕትነት ከፍለውበታል።እናት እልጇ አስከሬን ላይ ተቀምጣ የግፍ ፅዋ ጠጥታበታለች፣ በአንድ ቀን ከሃምሳ ያላነሱ ወጣቶች በጥይት አረር በባህር ዳር እረግፈውበታል፣ ከአምስት መቶ በላይ ወጣቶች በቢሸፍቱ በአንድ ጀንበር ብቻ በእረቻ በዓል እረግፏል፣ ድምፃችንን ስሙን ብለው የደቡብ ሕዝብ ኢትዮጵያውያን ጥይት ተርከፍክፎባቸዋል። ይህ ለውጥ በዕቃ ዕቃ ጫወታ የመጣ ለውጥ አይደለም።ይህ ለውጥ ይቅርታ፣ፍቅር እና ሕብረትን እየዘመረ የመጣው ከሰባ ሚልዮን ብር በላይ ለፕሮጀክት ሥራ ብለው እነ  ዓባይ  ፀሐዬ በተራራ ፀሐይ እንደዘረፉት ሳያውቅ ቀርቶ አይደለም።ይህ ሕዝብ እህቶቹን በአደባባይ በጉዞ ወኪል ስም  የሸጡበት በእየኤምባሲው የተሰገሰጉ የህወሓት ባለስልጣናትን ሳያውቃቸው ቀርቶ አይደለም። ይህ ሕዝብ ኢትዮጵያን በቢልዮን የሚቆጠር ዶላር በስሟ ተበድረው በውጭ ሀገር ባንኮች በልጆቻቸው ስም ያስቀመጡ የቡድን መሪ የህወሓት ሰዎች እንዳሉ ሳያውቅ ቀርቶ አይደለም።ህዝቡ ስጋውን ውጫ ለመብላት እንጂ አጥንቱን ለመብላት የተዘጋጁ ግን አልመሰለውም ነበር።

ዛሬ ግንቦት 6/2010 ዓም ህወሓት እኩይ ተግባሩን ተቃውመው የወጡትን የኢሕአዴግ ምክርቤት ውሳኔዎች የሚኮንን መግለጫ አውጥቶ ዳግም ልርገጣችሁ የሚል የተለመደ ዲስኩሩን በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ሲያሰማ አምሽቷል።የእስረኞች መፈታት፣የፍቅር መሰበክ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዓብይ እያደረጉ ያሉትን የለውጥ ነፋስ ምክንያት ስያጉረመርሙ የነበሩ ህወሓቶች ከአሁን በኃላ የኢትዮጵያን ሕዝብ  በምንም አይነት ለመረገጥ እንዳልተዘጋጀ ሊያውቁት ይገባል።በአሁኑ ሰዓት ህወሓት የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የምስራቅ አፍሪካ  ቀዳሚ የፀጥታ ስጋት ሆኗል።There is no an immediate danger, other than TPLF for the peace and stability of the horn of Africa. ስለሆነም ከኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ለውጥ ጎን የቆመው የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ይህንን የሰላም ስጋት የሆነ ህወሓት ካልተወገደ በምንም አይነት በኢትዮጵያ ሰላም እንደማይሰፍን ለመጨረሻ መጨረሻ ጊዜ ተረጋግጧል። ስለሆነም  
ለእዚህ አይነቱ የህወሓት  ትዕቢት የኢትዮጵያ ሕዝብ የትዕግሥቱ ልክ እንዳበቃ ማሳየት ያለበት ጊዜ አሁን ነው።የመጀመርያ እርምጃው መሆን ያለበት እርስ በርሱ ለማጋጨት ከሀገር ውስጥ እስከ ውጭ ሀገር የሚርመሰመሱትን የወያኔ ወኪሎች  በቀጥታ በማጋለጥ እና ለሕግ በማቅረብ አደብ ማስያዝ አለበት።የትግራይ ሕዝብ ህወሓት ይህንን ያህል ለበለጠ ወንጀል የሚዘጋጀው በቡድን ዝርፍያ ውስጥ ስለገባ በወንጀል ስለሚጠየቅ ትግራይ ሕዝብ ውስጥ ገብቶ ለመደበቅ እንደሆነ ማወቅ አለበት። ከቡድን ዘራፊ ጋር ለመቆም የሚፈልግ መብቱ ነው።ፅዋውንም ለመጠጣት አብሮ መዘጋጀት አለበት። 

በመጪው ቅዳሜ ይደረጋል የተባለው የመቀሌ ሰልፍን በራሱ የመቀሌ ነዋሪዎችም ደግመው ሊያስቡት የሚገባ ህወሓት በበርካታ የዝርፍያ እና የግድያ ወንጀል ውስጥ የገባ ቡድን ነው።በ21ኛው ክ/ዘመን የእንደዚህ አይነት ቡድንን ደግፎ በመሰለፍ የሚገኝ ትርፍ ሳይሆን አደገኛ ኪሳራ ነው።


የኢትዮጵያ ሕዝብ ሰኔ 9/2010 ዓም ቅዳሜ የመቀሌ ሰልፍ በተደረገ ማግስት ሰኔ 10/2010 ዓም ዕሁድ በአዲስ አበባ፣ሐዋሳ፣አዳማ፣ባህርዳር፣ጎንደር፣ደሴ፣ሐረር፣ነቀምት፣ወዘተ ዲሞክራሲ ወይንም ሞት! የሚል አስገራሚ ሰልፍ በማድረግ ለሕወሐትም ሆነ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ከዶ/ር ዓብይ የለውጥ ሂደት ጋር አብሮ መቆሙን ማሳየት አለበት።በተመሳሳይ መልኩ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በመጪው ሳምንት ህወሓትን የሚያስጠነቅቅ ዓለም አቀፍ ሰልፍ ማዘጋጀት አለባቸው።ዓለሙ ከኢትዮጵያ ጋር ነው።ህወሓት በትክክል እኩይ ስራው የበለጠ ይጋለጣል። አሁንም ዲሞክራሲ ወይንም ሞት! ሞት ለዲሞክራሲ ፀሮች እና ዘረኞች! መሪ መፈክራችን ነው።



ያመናል በለው።

  
ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Tuesday, June 12, 2018

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዓብይ ቋንቋን መሰረት ያደረገ ፌድራሊዝም አደጋ ዙርያ የሚያወያይ እና ምክር ቤቱ ውሳኔ እንዲያሳልፍ የሚረዳ ሀገራዊ ጉባኤ የመጥርያ ጊዜያቸው አሁን ነው።(የጉዳያችን ማሳሰብያ)

ጉዳያችን /Gudayachn
ሰኔ 5/2010 ዓም (ጁን 12/2018 ዓም)
በእዚህ ፅሁፍ ስር : - 
     1ኛ)/ር ጃን ኤርክ ከሊደን ዩንቨርስቲ በፈድራሊዝም እና ያላማከለ አስተዳደር ከኢትዮጵያ በሚል      
           የሰጡት ማብራርያ ቪድዮ እና 

    2ኛ) የሐረርወርቅ ጋሻው ለአውስትራሊያው ሲቢኤስ ራድዮ የጎሳ ፈድራልዝምን አስመልክተው    
          የተናገሩት ቪድዮ ያገኛሉ።

በኢትዮጵያ ቋንቋን መሰረት ያደረገ ፌድራሊዝም ላለፉት ሃያ ሰባት ዓመታት ኢትዮጵያ ልትደርስበት ከሚገባት የእድገት ደረጃ በምን ያህል ወደ ኃላ እንዳስቀራት ቢጠና በሩብ ክፍለዘመን ውስጥ መድረስ ከሚገባን የዕድገት ደረጃ በእጅጉ እንደተጎተትን ለመረዳት ይቻል ነበር። ቋንቋን መሰረት ያደረገ ፌድራሊዝም በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ሕዝብ ከቀዬው አሰድዷል፣ሺዎች ተገድለዋል፣ቤተሰብ ተበትኗል። ፈድራሊዝም በራሱ የእድገት ፀር አይደለም።ፈድራሊዝም ሕዝብ የእራሱን ባህል፣ማኅበራዊ፣ፖለቲካዊ እና ምጣኔ ሀብታዊ ግንኙነቱን የሚያዳብርበት እና እንዲሁም በፌድራል መንግስት ውስጥ ያለውን ኃላፊነት የሚወጣበት መንገድ ነው።ፈድራሊዝም ጎሳ እና ቋንቋን መሰረት ካላደረገ ምንን መሰረት ማድረግ አለበት? የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችላል። 


ፈድራሊዝም መሰረት ማድረግ የሚገባው እና አሁን ባለንበት ዓለም ሁሉ የሚጠቀምበት  ታሪክን÷ባህልን እና መልክአምድራዊ አቀማመጥን ባማከለ መልኩ ነው።አሁን ወቅቱ የፌድራል አስተዳደር መሰረታዊ ችግሩን መፈተሽ፣መወያየት እና አስፈላጊ እስከሆነ ድረስ ደግሞ ህገመንግስቱ ላይም መቀየር ያለበትን እስከመቀየር መድረስ የማይቻልበት ምክንያት የለም።ይህንን ጉዳይ ለመጪ መንግስት ተብሎ የሚተው አይደለም::

ዶ/ር ጃን ኤርክ በኢትዮጵያ የጎሳ ፈድራሊዝም ታስቦበት እና ተጠንቶ የመጣ ሳይሆን በ1983 ዓም ድንገት ሽምቅ ተዋጊዎች ሲያሸንፉ የመሰረቱት መሆኑን ያብራራል።አዎን! በኢትዮጵያ ፈድራሊዝም ከሀገሪቱ ታሪክ፣ባህል፣ምጣኔ ሃብታዊ ትስስር እና መልካምድራዊ አቀማመጥ ላይ ባለሙያዎች ሳያጠኑት ሕዝብ ሳይመክርበት በድንገት የተጫነ ድንገቴ ነው። ዶ/ር ጃን የኢትዮጵያ የጎሳ ፖለቲካ ሕግን መሰረት ከማድረግ ይልቅ ከሚገባው በላይ ፖለቲካዊ ስለሆነ ድህጣን ጎሳዎች መብታቸው ሊከበር እንደማይችል ያብራራል።


