ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Thursday, October 19, 2023

ኢትዮጵያ ባነሳችው የባሕር በር ጉዳይ ላይ አንድም የአውሮፓ፣የሰሜን አሜሪካ፣ደቡብ አሜሪካ፣እስያና አውስትራልያ ሀገር ትክክል አይደለም ያለ መንግስት የለም።

  • የአፍሪካ ሕብረትም ሆነ የተባበሩት መንግስታት በጉዳዩ ላይ ምንም አለማለት፣ሁለቱም በኢትዮጵያ የወደብ ባለቤትነት ጉዳይ ላይ ቅንጣት ታክል ጥርጣሬ እንደሌላቸው በትክክል ያሳያል።
============
ጉዳያችን
============


ኢትዮጵያ ባነሳችው የባሕር በር ጉዳይ ላይ አንድም የአውሮፓ፣የሰሜን አሜሪካ፣ደቡብ አሜሪካ፣እስያና አውስትራልያ ሀገር ትክክል አይደለም ያለ አንድም መንግስት የለም።ለወትሮው አንዲት ሀገር የእዚህ ዓይነት ጉዳዮችን ስታነሳ በቶሎ አስተያየት ለመስጠት እና ለመቃረን የሚጋፉ መንግስታትም ሆኑ ባለስልጣናት የሞሉባት ዓለማችን በኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጉዳይ ላይ ምንም ዓይነት ብዥታ አልተፈጠረባቸውም። ይህ ማለት በርካታ የዓለማችን ሀገሮች፣ በጉዳዩ ላይ የሚስማሙበት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ ቀንድ የራሱ የሆነ የኃይል ሚዛን የሚፈጥር እና የቀይ ባሕርና የሜዴትራንያ ባሕር ፀጥታም የሚያረጋጋ ለመሆኑ አንዳችም ጥርጣሬ አልፈጠረባቸውም። ከእዚህ ውጪ ከኤርትራ፣ጂቡቲና የሱማልያ የፓርላማ አባላት፣ጋዜጠኞች የተሰጡ ምላሾች የሚጠበቁ እና ተፈጥሯዊ ምላሾች ናቸው። ከኤርትራ ተሰጠ የተባለውም ጉዳዩን ሙሉ በሙሉ ለመርሳት ለመሞከር የሚደረግ እራስን የማታለል ዓይነት መግለጫ ነው። ይህም ሆኖ መግለጫው የዓለምን ትኩረት አልሳበም።

በሌላ በኩል በጉዳዩ ላይ ''ያዙኝ ልቀቁኝ '' ትላለች ተብላ የምትጠበቀው ግብፅ በጋዛ እስራኤል ጉዳይ ተወጥራ ''ነፍስ ውጪ ነፍስ ግቢ'' ላይ ነች።ከሰሜናዊ ጋዛ እንዲወጡ የተደረጉ ፍልስጤማውያን ጎርፍ እንዳያጥለቀልቃት ጭንቀት ውስጥ ነች።

ዓለም የኢትዮጵያን እውነት በእንዲህ ዓይነት ደረጃ ሲመለከት እራሳቸው የኢትዮጵያ የሆነው ሰፌድና የባዕድ የሆነ ድስት በመልክ መለየት አቅቷቸው እዚህ እና እዝያ እየዘለሉ ግራ ተጋብተው የኢትዮጵያን ሕዝብ ግራ ለማጋባት የሚሞክሩት ዩቱበር ወገኖቻችን ናቸው። የኢትዮጵያ ህዝብም ሆነ የኤርትራ ህዝብ ዛሬ ነቅቷል።ከኢትዮጵያም ከኤርትራም ሰው በከንቱ እንዳይወድቅ ካለፈው ተምሯል። ይህም ሆኖ ግን ኢትዮጵያን ካለወደብ አስቀርቶ በሰላም ውሎ ማደር እንደማይኖር ይህም ለማንም እንደማይበጅ ሁሉም በየቤቱ ገብቶታል።ጸብ ብሎ ነገር የለም። ኢትዮጵያም ካለወደብ ውላ ለማደር አትችልም።ይህንን እውነታ ማስታረቅ የግድ ነው።
============////==================

Thursday, October 12, 2023

የቀይ ባሕርን እውነት ጠ/ሚ/ር ዐቢይ ሲናገሩት ስህተት፣ሌላው ሲያወራው እውነት ሊሆን አይችልም። እራሳቸው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ የማይክዱትን እውነት ለማስተባበል አንሞክር።




ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ
  • ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ስለ ቀይባሕር አሁን የተናገሩት ''አቅጣጫ ለማስቀየር'' ነው የሚለው አሉባልታ ውሸት ለመሆኑ ግልጽ የሆኑ ማስረጃዎች አሉ።

