ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, January 29, 2021

ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን መድረክ "ድምፃችንን ለቤተ ክርስቲያናችን" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ የውይይት መድረክ እሁድ ጥር 23/ 2013ዓም (Sunday January 31/2021 ዓም) በዙም አዘጋጅቷል።

ጉዳያችን/Gudayachn

ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን መድረክ "ድምፃችንን ለቤተ ክርስቲያናችን"   በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ የውይይት መድረክ እሁድ ጥር 23/ 2013ዓም   (Sunday January 31/2021 ዓም) በዙም አዘጋጅቷል። በዝግጅቱ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ምዕመናን ስለ ቀጣዩ ምርጫ ምን ያስባሉ? ሚናቸውስ ምንድን ነው ? ለእነዚህና ተመሳሳይ ጉዳዮች የሚነሱበት መርሐግብር እንደሆነ ከመርሃግብሩ ማስታወቂያ ለማወቅ ተችሏል። 

በዝግጅቱ ላይ ምሑራን ገለጣዎች የሚያቀርቡ ሲሆን በሀገር ቤት እና በመላው ዓለም የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናት፣ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት እና ምዕመናን እንደሚገኙበት ጉዳያችን ተረድታለች።
የስብሰባውን የዙም መግቢያ ኮዱን ከእዚህ በታች ካለው የመርሐግብሩ ፖስተር እና በድምፅ ከተለቀቀው ቪድዮ ላይ ማግኘት ይችላሉ።

============
ማስታወቂያ 
============
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 


Wednesday, January 27, 2021

ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ወጣት ዲና (Dina) በመጪው ቅዳሜ በኖርዌይ ቴሌቭዥን ለመሎዲ ግራንድ ፕሪክስ ውድድር ትቀርባለች።በስልክዎ ድምፅ በመስጠት እንድታሸንፍ ያድርጉ።

Etiopisk-norske, Dina Matheussen, er blant fire artister for Melodi Grand Prix.

በኖርዌይ ነዋሪ የሆነችው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ወጣት ዲና (Dina) ከአዲሱ ነጠላ ዜማዋ ላይ የተወሰደ ፎቶ 


ጉዳያችን/Gudayachn

ዲና ማቴዎስ ትባላለች።ነዋሪነቷ በኖርዌይ የሆነና ትውልደ ኢትዮጵያ የሆነች የ17 ዓመት ወጣት ነች።ገና 12 ዓመት እያለች ነው የዳንስ እና የድምፃዊነት ስራዋን የጀመረችው።ዲና የሙዚቃ ሰው ብቻ አይደለችም።በካራቴ ስልጠና ባለ ጥቁር ቀበቶ ተሸላሚም ድንቅ ወጣት ነች።

በ2014 ዓም እኤአ በኖርዌይ ቲቪ ቻናል 2 ላይ በሚቀርብ የኖርዌይ ታለንት ውድድር ላይ ከፍተኛ አድናቆትን አትርፋ ነበር።በ2017 ዓም በኖርዌይ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን (ኤንአርኮ) የዓመቱ የዳንስ ውድድር ላይም ተሳትፋ ነበር።ባለፈው ዓመት በኖርዌይ አይዶል 2020 ላይ የበዮንሴን "Run the World (Girls)" የተሰኘውን ሙዚቃ በማቅረብ የኖርዌይ አድናቂዎቿን አስደምማለች።በ2019 ዓም በኖርዌይ ብሮድካስት ቴሌቭዥን (ኤንአርኮ) ቻናል 3 ላይ ''አንድ ነን'' ''we are one'' በሚል ያቀረበችው ሙዚቃ ላይ የት መጣ መሰረቷ ኢትዮጵያ መሆኑን በመድረኩ ላይ አሳይታበት ተመልካቾችን ሁሉ አስደንቃለች።

የዲና ተግባራት እነኝህ ብቻ አይደሉም።በእየዓመቱ ወደ ኢትዮጵያ እየሄደች የኦቲዝም እና ልዩ ልዩ ችግር ያለባቸውን ልጆች ለእዚሁ ሥራ ብላ ባጠራቀመችው ገንዘብ ትረዳለች።በያዝነው ዓመት ወደ ኢትዮጵያ ለተመሳሳይ መልካም ተግባር መሄድ ያልቻለቸው በኮቪድ ወረርሽኝ ሳብያ ነው።አሁንም ግን ኢትዮጵያውያንን ለመርዳት ገንዘብ እያጠራቀመች እንደሆነ እና መርዳቷን እንደምትቀጥል በያዝነው ሳምንትም ባደረገችው ቃለ መጠይቅ ገልጣለች።