የሐረርወርቅ ጋሻው፣በሌላ በኩል አሁን ያለው የጎሳ ፖለቲካ ፌዴራሊዝም የኢትዮጵያን ሕዝብ ለመለያየት የመጣ አደጋ ነው።ለኢትዮጵያ ማዕከላዊ መንግስት እንጂ የጎሳ ፖለቲካ ፌድራሊዝም አያስፈልጋትም ትላለች።በእዚህ ፅሁፍ ላይ ፈድራልዝም ወይንም ማዕከላዊነት ለኢትዮጵያ ይበጃል አይበጅም ለማለት ሕዝብ መምከር፣መንግስት የመመካከርያ መንገዱን ማመቻቸት እና ህገ መንግስቱን እስከመቀየርም ድረስ የሚደርስ ውሳኔ ሕዝብ እንዲወስን ማድረግ ኢትዮጵያ ወደፊት የማደግ እና አለማደግ ሁኔታ ላይ ወሳኝ ሚና አለው። ውይይቱ ግን በፍጥነት መጀመር አለበት።ብሔራዊ ጉባኤ መጠራት አለበት።ይህ ለመጪ መንግስት ተብሎ የሚቀመጥ ጉዳይ ሊሆን አይገባውም።ሕዝብ እያለቀ ነው።የበለጠ ጥፋት ደግሞ ሊከሰት ይችላል።


ከእዚህ በታች ዶ/ር ጃን ኤርክ ከሊደን ዩንቨርስቲ በፈድራሊዝም እና ያላማከለ አስተዳደር ከኢትዮጵያ አንፃር ያቀረቡትን እና ወ/ሮ የሐረርወርቅ ጋሻው ለአውስትራሊያው ሲቢኤስ ራድዮ ከጎሳ ፖለቲካ ይልቅ ማዕከላዊ አስተዳደር ይሻለናል በማለት ያቀረቡት ሃሳብ ቪድዮ በተከታታይ ከስር ያዳምጡ።ሁለቱም ቪድዮዎች እያንዳንዳቸው ከአስር ደቂቃዎች የበለጡ አይደሉም።



ዶ/ር ጃን ኤርክ ከሊደን ዩንቨርስቲ በፈድራሊዝም እና ያላማከለ አስተዳደር ከኢትዮጵያ አንፃር
Video Source ; -Centre for Innovation - Leiden University You Tube

የሐረርወርቅ ጋሻው ለአውስትራሊያው ሲቢኤስ ራድዮ የጎሳ ፈድራልዝምን አስመልክተው የተናገሩት 



ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

Monday, June 11, 2018

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ የተሰኘ አዲስ ንቅናቄ ባህርዳር ላይ ተመስርቷል።የንቅናቄው እድሎች እና ፈተናዎች ምንድናቸው?


የንቅናቄው ምስረታ ላይ የተገኘው ሕዝብ 

ጉዳያችን/ Gudayachn 
ሰኔ 3/2010 ዓም (ጁን 10/2018 ዓም)

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ መስራች ጉባኤውን ለሁለት ቀናት ያህል ሰኔ 2 እና 3/2010 ዓም በባህር ዳር ከተማ  አካሂዷል።በጉባኤው ላይ ንግግር ያደረጉት ጀነራር ተፈራ ማሞን ጨምሮ በርካታ ወጣቶች የተገኙ ሲሆን የንቅናቄውን አመራሮችም ይፋ ሆነዋል።በእዚህም መሰረት አመራሮቹ የሚከተሉት መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል። እነርሱም : -
1-ዶር ደሳለኝ ጫኔ-ሊቀመንበር
2-አቶ በለጠ ሞላ-ምክትል ሊቀመንበር
3-አቶ ጋሻው መርሻ-የድርጅት ጉዳይ 
4-አቶ መልካሙ ሹምየ-የፖለቲካ ጉዳይ ሀላፊ
5-አቶ ተመስገን ተሰማ-የማኅበራዊ ጉዳይ ሀላፊ
6-አቶ ዳምጠው ተሰማ -የውጭ ጉዳይ ሀላፊ
7-አቶ ካሱ ኃይሉ -የኢኮኖሚ ጉዳይ ሀላፊ
8-አቶ ክርሥቲያን ታደለ-የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ
9-ወ/ሪት መሰረት አስማማው-ሴቶች ጉዳይ ሀላፊ
10-አቶ የሱፍ ኢብራሄም-የጥናትና ስትራቴጂ ጉዳይ ሀላፊ
11-አቶ ጥበበ ሰይፈ-የህግ ጉዳይ ሀላፊ
12-አቶ ተሰማ ካሳሁን-የወጣቶች ጉዳይ ሀላፊ
13-አቶ ዳንኤል አበባው -የፋይናንስ ጉዳይ ሀላፊ
14-አቶ በለጠ ካሳ-የፓርቲ ፅ/ቤት ሀላፊ

የጉባኤው መርህ '' ሁሉም አማራ ለአንድ አማራ፣አንድ አማራ ለሁሉም አማራ'' የሚል መሆኑ በመርሐግብሩ መክፈቻ ላይ ተነግሯል።በመክፈቻው ላይ ንግግር ያደረጉት ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ በንግግራቸው ላይ  እስካሁን አማራው ያልተደራጀበት ምክንያት ውስጥ ችግሩ ይሻሻላል ከሚል ተስፋ እና በብሔር መደራጀት ለሀገር አንድነት አደጋ አለው ከሚል መሆኑን ጠቅሰው ሆኖም ግን ሁሉ ነገር ከልክ በማለፉ ለመደራጀት መወሰኑን አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። ዶ/ር ደሳለኝ ንግግራቸውን በመቀጠል  በቀጣይ የስራ ዕቅዳቸው ውስጥ የሚከተሉት ተግባራት እንዲከናወኑ እንደሚሰሩ አብራርተዋል።እነርሱም: -
  • አማራውን የሚጎዳ አከላለሎች እንዲስተካከል መስራት፣ 
  • በሕገ መንግስቱ ውስጥ የአማራ ሕዝብ የሚጎዱ አንቀፆች እንዲከለሱ መታገል፣ 
  • በሌላ ክልል የሚኖረው የአማራ ተወላጅ መብት እንዲከበር ማድረግ፣ 
  • ከወንድም የኦሮሞ እና ሌሎች ብሔሮች ጋር በህበረት መስራት፣
  • ብአዴን በትክክል እንዲሰራ መታገል እና በውስጡ ያሉት የንቅናቄው ደጋፊ እንዲሆኑ ማድረግ፣
  • በተለያዩ ቦታዎች ለታሰሩት እና ንብረታቸው ለተነጠቁ ሁሉ ካሳ እንዲሰጥ መታገል እና 
  • በኢትዮጵያ የሚኖሩ ማናቸው የፖለቲካ ሂደት  አማራው የሚሳተፍበት መንገድ ማመቻቸት እና ከሌላው ዜጋ እኩል ለስልጣን ማብቃት የሚሉት በንግግራቸው ውስጥ ከጠቀሷቸው ውስጥ ናቸው።

የንቅናቄው እድሎች እና ፈተናዎች

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ በተለይ በአሁኗ ኢትዮጵያ ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ አንፃር መመስረቱን ይዞ ለንቅናቄውም ሆነ ለኢትዮጵያ ፖለቲካ የሚያመጣው ዕድል እና ፈተናዎች አሉት።ከሁሉ በፊት ግን ንቅናቄው የተመሰረተበት ምክንያትን ከዳር ሆኖ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ለሚመለከት ተመልካች ሶስት ምክንያቶች ለመመስረቱ ማስቀመጥ ይችላል።የመጀመርያው ምክንያት የህወሓት ፅንፈኛ እና ዘረኝነት ላይ የተመሰረተ ፖለቲካ በአማራው ላይ ላለፉት ሃያ ሰባት አመታት የተሰራው የጭቆና ተግባር አንዱ ሲሆን፣በሁለተኛ ደረጃ ብአዴን-ኢህአዴግ ላለፉት ሃያ ሰባት ዓመታት በአማራው ስም እየነገደ የሰራው ሸፍጥ እና ሶስተኛው ምክንያት ከደቡብ እስከ ምስራቅ፣ከምዕራብ እስከ መሃል ኢትዮጵያ የሚኖሩ ዜጎች አማራ እየተባሉ መፈናቀላቸው እና ለሚፈናቀሉትም በቂ እርዳታ የሚያደርግም ሆነ በአፈናቃዮቹም ላይ ምንም አይነት እርምጃ አለመወሰዱ የእዚህ አይነት ንቅናቄ እንዲመሰረት ምክንያት እንደሆነ ለማወቅ ይቻላል።
ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ የንቅናቄው ሊቀመንበር 