=========
ጉዳያችን ምጥን
=========

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ስለ ቀይባሕር አሁን የተናገሩት አቅጣጫ ለማስቀየር ነው የሚለው አባባል ውሸት ለመሆኑ ግልጽ ማስረጃ

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ሰሞኑን ከከፍተኛ የመንግስት አመራሮች ጋር ያደረጉት ውይይት ላይ ገና ሙሉ ቪድዮው ያልተለቀቀ የቀይባሕርን አስመልክተው በተናገሩት ንግግር የቀይባሕር ጉዳይ የኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ ነው ማለታቸውን የተለያዩ ዩቱበሮች የተለያዩ አስተያየቶች ሲሰጡ እየተመለክትን ነው። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሙሉ ንግግር ገና አልተለቀቀም።ሙሉ ይዘቱ ሲለቀቅ የምንከታተለው ነው። 

ይህ በእንዲህ እያለ ግን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ሰሞኑን ስለ ቀይባሕር የተናገሩት አቅጣጫ ለማስቀየር ነው የሚለው ፈጽሞ ውሸት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን እንደመጡ በቅድምያ ከሰሩት ስራ ውስጥ የባሕር ኃይል መመስረት ነው።ከፈረንሳይ እስከ ዱባይ ለባሕር ኃይል ስልጠና ማነጋገር የጀመሩት፣ኢትዮጵያ ከ27 ዓመታት በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ የባሕር ኃይል አድሚራል ከመሾም ሰልጣኞች እስከ ማስመረቅ ያደረሱት ወደ ስልጣን እንደመጡ በጀመሩት ስራ ነው።

ይህ ብቻ አይደለም የመከላከያ ሚኒስትር ዓርማው ላይ የባሕር ኃይል ዓርማ ያከለበትም ከዓመት በፊት ነው። ከእዚህ በተጨማሪ  ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ በፓርላማ የቀይ ባሕርን አስመልክተው የተናገሩት ንግግር ላይ ከአንድ ዓመት በፊት ሲናገሩ የቀይ ባሕር ጉዳይ የማይተው ጉዳይ ነው፣በሰላማዊ መንገድ ባሕር የማግኘት መብት እንዳለን፣ ይህንን አናደርግም የሚሉ ካሉ ቃል በቃል '' እኛም መረበሻችን አይቀርም '' የሚል ቃል አክለው ይህ ሰላም አያመጣም በሚል በግልጽ አማርኛ መንገራቸውን ጉዳያችን ታስታውሳለች።ከእዚህ ሁሉ በላይ ብልጽግና የኢትዮጵያ የእድገት አቅጣጫ የሚጠቁም ሰነድ አስመልክቶ ከአንድ ዓመት በፊት ስራ አስፈጻሚ ስብሰባ እንደተጠናቀቀ የወጣ መግለጫ ላይም የብልጽግና ፓርቲ ኢትዮጵያ የባሕር በር እንዲኖራት እንደሚሰራ እና ይህ ተፈጥሯዊ መብቷ እንደሆነ አሁንም በግልጽ አማርኛ ጽፎ ነበር።

ይህ ሁሉ ማስረጃ እያለ ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተናገሩት ''አቅጣጫ ለማስቀየር ነው'' የሚለው አባባል ፈጽሞ ሚዛን አይደፋም። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀድመው በግልጽ ተናግረዋል።አቶ ኢሳያስ ይህንን ተረድተው የአሰብ ወደብን ወግ ባለው መልክ ለኢትዮጵያ እንዲከፍቱ ለማግባባት ከሰላም ስምምነት እስከ የአሰብ ወሎ መንገድ ግንባታ እስከ በኤርትራ ላይ የተጣለው እቀባ ይነሳ ብሎ ተመድን እስከመጠየቅ ድረስ ተጉዘዋል። ይህም ሆኖ እስካሁን ለውጥ አለመምጣቱ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ወቅቱን አንብበው ቀድመው የጀመሩትን ሥራ እንደገፉበት የሰሞኑ ንግግራቸው ያሳያል እንጂ ድንገት ዛሬ የመጣ ሃሳብ እንደሆነ አድርጎ መናገር ሚዛን የማይደፋ እና ማስረጃ አልባ አገላለጽ ነው። ጉዳዩ እውነት ነው። ከአንድ መቶ ሃያ ሚልዮን ሕዝብ በላይ የሆነ የኢትዮጵያ ሕዝብ በ30 ኪሎሜትር እርቀት ላይ ሆኖ የባሕር በር ሊነፈገው እንደማይገባ ይህ ፈጽሞ ሰላም እንደማያመጣ የኤርትራ ተወላጆችም ሆኑ አቶ ኢሳያስ ጠንቅቀው ያውቃሉ።

ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ዳርቻ ላይ መገኘቷን ከአሜሪካ እስከ ሩስያ፣ከቻይና እስከ ዱባይ የሚደግፉበት አምስት ምክንያቶች  

  • በዓለም ላይ የሚደረገው ንግድ አውሮፓን ከመካከለኛው ምስራቅና ከሩቅ ምስራቅ ጋር የሚያገናኘው የቀይ ባሕር በተባበሩት መንግስታት ግምት መሰረት በዙርያው አሁን ካለው ህዝብ ብዛት እኤአ 2050 ዓም 343 ሚልዮን የሚደርሰው ይህ አካባቢ አንድ ሺህ ኪሚትር እርዝመት ያለው የባሕሩ ክፍል አስር ሚልዮን የማይሞላ ህዝብ ባላት ኤርትራ ብቻ ሰላሙ ይጠበቃል ብለው ስለማያምኑ፣
  • ቀይባሕርን ለመቆጣጠር አንዳንድ የመካከለኛ ምስራቅ ሀገራት የያዙት አጀንዳ በምስራቁም በምዕራቡም ሀገራት በተለያየ የስጋት ደረጃ ላይ መውደቁ፣
  • አሜሪካ፣ሩስያ ወይንም ቻይና በቀጥታ የቀይባሕርን በብቸኝነት መቆጣጠር ስለማይችሉ እና አንዳቸው አንዳቸውን ስለሚጠባበቁ ከእዚህ ሁሉ እንደኢትዮጵያ በህዝብ ብዛት ከ120 ሚልዮን ህዝብ ባላት ኢትዮጵያ ቢጠበቅ ያላቸው ፍላጎት መኖሩ፣
  • አቶ ኢሳያስ የዕድሜያቸው መግፋት ተከትሎ በቀጣይ ኤርትራን የሚመራ ጠንካራ አመራር በሌለበት ሁኔታ አቶ ኢሳያስ በድንገት ቢያልፉ በኤርትራ በሚነሳው የስልጣን ሹክቻ ሀገሪቱ ወደየከፋ የእርስ በርስ ጦርነት ከገባች የቀይ ባሕር ባልተጠበቀ መልኩ በሽብርተኞች እጅ እንዳይወድቅ የሁሉም ኃያላን መንግስታት ስጋት ብቻ ሳይሆን የእስራኤልም ቀዳሚ ስጋት መሆኑ፣
  • የመጨረሻው ምክንያት እጅግ ወቅታዊው የፍልስጤም እስራኤል ጦርነት መልሶ ማገርሸቱ፣አሜሪካ ጦሯን ወደ መካከለኛው ምስራቅ በብዛት መላክ መቀጠሏን አስታኮ የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ከፈነዳ አንዱ ትኩረት የሚሆነው መንግስት አልባዋ የመንን የመፋለምያ ሜዳ አድርጎ ቀይባሕርን የማወከ ተግባሩ ስለሚባባስ ይህንን አሁንም ኤርትራ ለመቆጣጠር በሰው ኃይልም ሆነ በሃብት ፍሰት መቋቋም ስለማትችል አሁንም ለተለያዩ ኃይሎች ጋር በተለይ ጸረ ምዕራብ ከሆኑት ጋር የመዋዋል አደጋው አፍጥጦ በመምጣቱ፣
የሚሉት ዋና ዋና ሃሳቦች ውስጥ ሲሆኑ ቀይባሕር በህዝብ ብዛትም ሆነ በወታደራዊ ግንኙነት ከመካከለኛው ምስራቅ ጋር ያልተሞዳሞደ እና  የተሻለ ኃይል ያላት ኢትዮጵያ በቀይባሕር መገኘቷ ለሁሉም አንዱ ገላጋይ ሃሳብ መሆኑን ያመኑበት ይመስላል።ለእዚህ ዓይነቱ ጉዳይ በቀዳሚነት የምትቀናቀን ግብፅ ስትሆን አንዳንድ የተዳከመች ኢትዮጵያን ማየት የሚፈልጉ የመካከለኛው ምስራቅ ሀገሮች ከግብፅ ጀርባ የሚኮለኮሉ ይሆናሉ።

ለማጠቃለል ኢትዮጵያ መልሳ ከኤርትራ ጋር ወደ ደም መፋሰስ በባሕር ምክንያት እንድትገባ ኢትዮጵያውያንም ሆኑ የኤርትራ ተወላጆች ፍላጎት አይደለም። ይህ ግን ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር መውጫ የማግኘት መብትና እውነትን አይቀይረውም። ጉዳዩ ለትውልድ የሚሻገር ነው። ሕጋዊና ሰላማዊ በሆነ መንገድ መፍታት የሁሉም ግዴታ ነው። ጉዳዩን ግን  ጠ/ሚ/ር ዐቢይ ሲናገሩት ስህተት፣ሌላው ሲያወራው እውነት ሊሆን አይችልም። እራሳቸው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ የማይክዱትን እውነት  ለማስተባበል አንሞክር።
===============////============