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ሕይወት ውስጥ የሚናቅ ጉልበት ይኖረዋል ብሎ መገመት አይቻልም።ለእዚህም ሁለት ምክንያቶች አሉ።እነርሱም ህወሓት የትግራይ ብሔርተኝነትን እያስኬደበት ያለው ጉልበት ላይ የተመሰረተ ግንኙነት ብዙዎችን ወደ መረረ ትግል ስሜት ውስጥ ማስገባቱ አንዱ ሲሆን በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ በሌሎች ክልሎች የሚኖሩ አማራ እየተባሉ ለአመታት ከኖሩበት ቦታ እየተፈናቀሉ ሲሰደዱ እና ለልመና ሲዳረጉ ተገቢው ወቅታዊ ምላሽ አለመሰጠቱ ነው።በተለይ በማፈናቀሉ ሂደት ውስጥ ከኦሮምኛ በስተቀር  አማርኛ ፈፅመው የማይችሉ በቷልዳችሁ አማራ ናችሁ ተብለው የተሰደዱ በርካቶች አሁንም በመጠለያ ቦታ ወይንም በከተሞች ውስጥ እየተንከራተቱ ይገኛሉ።እነኝህ ሁለት ሁኔታዎች የአማራ ብሔርተኝነትን እያፋፋሙት ይምጡ እንጂ ትልቁ እና ዋናው ጉዳይ ግን ህወሓት ሰራሹ የጎሳ ፈድራሊዝም አደረጃጀት እና ህገ መንግስቱ የአማራውን ሕዝብ በሚያጠቃው መልኩ የተሰሩ ናቸው የሚለው መሪ ሃሳብ ነው።በሽግግር መንግስቱ ወቅትም ሆነ ህገ መንግስቱ ሲፀድቅ ሌላው ተወክሎ አማራው ግን አልተወከለም የሚለው አባባል አሁንም ድረስ ጎልቶ እየተነገረ ነው።የህወሓት ውጤት ብአዴን ስሙን የቀየረው ቆይቶ መሆኑ ይታወቃል።ስለሆነም ጉዳዩ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ መፍትሄ ከሚሹት ጉዳዮች ውስጥ አንዱ የአማራው ጉዳይ መሆኑን መካድ አይቻልም።እዚህ ላይ የአማራ ጉዳይ ሆኖ እንዲወጣ ያደረገው ህወሓት እራሱ የአማራ ጉዳይ የሚል አጀንዳ በማነፈስቶውም ሆነ በተግባሩ ግፍ በመስራት ጉዳዩ እራሱን ወደ አጀንዳነት እንዲቀየር ስላስገደደ ነው።

ይህ ንቅናቄ መልካም እድሎች አሉት።ከእነኝህ እድሎች ውስጥ የሚከተሉትን መጥቀስ ይቻላል። እነርሱም:  -
  • ብአዴን ውስጥ ያሉ በደሉን ለሚረዱ ወገኖች አዲስ ጉልበት ይዘው የመውጣት ዕድል አላቸው፣
  • የፈድራል አደረጃጀቱን ለማዋቀር ተፅኖ የመፍጠር አቅም አለው፣
  • በእየቦታው አማራ በሚል ስም ለሚፈናቀሉ ኢትዮጵያውያን አፋጣኝ የሕግም ሆነ የማቴርያል ድጋፍ እንዲደርስ የማስተባበር አቅም ይኖረዋል፣
  • በፌድራል ደረጃ የሚደርሱ በደሎችን በጥናት በማስደገፍ ለፌድራል መንግስት በማሳሰብ እንዲስተካከል ተፅኖ ለመፍጠር ይችላል፣
  • የክልሉ ተወላጆች በውጭም ሆነ በውስጥ ያሉ ገንዘባቸውን፣እውቀታቸውን እና ጊዜያቸውን በመሰዋት ለሀገር እድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ የማድረግ ዕድል ይኖራል።

የሚሉት ለንቅናቄው የወደፊት እድሎች ውስጥ የሚጠቀሱ ናቸው።ከእዚህ በተለየ ግን ንቅናቄው ከእድሎች በተለየ ፈተናዎችም ይኖሩበታል።

የንቅናቄው ፈተናዎች

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ከሚኖሩበት ፈተናዎች ውስጥ ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ተጠቃሾች ናቸው። እነርሱም -
  • የከረረ ብሔርተኝነት ያላቸው ወደ አመራሩ ከመጡ ከኢትዮጵያዊነት ጋር አጣጥሞ ለመሄድ የመቸገር ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል፣
  • በህወሓት ሰርገው እንዲገቡ የሚደረጉ ግለሰቦች የሚፈጥሩት አሉታዊ ስዕል በንቅናቄው ላይ የሚሰጠው መልካም ያልሆነ ስዕል እና ከሌሎች ብሔሮች ጋር ለማጋጨት የሚደረጉ ሙከራዎች፣
  • እራሱን በቶሎ ወደ ኢትዮጵያዊ ንቅናቄ ካልቀየረ በከረረ ብሔርተኝነት ስሜት የተመሰጡ አባላቱን ወደ ሃገራዊ አጀንዳ ባለቤትነት ለመቀየር የመቸገር ሁኔታ መፈጠር።የእዚህ አይነቱ ችግር አሁን ህወሓት እራሱ ገጥሞት የሚገኘው ችግር ነው።መግብያ ሲዘጋጅ መውጫው አብሮ መታየት አለበት።
  • በተሰሩ ግፎች እና ጥፋቶች ላይ ከሚገባው በላይ በመዘከር የይቅርታ እና የአንድነት መንገዶች እንዲከፈቱ ማድረግ ካልቻለ አማራን ብቻ ሳይሆን በብሔራዊ ደረጃ ወደ አደገኛ መንገድ የመሄድ አዝማምያ እንዳይኖር ጥንቃቄ ያስፈልጋል።

ባጠቃላይ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ብአደንን ልገዳደር ወይንም ሊጠቀልል ባህርዳር ላይ ተመስርቷል።በሂደቱ የብአዴን አመራርም ሆነ ለውጥ ፈላጊው ክፍል ይህንን ንቅናቄ እንደስጋት እንደማያየው መገመት ይቻላል።ብአዴን ብዙ ጊዜ በውስጡ ባሉ ስውር እጆች በህወሓት ፍላጎት ሲነዱ ተመልክቷል።ስለሆነም ንቅናቄው ከብአዴን በኩል የጎላ ተግዳሮት ሊገጥመው ይችላል ብሎ ቢያንስ ለጊዜው ይኖራል ተብሎ አይገመትም።በሌላ በኩል ንቅናቄ እንጂ ፓርቲ ስላልሆነ የሚያቅፈው መልከአ ምድራዊም ሆነ የህዝብ ብዛት ቀላል የሚባል ስላልሆነ በኢትዮጵያ ፖለቲካዊም ሆነ ምጣኔ ሃብታዊ ሂደት ላይ የእራሱ አሻራ ይዞ ሊመጣ ይችላል።ከእዚህ ሁሉ ጋር ግን መጪው የኢትዮጵያ ፖለቲካ በሕበረ ብሔር ፖለቲካ ፓርቲዎች ወይንስ በብሔር የፖለቲካ ፓርቲዎች ይመራል? ወይንስ ሁለቱም በእየፊናቸው ተደራጅተው ለውድድር ይቀርባሉ? እዚህ ላይ ግን ኦፌኮን ኦህዴድን፣አብን ደግሞ ብአደንን ለመገዳደር ከቆሙ ሌላ የፖለቲካ መሰነጣጠቅ እንዳይፈጠር ያሰጋል።ከእዚህ ያልቅ ግን ድርጅቶች ውሕደት ፈጥረው የሁሉም መብት የሚከበርባት ኢትዮጵያን እንዲያሳዩን የምድሪቱ ፍጥረታት በሙሉ የምንመኘው ቀዳሚ ምኞታችን ነው።


ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Friday, June 8, 2018

ሀያ አራት ዓመታት በእስር የሚገኙት ሊቁ መምህር እንደሥራቸው አግማሴ እንዲፈቱ ከቤተሰቦቻቸው የተላለፈ የተማጽኖ ጥሪ ቪድዮ



የኢሳት ሰኔ 1/2010 ዓም ዘገባ በመምህር እንደስራቸው አግማሴ ጉዳይ 

ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com

Wednesday, June 6, 2018

ለኢትዮጵያውያን በሙሉ! የማኅበራዊ ሚድያ ጥሪ በመምህር እንደስራቸው አጉማሴ እስር ጉዳይ

በያዝነው ሳምንት መጀመርያ ጀምሮ ለሃያ አራት ዓመታት በእስር እየተሰቃዩ ለሚገኙት አባት መምህር እንደስራቸው አግማሴ ከእስር እንዲፈቱ እና ወደ ቤተሰባቸው እንዲቀላቀሉ የማኅበራዊ ሚድያ ጥሪ ለማዘጋጀት እና በሀገር ቤት እና በመላው ዓለም ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጥሪ ቀርቧል።ሙሉ መልእክቱን ይመልከቱት።

ለኢትዮጵያውያን በሙሉ!
============
የማኅበራዊ ሚድያ ጥሪ በመምህር እንደስራቸው አግማሴ እስር ጉዳይ ይመለከታል  
===================================================================
ይህ የሰብዓዊነት ጉዳይ ነው።ይህ የሰባት ልጆች አባት ሆኖ 24 ዓመታት ያህል በእስር ቤት የቆየ አባት ጉዳይ እንዲሁም የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ካላት የተክሌ ዝማሜ መምህር እና ሊቅ የ24 ዓመታት በእስር ቤት ተዘግቶባቸው ዝም እንዲሉ የተደረጉበት ጉዳይ ነው። መምህር እንደሥራቸው አጉማሴ ለ24 ዓመታት ከተዘጋባቸው እስር ቤት ተለቀው ከቤተሰባቸው ጋር እንዲቀላቀሉ ድምጽዎን ያሰሙ።

ቅዳሜ ሰኔ 2/2010 ዓ.ም (June 9 /2018) በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 12 ሰዓት እስከ 2 ሰዓት እኝህ የሀገር ሀብት ዕንቊ አባት ከእስር እንዲፈቱ በትዊተር እና ፌስቡክ ዓለም አቀፍ ጥሪ ይቀርባል። ተሳታፊ ይሁኑ።

የጥሪው ዋና ዓላማ 
============
የዚህ የማኅበራዊ ሚድያ ጥሪ ዋና ዓላማ መንግሥት፣ ሕዝብ እና ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ በመምህር እንደሥራቸው ላይ የተፈፀመውን ግፍ እንዲረዳ ማድረግ እና ትኩረት መሳብና በመጨረሻም መምህሩ እንዲፈቱ ግፊት ማድረግ ነው።
እርስዎ በበጎ ኅሊና በጥሪው ላይ ለመሳተፍ ይዘጋጁ እንጂ መንገዶቹን እንጠቁምዎታለን። በጥሪው ላይ የሚሳተፉባቸው መንገዶች የሚከተሉትን ይጨምራል።

ሀ) ከቅዳሜ በፊት 

1ኛ/ እስከ ቅዳሜ ባሉት ቀኖች ውስጥ 

** ቅዳሜ በተባለው ሰዓት ጥሪው እንደሚደረግ ፖስተሩን በመለጠፍ፣ የማኅበራዊ ሚድያውን ማንቃት፣ ** በፌስ ቡክ፣ በትዊተር የሚሰራጩ ፖስተሮችን፣ ቃላትን እና ዐረፍተ ነገሮችን ከአሁኑ ማዘጋጀት እና ፈጠራን መጨመር፣ 

** የሚዘጋጁት ፅሁፎች እና ፖስተሮች በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ሊዘጋጁ ይችላሉ።
2ኛ) ቅዳሜ ጥሪ እንደሚደረግ የሚገልጥ መልዕክት  ለምናውቀው ሰው በኢሜል፣ በውስጥ መስመር፣ በቫይበር/ዋትስአፕ/ቴሌግራም እና በግላችን ገጾች ላይ በመለጠፍ ከቅዳሜ በፊት ባሉት ቀናት ማስታወቂያውን ማሰራጨት ፣

ለ) በዕለተ ቅዳሜ 
    =========
1ኛ) ቅዳሜ 
** በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 2 ሰዓት ድረስ ካለምንም እረፍት በተከታታይ የ“ይፈቱልን” ማስታወቂያውን መልቀቅ።
** መልዕክቶቹ ቀደም ብለው ያዘጋጇቸው ወይንም ሌሎች የለቀቁትን "ሼር" በማድረግ በፌስ ቡክ እና ትዊተር ገጽዎ ላይ መለጠፍ ነው።
ማሳሰቢያ መምህር እንደስራቸውን ማንነት ለማወቅ ይህንን ተጭነው ያንብቡ ።
የመምህር እንደስራቸው የመንፈስ እና የስጋ ልጆች የአባታቸውን መፈታት እየጠበቁ ነው።
አንተ አቡነ (ያሬዳዊ ዜማ ቪድዮ)

ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Tuesday, June 5, 2018

የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ያሳለፈውን ውሳኔ በተመለከተ የጉዳያችን ማስታወሻ

የኢህአዴግ ማዕከላዊ ኮሚቴ 
በእዚህ ፅሁፍ ስር የሚከተሉትን ነጥቦች ያገኛሉ 

  •   የመንግስት ድርጅቶችን ወደ ግል ባለ ሀብትነት የማዞሩ ሂደት በተመለከተ፣
  • የመንግስት ድርጅቶች ወደ ግል በከፊል እና በሙሉ የማዞር ጉዳይ የሚያመጣው አዎንታዊ እና አሉታዊ ተፅኖዎች፣
  • የዛሬው የኢህአዴግ ውሳኔ በርካታ ጥያቂዎች ይዟል፣
  • የውጭ ባለ ሀብት ሁሉ ጠላት ነው የሚል የተሳሳተ አስተሳሰብ፣
  • የባድሜ ጉዳይ እና የኢትዮ- ኤርትራ ግንኙነት፣
  • በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል እአአ ታህሳስ 12/2000 ዓም የተደረገው ስምምነት አንቀፆች (Agreement Between Eritrea and Ethiopia signed in Algiers, 12 Dec. 2000)


ጉዳያችን/Gudayachn
ግንቦት 29/2010 ዓም (ጁን 6/2018 ዓም)

የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ግንቦት 28/2010 ዓም በጠራው ስብሰባ ላይ በሁለት ወሳኝ ፖለቲካዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳልፏል።ውሳኔዎቹ ሁለት ሲሆኑ የመጀመርያው ከእዚህ በፊት ሙሉ በሙሉ በመንግስት እጅ የነበሩ ዋና ዋና ድርጅቶች ማለትም የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣መብራት ኃይል እና ቴሌን ጨምሮ በብዛኛው በመንግስት ይዞታ ስር ሆነው ቀሪው ድርሻ ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ባለሀብቶች በአክስዮንነት እና ሌሎች ደግሞ ሙሉ በሙሉ እንዲሰጡ የሚል እና ሁለተኛው ከኤርትራ ጋር የነበረው ግንኙነት ለማሻሻል የአልጀርሱን ስምምነት ሙሉ በሙሉ ተቀብሎ ወደ ተግባር መቀየር የሚሉ ውሳኔዎች ናቸው።የአልጀርሱን ውሳኔ በተመለከተ የባድመን ለኤርትራ መሰጠት ያጠቃልላል።

የመንግስት ድርጅቶችን ወደ ግል ባለ ሀብትነት የማዞሩ ሂደት በተመለከተ

የመንግስት ድርጅቶችን ወደ ግል (የግል የሚለው እራሱ ብዙ መብራራት ይፈልጋል) የማዞር ጉዳይ በሁለት አካላት ሲቀነቀን ዓመታት አሳልፏል።የመጀመርያው ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት እና የምዕራቡ ዓለም ሲሆን በሌላ በኩል በሀገር በቀሉ ባለሀብቶች ነው።የምዕራቡ ዓለም ኢትዮጵያ ላለፉት አርባ ዓመታት በመንግሥትነት የተያዙ ትልልቅ ድርጅቶች በተለይ የስልክ፣አየርመንገድ እና መብራት መያዛቸው ለሌላ የአፍሪካ ሀገሮች ምሳሌ እንዳይሆን ትልቅ ስጋት አለባቸው።ለምሳሌ የባንክ ሴክተሩን ብንመለከት የውጭ ሀገር ባንክ ፈፅሞ ያልገባባት ሀገር ኢትዮጵያ ነች።ይህ ደግሞ በእራሱ ይዞ የሚመጣው በጎ እና በጎ ያልሆኑ እድሎች አሉ።የአፍሪካ የአሁኑ ምጣኔ ሀብት ባብዛኛው የተያያዘው ከቀድሞ ቅኝ ገዢዎቻቸው ጋር የተጣመረ ነው።ይህም በመሆኑ ፖለቲካውም በእነኝህ አካላት በቀላሉ እንዲዘወር አድርጎታል።ይህ ሁኔታም ለብዙ የአፍሪካ ሀገሮች የምጣኔ ሀብት እና የፖለቲካ ፖሊሲያቸውን በሚፈልጉት መልክ እንዳይቀርፁ እንቅፋት ሆኖባቸዋል።

የመንግስት ድርጅቶች ወደ ግል በከፊል እና በሙሉ የማዞር ጉዳይ የሚያመጣው አዎንታዊ እና አሉታዊ ተፅኖዎች 

ቁልፍ የምጣኔ ሀብት አውታሮች ለምሳሌ የመብራት፣አየር መንገድ፣ባህር ትራንዚት፣ቴሌ የመሳሰሉት ድርጅቶች በመንግስት ቁጥጥር ስር በዋናነት መያዛቸው አስፈላጊ የሚሆንበት ምክንያት እነኝህ አውታሮች ለሁሉም ባለ ሀብት እና ለሕዝብ እኩል ካለምንም አድልዎ ማዳረስን የመንግስት ያህል የለም ከሚል እሳቤ ነው። ይህ ማለት በፖሊሲ ደረጃ ለምሳሌ ቴሌ አገልግሎቱን የሚሰጠው ትርፍ በሚያገኝበት በአዲስ አበባ ብቻ ሳይሆን ትርፍ በማያገኝበት እንደ ማጂ ዞን ያሉ የጠረፍ ቦታዎች ሁሉ ከአዲስ አበባ የሚያገኘውን ትርፍ በማካፈል አገልግሎቱን ያዳርሳል።ሆኖም ግን ሙሉ በሙሉ በግል ድርጅቶች እጅ ከወደቀ ግን ትርፍ የሚገኝበት ቦታ ላይ ብቻ እንጂ ገጠራማ ቦታዎች አገልግሎቱን ለማግኘት አይችሉም።የብዙ የአፍሪካ ሀገሮች ያልተመጣጠነ የአካባቢ እድገት የሚያጋጥመው አንዱ የግል ዘርፉ በቁልፍ የምጣኔ ሀብቶች ላይ የወሳኝ ሚና ሲኖረው እና ትርፍ ብቻ ያለመ ፖሊሲ ምስኪኑን ያገለለ ይሆናል። ይህ ብቻ አይደለም የግል ባለሀብቱ የውጭ ባለ ሀብት ከሆነ የመጣበት ሃገርን ፖለቲካዊ ተፅኖ አስፈፃሚ የመሆኑ አጋጣሚ ቀላል አይደለም።ለእዚህም ነው በርካታ የዓለም አቀፍ የንግድ ድርጅቶች በታዳጊ ሀገሮች ውስጥ ገብተው የሚያደርጉት የፖለቲካ ጣልቃ ገብነት ለመንግሥታት መቀያየር ምክንያት የሚሆኑበት ሁኔታ ቀላል አይደለም።

ከላይ ከተጠቀሰው የግል ባለ ሃብቱ አሉታዊ ገፅታ በተለይ በሌሎች አፍሪካ ሀገሮች በምሳሌነት ናይጀርያ እና ኮንጎን መጥቀስ ይቻላል፣በኢትዮጵያ እንዳይደገም የግሉን ዘርፍ በተለየ አቀራረብ ማሳተፍ ይቻላል።የናይጀርያ እና የዛየር ሀብት ለድሃው ለምን አልደረሰም? ለምንድነው የተረጋጋ መንግስት እንዳይኖራቸው የሆነው? የውጭ ባንኮች እና ባለመዋለ ንዋይ አፍሳሾች በመንግሥታት አለመረጋጋት ዙርያ ሚናቸው ምንድነው? የሚሉት ሁሉ በሚገባ ቢፈተሹ በርካታ ጉዳጉድ የያዘ ታሪክ አፍሪካ ተሸክማለች።