Sunday, October 8, 2023

በቋፍ ላይ የነበረው የዓለማችን አጠቃላይ ፀጥታ አደጋ ላይ ወድቋል፣የተፈራው የፍልስጤም-እስራኤል ጦርነት ተቀስቅሷል፣ሀገራት ጎራ መለየት ጀምረዋል።

  • የአሁኑ የፍልስጤም እስራኤልን ጦርነት ለዓለማችን የከፋ ከሚያደርጉት ውስጥ ስድስቱ ምክንያቶች
=========
ጉዳያችን ምጥን
=========

በዓለማችን ላይ ሁሉንም ሀገር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ይነካል የተባለው ''እምብርት'' የፍልስጤም- እስራኤል ጦርነት ተቀስቅሷል።የጦርነቱን መቀስቀስ ተከትሎ የአሚሪካው ፕሬዝዳንት ባይደን ለእስራኤል የጦር መሳርያ መላካቸውን እና መንገድ ላይ መሆኑን መግለጻቸው ማምሻውን ተገልጿል። ኢራን ከፍልስጤም ጎን እንግሊዝና ኔቶ ከእስራኤል ጎን መሰለፋቸውን አሳውቀዋል።የተባበሩት አረብ ኢምሬት በተለየ ሁኔታ የገለልተኛነት ቦታ መያዟ ሲሰማ፣ በግብጽ የእስራኤል ቱሪስቶች ላይ ጥቃት መፈጸሙ ሲገለጽ አጠቃላይ ክስተቱ በቋፍ ላይ የነበረውን የተከፋፈለ ዓለም ''ጠብ ያለሽ በዳቦ'' ዓይነት ትርጉም የለሽ ግጭት ውስጥ እንዳያስገባ ተፈርቷል። የአሁኑ የሀማስ በእስራኤል ላይ የጀመረው ጥቃት ከቀደሙት የሚለየው እስራኤል በኃይል ይዛቸዋለች ባላቸው ግዛቶች ላይ ሳይሆን ጥቃቱ የፍልስጤም ግዛት ባልሆነው የእስራኤል መሬት ላይም መሆኑ የነገሩ ሰፋ ብሎ መጀመር ያሳያል፣ይህ በቀላሉ በዲፕሎማሲ የሚፈታ እንደማይሆን በራሱ አመላካች ነው።

የአሁኑ የፍልስጤም እስራኤልን ጦርነት ለዓለማችን የከፋ ከሚያደርጉት ውስጥ ስድስቱ ምክንያቶች : 
  • የሩስያ ዩክሬን ጦርነትን ተከትሎ በምዕራቡና ሩስያ፣ቻይና መሃል ያለው ውጥረት ከመቼውም ጊዜ በከፋ ሁኔታ ላይ መሆኑ፣
  • የተባበሩት መንግስታት በተዳከመበት እና የዓለምን ጸጥታ ችግር የመፍታት አቅሙ በተደጋጋሚ ተፈትኖ በወደቀበት ጊዜ መሆኑ፣
  •  የጸጥታው ምክር ቤት አምስቱ አባላት በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ የጋራ አጀንዳቸው በሳሳበት እና ለእዚህም አንድ ዓይነት መፍትሄ ገና ባላገኙበት ወቅት መሆኑ፣
  • የሰሜን አትላንቲክ ቃልኪዳን ሀገሮች ውስጥ አባል የሆነችው ቱርክ በፍልስጤም እስራኤል ጉዳይ የምትወስደው አቋም ለድርጅቱ የራሱ የሆነ ጥላ ማጥላቱ፣
  • ከኮቪድ በኋላ የተጎዳው የብዙ ሀገሮች ምጣኔ ሀብት በፈጠረው የኑሮ ውድነት ሳብያ በብዙ ሀገሮች ያለው የውስጥ ቅራኔ በተባባሰበት ጊዜ መሆኑና ይህም በብዙ ቦታዎች ''ግልገል ጦርነቶች'' የመፍጠር አደጋ መኖሩና
  • የምዕራቡን ዓለም በማስተባበር የመሪነቱ ሚና የነበራት አሜሪካ በአሁኑ ጊዜ ያላት ፕሬዝዳንት የነቃና የተጋ አለመሆን ብቻ ሳይሆን ሰላማዊ መፍትሄ የማምጣት አቅሙ ያነሰ መሆኑ የሚሉት ይጠቀሳሉ።
================//////============
ኢትዮጵያ በቴዎድሮስ ካሣሁን



ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...