በሌላ በኩል ግን የግል ባለ ሃብቱ በቁልፍ የምጣኔ ሀብት ድርጅቶች ላይ መሳተፍ ይዞ የሚመጣው ሶስት መልካም ነገሮች አሉ።እነርሱም የቴክኖሎጂ ሽግግር፣የሰለጠነ የሰው ኃይል ማፍራት እና የመዋለ ንዋይ መሳብ ነው። እነኝህ መልካም ዕድሎች ግን ዕድል ሊሆኑ የሚችሉት ከሙስና የፀዳ፣የሀገሩን ርዕይ የሚያስቀድም እና ትክክለኛ ፖሊሲ የቀረፀ መንግስት ወደ ስልጣን ላይ ሲመጣ ብቻ ነው።እዚህ ላይ ሲንጋፖር፣ቦትስዋና እና ደቡብ ኮርያን በምሳሌነት መመልከት ይቻላል።እነኝህ ሀገሮች የግል ባለ ሃብትን ከምዕራቡ ዓለም ቢስቡም ትክክለኛ የቀረጥ ገቢ ለመንግሥታቸው በማስገባት እና የገባውን ገንዘብ ከሙስና በፀዳ መልክ በትክክል ለሕዝብ ልማት በማዋል የግል ባለሀብቱን ሚና ተጠቅመውበታል።በተቃራኒው ዋልጌ እና በሙስና የተነከሩ መንግሥታት ያላቸው እንደ ናይጄርያ እና ኮንጎ ያሉ መንግሥታት ከውጭ ባለሀብቶች ጋር የማይገባ ግንኙነት እያደረጉ ሀገራቸውን ለበለጠ ድህነት እየዳረጉ ይገኛሉ።

የዛሬው የኢህአዴግ ውሳኔ በርካታ ጥያቂዎች ይዟል

ከላይ ከተጠቀሰው  የግል ዘርፍ እና የመንግስት ግንኙነት አንፃር የዛሬው የኢህአዴግ ውሳኔ በብዙ ጥያቄዎች የታጀበ ነው።ከጥያቀዎቹ ውስጥ
- የእዚህ አይነቱ አቅጣጫ ቀያሪ ውሳኔ ሲደረግ ሕዝብ ቀድሞ እንዲወያይበት ለአደባባይ ማቅረብ አይገባም ነበር ወይ?
- በጉዳዩ ዙርያ የባለሙያ ጥናት በተለይ ከትርፍ እና ኪሳራ አንፃር ብቻ ሳይሆን ከኢትዮጵያ ታሪካዊ እና ባህላዊ እሴት አንፃር መታየት ያሉባቸው ጉዳዮች ታይተዋል ወይ?
- የእዚህ አይነት ውሳኔ ከሁለት ዓመት በኃላ በሚኖር ምርጫ ፓርቲዎች የሚያቀርቡት የውድድር አጀንዳ መሆን አይገባውም ነበር?
- እንደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ ያሉ የሀገር ምልክት የሆኑ ድርጅቶችን በቀላሉ በውጭ ሀገር ባለሀብቶች እጅ ማስገባት የሚያመጣው ጉዳት ተጠንቷል?
- የመገናኛ ብዙሃን በታፈኑበት ሀገር የውጭ ባለ ሀብት ምን ያህል የሀገር ሕግ አክብሮ እየሰራ እንደሆነ እና እንዳልሆነ ለሕዝብ የሚነግር በሌለበት ሀገር የውጭ ባለ ሀብቶች ከባለስልጣናት ጋር የሚሰሩትን ህገ ወጥ ተግባር ለሕዝብ ማን ይነግረዋል?
- የፓርላማ አባላት እና ፓርላማው እራሱ የሀገሪቱን ፖለቲካዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ እንቅስቃሴዎች የመረዳት፣የመተንተን እና ተከራክረው ሕግ የማስቀየር አቅም አላቸው ወይ?
- ከሀገር ውስጥ የሚመጣው ባለ ሀብት ምንጩ የተዘረፈ ገንዘብ ከሆነ በትክክለኛ መዋለ ንዋይነት ይታያል? የሚሉት እና በርካታ ጥያቄዎች ማንሳት ይቻላል።

የውጭ ባለ ሀብት ሁሉ ጠላት ነው የሚል የተሳሳተ አስተሳሰብ

የውጭ ባለ ሀብት በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ አውታር ላይ የሚገባበት በጎ እና በጎ ያልሆኑ ሁኔታዎችን በምናነሳበት ጊዜ ግን ያማንክደው የእኛ የኢትዮጵያውያን ማስተካከል የሚገባን የውጭ ባለ ሀብት ሁሉ ጠላት ነው የሚል የተሳሳተ አስተሳሰብ አለ።ኢትዮጵያ የምጣኔ ሀብቷን ለውጭው ዓለም በሚገባ እንዳልከፈተች በጣም ግልጥ ነው።እዚህ ላይ የሀገር ውስጥ ተወላጆች በሚገባ በሥራ ሳይሰማሩ የውጭ ባለ ሀብት ሊመጣ አይገባም ከሚለው እስከ አንድ የውጭ ሀገር ዜጋ ሱቅ ከፍቶ ስመለከት ሃገሩን ተቆጣጠሩት እስከሚለው አስተሳሰብ ብዙ መታረም ያለባቸው አስተሳሰቦች አሉን።ይህንኑ ሃሳብ ወደ ውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በምን ያህል ጥልቀት በንግድ ዘርፍ ተሰማርተው የሀገራቱን ሕጎች ተገን አድርገው እየኖሩ ነው ? ብለን ብንጠይቅ በርካቶች በእየሃገራቱ ውስጥ ተከብረው እና ታፍረው እንደሚኖሩ እንገነዘባለን።ይህ ሁኔታ ምናልባት እንደ ደቡብ አፍሪካ ባሉ ሀገሮች ችግሮች ቢገጥሙትም ባብዛኛው ለምሳሌ በኬንያ፣ዑጋንዳ፣ እና ሌሎች ሀገሮች በጥቃቅን ንግድ ዘርፎች ሳይቀር ተሰማርተው ይኖራሉ።በአሜሪካ እና አውሮፓም እንዲሁ በርካቶች በግል ዘርፉ ተሰማርተው ይኖራሉ።ይህንኑ ጉዳይ የውጭ ሀገር ዜጎች መርካቶ ውስጥ በምን ያህል ደረጃ አሉ? ብለን ብናስብ ግን አሁንም የሚሰማን ትክክል ያልሆነ ስሜት መኖሩን መካድ አይቻልም። ይህ ማለት የውጭ ባለ ሀብት ወደ ኢትዮጵያ ስንጋብዝ የእንግዳ ተቀባይ  የመሆናችንን ያህል  የሀገራችን ሕጎች በተቻለ መጠን የውጭ ሀገር ዜጋንም እንደሚመለከት ልክ የእኛ ዜጎች በውጭ ሀገር እንደሚገጥማቸው ተግዳሮት ተገብቶ የማሰብ ባህል ሊኖረን ይገባል።ይህ ሁኔታ በእራሱ ይዞ የሚመጣው በጎ የሆነም ያልሆነም ጉዳይ ቢያስከትልም የመንግስት ስርዓቱን የመቆጣጠር ሂደት ግን ሁሉንም ሊያስተካክል ይችላል።ይህ ግን አሁንም ከሙስና የፀዳ እና አቅም ያለው የመንግስት መዋቅር ያስፈልጋል።

የባድሜ ጉዳይ እና የኢትዮ- ኤርትራ ግንኙነት 

የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ዛሬ ያሳለፈው ውሳኔ ውስጥ አንዱ የአልጀርሱን ውሳኔ መቀበል እና ባድመን ለኤርትራ መስጠት ላይ መስማማት የሚል ነጥብ ይዟል።የዛሬው ውሳኔ በሰጥቶ መቀበል ደረጃ ስንመለከተው ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር በሚኖራት ግንኙነት ምን ታገኛለች የሚለው አሁን ይሄ ነው ብሎ ለመገመት ያስቸግራል።አሳዛኙ ጉዳይ ግን በእርባና ቢስ ጦርነት ያለቀው ከ80ሺህ በላይ የሚሆን የሰው ሕይወት ነው።የዩጋንዳው ፕሬዝዳንት በአንድ በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ሰሞን የጦርነቱን ምክንያት ሲገልጡ  '' ብታዩ የሚጣሉበት ቦታ እዚህ ግባ የማይባል ትንሽ ኮረብታ ቦታ ነች" በማለት ገልጠው ነበር።ጦርነቱ በሁለቱም በኩል የቆየ የቂም እና እብሪት መገለጫ እንጂ ሌላ ትርጉም አልነበረውም።

አንድ ምሁር ከሁለት ሳምንት በፊት  ለሸገር ራድዮ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ጉዳይ አስመልክተው ሲናገሩ  እንዲህ ብለዋል " ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ሲነጋገሩ የሚያተኩሩት ታክቲካዊ ጉዳይ እና ስነ ልቦናዊ የበላይነት ለማግኘት እንጂ ዘለቄታዊ በሆነው ስልታዊ ጉዳይ ላይ ማተኮር አለባቸው'' ብለዋል።ይህ አገላለጥ እኔ ሃሳቤን በሚገባ የምገልጥልኝ አድርጌ አየዋለሁ። የኤርትራ መንግስት ባድሜ ማግኘት ላይ ብቻ ሲያተኩር ህወሓት መራሹ መንግስትም ባድማ የእኔ ነች የሚል ስነ ልቦናዊ የበላይነት ለማግኘት ብቻ ሕዝብ ከህዝብ አለያይተው የኖሩት መንግሥታት ትልቅ ወንጀል ሰርተዋል።ህወሓት ባድመን ለመስጠት ከወሰነ ቆይቷል ሆኖም ግን  የትግራይ ህዝብንም ሆነ የኢትዮጵያን ሕዝብ ሲፈራ ኖሯል።አሁን በዶ/ር ዓብይ የጠቅላይ ሚኒስትርነት ዘመን ህወሓት ለትግራይ ሕዝብ እኔ አላደረኩትም ለማለት ዶ/ር ደብረ ፅዮን ዛሬ የባድመን መሰጠት ተስማምተው ተመልሰዋል።የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ግጭት ጉዳይ የባድሜ ጉዳይ አለመሆኑን ለመረዳት የአልጀርሱን ስምምነት መቀበል ብቻ ሰላም ላያመጣ በመቻሉ መረዳት ይቻላል።

ለማጠቃለል የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ስብስባ ቁልፍ የምጣኔ ሀብት አውታሮች ወደ ግል መዘዋወር ከሙስና የፀዳ፣ጠንካራ እና አቅም ያለው የሰው ኃይል ያለው መንግስት መኖር ወሳኝ ነው።በደካማ እና በሙስና የተዘፈቀ  መንግስት ውስጥ የውጭ ባለ ሀብት አስፈላጊ ቀረጥ ካለመክፈሉ በላይ የተከፈለውም ቀረጥ በትክክል ለሕዝብ ልማት አይውልም።ስለሆነም ሁሉም ዜጋ ሃገሩን ከባዕድ ወታደር ከመጠበቅ እኩል የምጣኔ ሀብት ቅርምቱን መቆጣጠር አለበት።የኢትዮጵያ ኤርትራ ጉዳይ በሌላ በኩል በአፍሪካ ቀንድ ከሚያንዣብበው የአካባቢ አረብ ሃገራት እና የውጭ ኃይሎች አንፃር ሁለቱ ሀገሮች ከመስማማት ውጭ አንዳችም አማራጭ የላቸውም። ይህ የባድሜ ስምምነት ግን የትግራይ ሕዝብ በህወሓት አዛውንት መሪዎቹ ላይ የሚነሳበት አዲስ የትግል ግንባር ሊሆን የማይችልበት ምክንያት አይታይም።

በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል እአአ ታህሳስ 12/2000 ዓም የተደረገው ስምምነት አንቀፆች 
Agreement Between Eritrea and Ethiopia signed in Algiers, 12 Dec. 2000.

Article 1

  1. The parties shall permanently terminate hostilities between themselves. Each party shall refrain from the threat or use of force against the other.
  2. The parties shall respect and fully implement the provisions of the Agreement on Cessation of Hostilities.

Article 2

  1. In fulfilling their obligations under international humanitarian law, including the 1949 Geneva Conventions relative to the protection of victims of armed conflict ("1949 Geneva Conventions"), and in cooperation with the International Committee of the Red Cross, the parties shall without delay, release and repatriate all prisoners of war.
  2. In fulfilling their obligations under international humanitarian law, including the 1949 Geneva Conventions, and in cooperation with the International Committee of the Red Cross, the parties shall without delay, release and repatriate or return to their last place of residence all other persons detained as a result of the armed conflict.
  3. The parties shall afford humane treatment to each other's nationals and persons of each other's national origin within their respective territories.

Article 3

  1. In order to determine the origins of the conflict, an investigation will be carried out on the incidents of 6 May 1998 and on any other incident prior to that date which could have contributed to a misunderstanding between the parties regarding their common border, including the incidents of July and August 1997.
  2. The investigation will be carried out by an independent, impartial body appointed by the Secretary General of the OAU, in consultation with the Secretary General of the United Nations and the two parties.
  3. The independent body will endeavor to submit its report to the Secretary General of the OAU in a timely fashion.
  4. The parties shall cooperate fully with the independent body.
  5. The Secretary General of the OAU will communicate a copy of the report to each of the two parties, which shall consider it in accordance with the letter and spirit of the Framework Agreement and the Modalities.

Article 4

  1. Consistent with the provisions of the Framework Agreement and the Agreement on Cessation of Hostilities, the parties reaffirm the principle of respect for the borders existing at independence as stated in resolution AHG/Res. 16(1) adopted by the OAU Summit in Cairo in 1964, and, in this regard, that they shall be determined on the basis of pertinent colonial treaties and applicable international law.
  2. The parties agree that a neutral Boundary Commission composed of five members shall be established with a mandate to delimit and demarcate the colonial treaty border based on pertinent colonial treaties (1900, 1902 and 1908) and applicable international law. The Commission shall not have the power to make decisions ex aequo et bono.
  3. The Commission shall be located in the Hague.
  4. Each party shall, by written notice to the United Nations Secretary General, appoint two commissioners within 45 days from the effective date of this agreement, neither of whom shall be nationals or permanent residents of the party making the appointment. In the event that a party fails to name one or both of its party-appointed commissioners within the specified time, the Secretary-General of the United Nations shall make the appointment.
  5. The president of the Commission shall be selected by the party-appointed commissioners or, failing their agreement within 30 days of the date of appointment of the latest party-appointed commissioner, by the Secretary-General of the United Nations after consultation with the parties. The president shall be neither a national nor permanent resident of either party.
  6. In the event of the death or resignation of a commissioner in the course of the proceedings, a substitute commissioner shall be appointed or chosen pursuant to the procedure set forth in this paragraph that was applicable to the appointment or choice of the commissioner being replaced.
  7. The UN Cartographer shall serve as Secretary to the Commission and undertake such tasks as assigned to him by the Commission, making use of the technical expertise of the UN Cartographic Unit. The Commission may also engage the services of additional experts as it deems necessary.
  8. Within 45 days after the effective date of this Agreement, each party shall provide to the Secretary its claims and evidence relevant to the mandate of the Commission. These shall be provided to the other party by the Secretary.
  9. After reviewing such evidence and within 45 days of its receipt, the Secretary shall subsequently transmit to the Commission and the parties any materials relevant to the mandate of the Commission as well as his findings identifying those portions of the border as to which there appears to be no dispute between the parties. The Secretary shall also transmit to the Commission all the evidence presented by the parties.
  10. With regard to those portions of the border about which there appears to be controversy, as well as any portions of the border identified pursuant to paragraph 9 with respect to which either party believes there to be controversy, the parties shall present their written and oral submissions and any additional evidence directly to the Commission, in accordance with its procedures.
  11. The Commission shall adopt its own rules of procedure based upon the 1992 Permanent Court of Arbitration Option Rules for Arbitrating Disputes Between Two States. Filing deadlines for the parties' written submissions shall be simultaneous rather than consecutive. All decisions of the Commission shall be made by a majority of the commissioners.
  12. The Commission shall commence its work not more than 15 days after it is constituted and shall endeavor to make its decision concerning delimitation of the border within six months of its first meeting. The Commission shall take this objective into consideration when establishing its schedule. At its discretion, the Commission may extend this deadline.
  13. Upon reaching a final decision regarding delimitation of the borders, the Commission shall transmit its decision to the parties and Secretaries General of the OAU and the United Nations for publication, and the Commission shall arrange for expeditious demarcation.
  14. The parties agree to cooperate with the Commission, its experts and other staff in all respects during the process of delimitation and demarcation, including the facilitation of access to territory they control. Each party shall accord to the Commission and its employees the same privileges and immunities as are accorded to diplomatic agents under the Vienna Convention on Diplomatic Relations.
  15. The parties agree that the delimitation and demarcation determinations of the Commission shall be final and binding. Each party shall respect the border so determined, as well as the territorial integrity and sovereignty of the other party.
  16. Recognizing that the results of the delimitation and demarcation process are not yet known, the parties request the United Nations to facilitate resolution of problems which may arise due to the transfer of territorial control, including the consequences for individuals residing in previously disputed territory.
  17. The expenses of the Commission shall be borne equally by the two parties. To defray its expenses, the Commission may accept donations from the United Nations Trust Fund established under paragraph 8 of Security Council Resolution 1177 of 26 June 1998.

Article 5

  1. Consistent with the Framework Agreement, in which the parties commit themselves to addressing the negative socio-economic impact of the crisis on the civilian population, including the impact on those persons who have been deported, a neutral Claims Commission shall be established. The mandate of the Commission is to decide through binding arbitration all claims for loss, damage or injury by one Government against the other, and by nationals (including both natural and juridical persons) of one party against the Government of the other party or entities owned or controlled by the other party that are (a) related to the conflict that was the subject of the Framework Agreement, the Modalities for its Implementation and the Cessation of Hostilities Agreement, and (b) result from violations of international humanitarian law, including the 1949 Geneva Conventions, or other violations of international law. The Commission shall not hear claims arising from the cost of military operations, preparing for military operations, or the use of force, except to the extent that such claims involve violations of international humanitarian law.
  2. The Commission shall consist of five arbitrators. Each party shall, by written notice to the United Nations Secretary General, appoint two members within 45 days from the effective date of this agreement, neither of whom shall be nationals or permanent residents of the party making the appointment. In the event that a party fails to name one or both of its party-appointed arbitrators within the specified time, the Secretary-General of the United Nations shall make the appointment.
  3. The president of the Commission shall be selected by the party-appointed arbitrators or, failing their agreement within 30 days of the date of appointment of the latest party-appointed arbitrator, by the Secretary-General of the United Nations after consultation with the parties. The president shall be neither a national nor permanent resident of either party.
  4. In the event of the death or resignation of a member of the Commission in the course of the proceedings, a substitute member shall be appointed or chosen pursuant to the procedure set forth in this paragraph that was applicable to the appointment or choice of the arbitrator being replaced.
  5. The Commission shall be located in The Hague. At its discretion it may hold hearings and conduct investigations in the territory of either party, or at such other location as it deems expedient.
  6. The Commission shall be empowered to employ such professional, administrative and clerical staff as it deems necessary to accomplish its work, including establishment of a Registry. The Commission may also retain consultants and experts to facilitate the expeditious completion of its work.
  7. The Commission shall adopt its own rules of procedure based upon the 1992 Permanent Court of Arbitration Option Rules for Arbitrating Disputes Between Two States. All decisions of the Commission shall be made by a majority of the commissioners.
  8. Claims shall be submitted to the Commission by each of the parties on its own behalf and on behalf of its nationals, including both natural and juridical persons. All claims submitted to the Commission must be filed no later than one year from the effective date of this agreement. Except for claims submitted to another mutually agreed settlement mechanism in accordance with paragraph 17 or filed in another forum prior to the effective date of this agreement, the Commission shall be the sole forum for adjudicating claims described in paragraph 1 or filed under paragraph 9 of this Article, and any such claims which could have been and not submitted by that deadline shall be extinguished, in accordance with international law.
  9. In appropriate cases, each party may file claims on behalf of persons of Eritreans or Ethiopian origin who may not be its nationals. Such claims shall be considered by the Commission on the same basis as claims submitted on behalf of that party's nationals.
  10. In order to facilitate the expeditious resolution of these disputes, the Commission shall be authorized to adopt such methods of efficient case management and mass claims processing as it deems appropriate, such as expedited procedures for processing claims and checking claims on a sample basis for further verification only if circumstances warrant.
  11. Upon application of either of the parties, the Commission may decide to consider specific claims, or categories of claims, on a priority basis.
  12. The Commission shall commence its work not more than 15 days after it is constituted and shall endeavor to complete its work within three years of the date when the period for filing claims closes pursuant to paragraph 8.
  13. In considering claims, the Commission shall apply relevant rules of international law. The Commission shall not have the power to make decisions ex aequo et bono.
  14. Interest, costs and fees may be awarded.
  15. The expenses of the Commission shall be borne equally by the parties. Each party shall pay any invoice from the Commission within 30 days of its receipt.
  16. The parties may agree at any time to settle outstanding claims, individually or by categories, through direct negotiation or by reference to another mutually agreed settlement mechanism.
  17. Decisions and awards of the Commission shall be final and binding. The parties agree to honor all decisions and to pay any monetary awards rendered against them promptly.
  18. Each party shall accord to members of the Commission and its employees the privileges and immunities that are accorded to diplomatic agents under the Vienna Convention on Diplomatic Relations.

Article 6

  1. This agreement shall enter into force on the date of signature.
  2. The parties authorize the Secretary General of the OAU to register this agreement with the Secretariat of the United Nations in accordance with article 102(1) of the Charter of the United Nations.

ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

መፅሐፌ ለገበያ ውሏል።My book is on sale.


===================
ጉዳያችን/ Gudayachn
ግንቦት 28/2010 ዓም (ጁን 5/2018 ዓም)

(Please read in English below after Amharic)
መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ፖሊሲ በመልካም የመንግስት አስተዳደር ላይ ያላቸውን ተፅኖ ዙርያ የተሰራው የጥናት ስራዬ በአውሮፓ ታዋቂ የሆነ አሳታሚ ድርጅት በመፅሐፍ መልክ ለማውጣት መርጦታል።በመሆኑም መፅሐፉን አማዞንን ጨምሮ በአውሮፓ እና አሜሪካ ባሉ የመፅሐፍ መሸጫዎች በኦንላይንም ማዘዝ ይችላሉ።በተለይ እርስዎ ቢገዙትም ሆነ  ለሚሰሩበት ድርጅት እንዲያዝ መረጃውን ቢሰጡ አይቆጩም።መፅሐፉን በእዚህ ማስፈንጠርያ ከፍተው ማዘዝ ይችላሉ።ከሞር ቦክስ ሱቅ ለመግዛት ይህንን ይጫኑ https://www.morebooks.shop/store/gb/book/policy-of-ngos-on-democratic-governance-case-study-of-dgf/isbn/978-613-9-84101-1

አማዞን ላይ ለማዘዝ ይህንን ማስፈንጠርያ ይጫኑ https://www.amazon.com/gp/offer-listing/6139841011/ref=sr_1_1_olp?ie=UTF8&qid=1528208707&sr=8-1&keywords=policy+of+ngos+on+democratic+governance+case+study+of+dgf 

My book is now available on international books market (including Amazon book sale) all over the world. Do not miss also to buy and share the information to others to make it their own property. Here is the link that you can order online from Morebooks click https://www.morebooks.shop/store/gb/book/policy-of-ngos-on-democratic-governance-case-study-of-dgf/isbn/978-613-9-84101-1

 To order from Amazon click on https://www.amazon.com/gp/offer-listing/6139841011/ref=sr_1_1_olp?ie=UTF8&qid=1528208707&sr=8-1&keywords=policy+of+ngos+on+democratic+governance+case+study+of+dgf

ጌታቸው በቀለ
Getachew Bekele Damtew 

Saturday, June 2, 2018

ወደፊት ለመራመድ በአካል ብቻ ሳይሆን በመንፈስም ዝግጅት ማድረግ ይገባናል።ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ኦስሎ፣ኖርዌይ ያደረጉት ንግግር (የጉዳያችን ልዩ ሪፖርታዥ)


ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ኦስሎ ግንቦት 25፣2010 ዓም (ፎቶ ጉዳያችን)


ጉዳያችን/ Gudayachn
ግንቦት 25/2010 ዓም (ጁን 2/2018 ዓም)

በእዚህ ሪፖርት ውስጥ የሚከተሉት ነጥቦች ተካተዋል። እነርሱም : - 

  • በኢትዮጵያ ፖለቲካ ያሉብን ችግሮች ምንድናቸው?
  • የብሔር ፖለቲካ በኢትዮጵያ እንዴት መጣ?
  • የ1983 ዓም የብሔር ፖለቲካ ዋነኛ ስህተት ምንድነው?
  • የለማ ቡድን (ዶ/ር ዓብይ) የለውጥ ዕድል በተመለከተ እንዴት እንሂድ?
  • የእነ ለማ ቡድን (ዶ/ር ዓብይ) የለውጥ ኃይል ከሌሎች ሀገሮች ምን መማር አለበት?
  • ሀገር ክትፎ አይደለም 


የአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ  እና አቶ ኦኬሎ በአካል እና  የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በስካይፕ የተገኙበት በርካታ ኢትዮጵያዊ ከኖርዌይ ልዩ ልዩ ከተሞች (ኦስሎን ጨምሮ)፣ከስዊድን፣እንግሊዝ እና ሌሎች የአውሮፓ ከተሞች የታደሙበት ስብሰባ ዛሬ ግንቦት 25/2010 ዓም ኦስሎ ከተማ ተደርጎ ነበር።በስብሰባው መክፈቻ ላይ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ አጭር የምስጋና ንግግር ካደረጉ በኃላ የዝግጅቱ አስተባባሪ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ አቶ ይበልጣል የመክፈቻ ንግግር፣ በኖርዋይ የአርበኞች ግንቦት 7 ወክለው አቶ ደባሱ ንግግር ካሰሙ በኃላ ግጥም በአማርኛ ወ/ሮ አፎምያ፣ እንዲሁም ግጥም በእንግሊዝኛ አቶ ልዑል አቅርበዋል።በመቀጠል የዕለቱ ዋና ተናጋሪ የነበሩት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ንግግር አሰምተዋል።

ፕሮፌሰር ብርሃኑ በዛሬው የኦስሎ ንግግራቸው መግብያ ላይ ባለፈው ዋሽንግተን ላይ ያደረጉትን ንግግር እንደማይደግሙ ነገር ግን እዛ ላይ ያልተነሱ ሌሎች ጉዳዮች ላይ እንደሚያተኩሩ በቀልድ አዋዝተው ከገለጡ በኃላ ንግግራቸውን ጀምረዋል።በንግግራቸው ላይ የተነሱትን ነጥቦች ከእዚህ በታች በርእስ ከፍዬ አቀርባለሁ።እዚህ ላይ ርዕሶቹ ለአንባቢ የትኩረት ነጥቦች እንዲረዳ ርዕሶቹን የሰጠሁት እኔ ነኝ።ንግግራቸው በርእስ ሳይከፈል በወጥነት የቀረበ ነው።

በኢትዮጵያ ፖለቲካ ያሉብን ችግሮች ምንድናቸው?

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የንግግራቸው መግብያ ያደርጉት በፖለቲካው መድረክ ለዘመናት የኖሩ ችግሮቻችንን ሲገልጡ በሶስት ዋና ዋና ነጥቦች አስቀምጠዋቸዋል።እነርሱም የመንፈስ ችግር፣ ለኢትዮጵያ ከእኔ ሌላ የሚያውቅ የለም ማለት እና የሌላውን አለመስማት ችግሮች ዋና ዋና እንደሆኑ አብራርተዋል።የመንፈስ ችግር ያሉት ላለፉት አርባ አመታት የኖረው ከፍተኛ የመጠራጠር እና ሁሉንም በበጎ አለማየት መሆኑን አብራርተው ይህ አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ሁኔታ ሳይቀር ዝም ብሎ የመጠርጠር መንፈስ መኖሩን ነገር ግን በእዚህ መንፈስ መያዝ እራሱ ወደ አደገኛ ሁኔታ እንዳይመራ ያላቸውን ስጋት ገልጠዋል።ይህንን ሲገልጡት ቃል በቃል  " መጠርጠርን አርት አድርገነዋል" ስለሆነም ከእዚህ የመንፈስ ችግር መውጣት አስፈላጊ ነው።ይህንን ስል ሁሉ ነገር አበቃ ተስተካከለ እያልኩ አይደለም።ሆኖም ግን በጥንቃቄ እያየን የምንሄደው መሆን እንዳለበት ከገለጡ በኃላ በአሁኑ ጊዜ አነጋገራችንም መቀየር አለበት ህወሓት እና ኢህአዴግ እያልን ነው የምናወራው ምክንያቱም ለለውጥ የተነሳ ከመካከላቸውም ስላለ ብለዋል።

ሁለተኛው እና ሶስተኛው ችግር  እኔ ያልኩት ብቻ ነው ትክክል የሚለው እና የሌላውን አለመስማት ፖለቲካችን መነሻው ከ1966 ዓም የለውጥ እንቅስቃሴ ጋር የተያያዘ እንደሆነ አብራርተው በዛን ጊዜ ወጣት በነበርንበት ወቅት ኢትዮጵያ የእራሷን ተጨባጭ ሁኔታ ያላገናዘበ ግን ከውጭ የመጣ ርዕዮት የተጫነባት አንዱ ምክንያት እኔ ያሰብኩት ብቻ ለኢትዮጵያ ይበጃል የሚል ስሜት ነበር።በእዚህም በርካታ ለሀገር የሚጠቅሙ ዜጎቻችንን አጥተናል።ይህ አደገኛ ስሜት ክፋቱ የተለየ ሃሳብ የሚያስበውን በሙሉ በጠላትነት መፈረጁ ነው። ይህ በ1983 ዓም የነበረው ለውጥም በተመሳሳይ መልኩ ደግሞታል ብለዋል። እነኝህ ሶስቱ ችግሮች ለመጀመርያው አብዮት መክሸፍ ምክንያት መሆናቸውን ያብራሩት ፕሮፌሰር ብርሃኑ የብሔር ፖለቲካ አነሳስ ታሪካዊ ዳራ ላይ ፍንጭ ሰጥተዋል።

የብሔር ፖለቲካ በኢትዮጵያ እንዴት መጣ?

የመጀመርያው ለውጥ ወቅት የውጭ ርዕዮት ዓለምን እንደ አመለካከት ወስዶ በሁሉም ኢትዮጵያዊ ላይ የመጫን ስህተት አንዱ እና ዋናው የክሽፈት ፖለቲካችን መሆኑን ከገለጡ በኃላ የብሔር ፖለቲካ እንዴት እንደ ርዕዮት ዓለም ራሱን ችሎ ብቅ እንዳለ ሲያብራሩ እንዲህ ብለዋል።
    " የብሔር ፖለቲካ በኢትዮጵያ በመጀመርያ በርዮት ዓለምነት የወጣ አስተሳሰብ አልነበረም።
       ያኔ የብሔር ፖለቲካ የታሰበው በታክቲክ ደረጃ ነበር።በታክቲክ ደረጃ የታሰበው የብሔር 
       ፖለቲካ እራሱን ችሎ ከምር አደረጉት እና በርዮት ዓለምነት ብቅ ያለው በ1983 ዓም ነው።"

የ1983 ዓም የብሔር ፖለቲካ ዋነኛ ስህተት ምንድነው?

ፕሮፌሰር ብርሃኑ በታክቲክነት ይነሳ የነበረው የብሔር ፖለቲካ ከምር ሆኖ በ1983 ዓም ራሱን ችሎ በርዮት ዓለምነት ሲቀርብ የአንድ የተለየ ኅብረተሰብን ጥቅም ለይቶ መቆም ያለውን አደገኛነት ከግንዛቤ አላስገባም ብለዋል።አንድን ኅብረተሰብ በብሔርም ሆነ በሌላ ለይቶ ለመብቱ መቆም በእራሱ የሚያመጣው ጉድለት ሲያብራሩ ግለሰብ፣ቤተሰብ እና የወል ስብስቦች የእየራሳቸው ፍላጎቶች ኖሯቸው ሳለ የብሔር ፖለቲካ ግን የሁሉንም የተለያየ ፍላጎት ጨፍልቆ እኔ የማውቅላችሁን ፍላጎት ውሰዱ የሚል ነው ብለዋል። ይህንንም በምሳሌነት ሲያስረዱ በወል ስብስብ ውስጥ ለምሳሌ የክርስትና እና የሙስሊም ወገኖቻችን የእየራሳቸው ፍላጎት አላቸው፣ሙስሊሙ ክርስቲያኑ አምልኮ ውስጥ አይገባም፣ክርስቲያኑም ሙስሊሙ ውስጥ እንዲሁ አይገባም።የወል ስብስብን ፍላጎት ጨፍልቆ እኔ በማውቅልህ መንገድ ሂድ ማለት አይቻልም።ምክንያቱም ሀገር እና ፖለቲካን ስታስብ ሁል ጊዜ ሁሉንም የወል ስብስቦች የሚያረካ መሆን አለበት።አንዱን በብሄር ወይንም በሌላ መልክ ነጥሎ ለመጥቀም የሚያስበው የብሔር ፖለቲካ አንዱ እና ዋናው ስህተቱ አሁን ድረስ ሀገራችን ችግር ላይ የጣላት ምክንያትም ፖለቲካ (መንግስት) ለወል ስብስቦች መብት ብቻ ለመቆም የመሞከሩ አባዜ መሆኑን ፕሮፌሰር ብርሃኑ በንግግራቸው አስረግጠው አብራርተዋል።

ከእዚሁ የብሔር ፖለቲካ ለአንድ የወል ማኅበረሰብ ጥቅም ከመቆሙ አንፃር በመጨረሻ ውድቀቱ ላይ ቆምኩለት የሚለውን የወል ማኅበረሰብ ብቻ ሳይሆን ቆሜለታለሁ የሚለውን የራሱን ማኅበረሰብ መጨረሻ ላይ መብላቱ ነው አስከፊው ሁኔታ ብለዋል።

የለማ ቡድን (ዶ/ር ዓብይ) የለውጥ ዕድል በተመለከተ እንዴት እንሂድ?

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከላይ የተሰጠውን የለማ ቡድን ወይንም የዶ/ር ዓብይ የለውጥ ዕድል በሚል በቀጥታ ርዕስ አይስጡት እንጂ የአሁኑን የሀገር ቤት ለውጥ አስመልክተው ሲናገሩ ሶስተኛው ዕድል በሚል ገልጠውታል።ማንም ሀገር ለለውጥ ሶስት ጊዜ ዕድል ያገኘ ሀገር የለም ካሉ በኃላ "የአሁኑን ዕድል ኢትዮጵያ ካበላሸች እና ካበላሸን እንደ ሀገር ልንቀጥል የምንችልበት ሁኔታ ያሰጋል" ብለዋል። ዓቢይ ከሰማይ የመጣ አድርጋችሁ አትዩ በትግሉ ሂደት የመጣ ነው።አንዳንድ ወገኖች ሲያታልሉን ነው ምናምን እያሉ ያወራሉ።ቀደም ብዬ እንዳልኩት መጠርጠር አርት አድርገን ይዘነዋል።እነ ዓብይ የመጡበትን ሂደት እናስታውስ ከመመረጣቸው በፊት ማን ይመረጣል እያልን እንደነበር አስታውሰው በሂደቱ ግን እነዓብይ እንዳሸነፉ በግልጥ እንደታየ አስታውሰዋል።ስለሆነም አሉ ፕሮፌሰር ብርሃኑ " የለውጥ ኃይሎችን (እነዶ/ር ዓብይን ኢትዮጵያን ዲሞክራሲያዊ ለማድረግ እስከ ሄዱ ድረስ እንደግፋቸዋለን።የምያደናቅፉትንም መታገል አለብን" ብለዋል።

የእነ ለማ ቡድን (ዶ/ር ዓብይ) የለውጥ ኃይል ከሌሎች ሀገሮች ምን መማር አለበት?

ፕሮፌሰር ብርሃኑ እነዶ/ር ዓብይ በፖለቲካ አሸንፈዋል።ህወሓትም በፖለቲካ ተሸንፏል ካሉ በኃላ ሆኖም ግን ህወሓት በወታደሩ ዙርያ እና በዝርፍያ የደለበ ሀብት በመያዝ አሁንም አሉ ብለዋል።ስለሆነም የለውጥ ኃይሉ ይህንን ማወቅ እንዳለበት እና ከእዚህ አንፃር አካሄዱን መቃኘት እንዳለበት አሳስበው ለአብነት የግብፅን እና የደቡብ አፍሪካን የቅርብ ታሪክ ጠቁመዋል።የግብፅ አብዮት ሲነሳ እና ሙርሲ የሙባረክን ኃይል ከጣለ በኃላ የሀገሪቱን ሀብት 50% የያዘው የግብፅ ጦር ኃይል ህዝቡ የዕለት ዳቦ እንዳያገኝ በማድረግ ሕዝብ ሙርሲ ላይ እንዲነሳ እና የሙባረክ ሰዎች ተመልሰው እንዲመጡ ማድረጉን ገልጠዋል።በተመሳሳይ መልኩ ከነጭ የአፓርታይድ ወገን ሁኔታው እንደማያስኬድ የተመለከተው ዲክለርክ ለለውጥ ሲነሳ የተፈጠረውን የመቀልበስ ሂደት በምሳሌነት አሳይተዋል።ስለሆነም አሁን በኢትዮጵያ ያለው የለውጥ ኃይል (የለማ ቡድን) ይህንን ከግንዛቤ ውስጥ ባስገባ መልክ መንቀሳቀስ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል።

ሀገር ክትፎ አይደለም 

በንግግራቸው መጨረሻ ላይ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ኢትዮጵያን ዲሞክራሲያዊ ከማድረግ ውጭ ሌላ አማራጭ እንደሌለ ገልጠው ለውጡን እኛ ካላመጣነው የሚል የስልጣን ጥማት የለንም።እኛ መድረስ አለብን የምንለው ዜጎች አሽከር ሳይሆን የእኔ የሚሉት ሀገር ባለቤት እንዲሆኑ ነው ካሉ በኃላ ንግግራቸውን ሲደመድሙ እንዲህ ብለዋል : -
      " ሀገር ክትፎ አይደለም።ሀገር ሁላችን ባለቤት የምንሆንባት ደረጃ መድረሷን ማረጋገጥ አንዱ ግባችን ነው ከአሁን በኃላ ተመልሶ የወያኔ ኃይል ስልጣን ላይ እንዳይመጣ ማድረግ ዋና ስራችን መሆን አለበት።ለእዚህም በአካሄድ ብቻ ሳይሆን ቀደም ብዬ እንደተቀስኩላችሁ በመንፈስ ዝግጅትም ሊኖረን ይገባል።በ1966 እንደነበረው የእኔ ብቻ ሃሳብ ትክክል ነው የሚል ፖለቲካ ውስጥ መግባት የለብንም።ስለኢትዮጵያ መጨነቅ የእኛ ብቻ ሥራ ነው ብለን አናምንም የዓብይም የሁሉም እኩል ኃላፊነት ነው።ከእነ ዓብይም ሆነ ከሌሎች ሀገር ለመገንባት ከሚቆሙት ጋር ሁሉ መቆም አለብን ከትጥቅ ትግል ጋር እና ከተቃዋሚነት ጋር አልቆረብንም" ብለዋል።




ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com