ከዲና ጋር ያለፉት ሌሎች አራት አርቲስቶች ካርሰን (Karsten)፣ኤሚ (Emmy) እና ኡለ ሀርዝ (Ole Hartz)
FOTO: JULIA MARIE NAGLESTAD / NRK

ዲና የአሁኑ ቅዳሜ ጥር 22/2013 ዓም (ጃንዋሪ 30/2021ዓም) የኖርዌይ ብሮድካስት ቴሌቭዥን የኖርዌይ ሜሎዲ ግራንድ ፕሪክስ (Norsk Melodi Grand Prix) ውድድር  ከተመረጡት አራቱ ውስጥ ገብታለች።በውድድሩ ሰዓት ዲና እንድታልፍ ኢትዮጵያውያን በስልክ በሚሰጠው ድምፅ በመስጠት ተሳታፊ እንዲሆኑ ተጠይቀዋል።የኖርዌይ ቴሌቭዥን (ኤን አር ኮ -NRK) ''ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ዲናዬ በዘፈኗ ውስጥ የአማርኛ ቃላት እንዲገቡ ያደረገችው መነሻዋ ከኢትዮጵያ መሆኑን ለማመልከት ነው'' በማለት ገልጦታል።

ዲና የቅዳሜውን ውድድር አልፋ ለፍፃሜው ስትደርስ በአውሮፓ ደረጃ ለሚደረገው ዋናው ውድድር ደረሰች ማለት ነው።በእዚህም አንዲት ትውልደ ኢትዮጵያዊት ለአውሮፓ ምርጥ ውስጥ ስትገባ የመጀመርያዋ ያደርጋታል ማለት ነው።በመሆኑም በቅዳሜው ምሽት ውድድር ላይ ኢትዮጵያውያውያን፣ትውልደ ኢትዮጵያውያን እና ኖርወጅያውያን ለዲና በስልካችሁ ድምፅ በመስጠት ኃላፊነታችሁን መወጣት አትዘንጉ።

ከእዚህ በታች ዲና ከሦስት ቀናት በፊት የለቀቀችውን ነጠላ ዜማ ከዩቱቧ ላይ ያለውን ከስር ይመለከቱ።


============
ማስታወቂያ 
============
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Tuesday, January 26, 2021

አስደናቂዋ ክብርት ፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ግብፅ በኢትዮጵያ አንፃር በአፍሪካ ለመቆለፍ የሞከረችውን ዲፕሎማሲ አንድ በአንድ እየተረተሩት ነው።

ክብርት ፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ

ጉዳያችን/Gudayachn 

>> ከጽሁፉ ስር አንድ ወጣት ታንዛንያዊ በክብርት ፕሬዝዳንት ጉብኝት ተደስቶ ጉብኝቱን በቪድዮ ያቀናበረውን ይመልከቱ።

የአንደኛ  እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአዲስ አበባ ሊሴ ገብረማርያም የፈረንሳይኛ ትምህርት ቤት ተምረዋል።በመቀጠለም በፈረንሳይ ሀገር የሚገኘው ሞንትፒለር ዩንቨርስቲ ተምረዋል።ፕሬዝዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ ከአምባሳደር ዮዲት እምሩ ቀጥለው ሁለተኛ ሴት ኢትዮጵያዊ አምባሳደር ናቸው።በአምባሳደርነት በሴኔጋል መቀመጫቸውን አድርገው የማሊ፣ከፕቨርድ፣ጊኒ ቢሳው፣ጋምብያ እና ጊኒ አምባሳደር ሆነው አገልግለዋል።በጅቡቲ አምባሳደርነታቸው ደግሞ የኢጋድ ተጠሪ ሆነው አገልግለዋል።ከእዚህ በተጨማሪ በፈረንሳይ አምባሳደርነታቸው ደግሞ የመንግሥታቱ ድርጅት የዩኔስኮ ዋና ተጠሪ ሆነው አገልግለዋል።በናይሮቢ ደግሞ የመንግሥታቱ ድርጅት ዋና ፀሐፊ ባንኪሙን ዋና መልክተኛ እና የቢሮ ኃላፊ ሆነው አገልግለዋል።

ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ላለፉት ሁለት ዓመታት ከፕሬዝዳንትነት ስራዎቻቸው በተጨማሪ የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ መታገዝ ባለበት ሁሉ እየተገኙ ክፍተቱን በመሙላት እየሰሩ ያሉት ተግባር ትልቅ ፍሬ እያፈራ ነው።በዲፕሎማሲው የረጅም ጊዜ ልምድ አላቸው የሚባሉት የግብፁ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሳማህ ሽኩሪ ከሀገር ሀገር እየዞሩ በኢትዮጵያ ላይ የዲፕሎማሲ ዘመቻ እንዲከፈት ያልረገጡት ምድር የለም።ከእነኝህ ሀገሮች ውስጥ የአፍሪካ ሀገሮች ተጠቃሽ ናቸው።ከእነኝህ ሀገሮች ውስጥ ታንዛንያ እና ኮንጎ ይጠቀሳሉ።በእዚህ በኩል ክብርት ፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ከኬንያ እስከ ዩጋንዳ፣ከደቡብ አፍሪካ እስከ ፈረንሳይ፣ሰሞኑን ደግሞ ከታንዛንያ እስከ ኮንጎ ድረስ ግብፅ ለመቆለፍ የሞከረችውን የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲ በአፍሪካ አንድ በአንድ እየፈቱት ነው።በእርግጥ በአፍሪካ አንፃር ቀድሞም ኢትዮጵያ በአፍሪካውያን ዘንድ ከፍ ያለ ከበሬታ አላት። ይህንን ከበሬታ ግን በአግባቡ ተረድቶ የሚያፋፍመው ጥበበኛ ዲፕሎማት ይፈልግ ነበር።ክብርት ፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ  ዘውዴ ሰሞኑን በታንዛንያ እና በኮንጎ ያደረጉት ጉብኝት ትልቅ ትኩረት በአፍሪካውያን ወጣቶች ዘንድ ሳይቀር ትኩረት እና ከበሬታ አግኝቷል።

ግብፅ የታንዛንያ እና ኮንጎን ድጋፍ ለማግኘት ስትጥር ሰንብታለች።በታንዛንያ ኢንቨስትመንት ዘርፍ ሲሆን ኮንጎን ደግሞ ከደቡብ አፍሪካ ቀጥላ ቀጣይ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር በመሆኗ ማባበሉ በዝቶ ነበር።የፈረንሳይኛ ተናጋሪ ክብርት ፕሬዝዳንት ሳሕለወርቅ ዘውዴ ዛሬ ኮንጎዎችን በፈረንሳይኛ እያናገሩ ከደረሱበት አንዱ ስምምነት ውስጥ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኮንጎ እንዲከፈት የሚለው ይገኝበታል።''ነቢይ በሀገሩ'' ሆኖ ነው እንጂ ክብርት ፕሬዝዳንቷ የሰሩት ዲፕሎማሲያዊ ጀብዱ ትልቅ ከበሬታ የሚያስገኝላቸው ነው።እናመሰግናለን! ክብርት ፕሬዝዳንት ልንላቸው ይገባል።

ከእዚህ በታች የምትመለከቱት ቪድዮ ክብርት ፕሬዝዳንት ሰሞኑን በታንዛያ ያደረጉት ጉብኝት የሚያሳይ ቪድዮ ነው።ቪድዮውን ያዘጋጀው ወጣት ታንዛንያዊ ነው።ምን ይህል በአፍሪካውያን ዘንድ በተስፋ እንደምንጠበቅ አስተማሪ ነው።


============
ማስታወቂያ 
============
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Monday, January 25, 2021

የፀጥታ ስጋት የነበረባቸው በሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር አዲስ አበባ ተመለሱ።አምባሳደሩ ከካርቱም ወደ ኢትዮጵያ በመኪና ለመግባት ጠይቀው ነበር።


በሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ
ጉዳያችን ዜና / Gudayachn News
  • የእስራኤል ደህንነት ሚኒስትር ኤሊ ኮህን (Eli Cohen) ዛሬ ሰኞ ካርቱም ነበሩ። 
በሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ በካርቱም የፀጥታ ስጋት እንደነበረባቸው እና ወደ ኢትዮጵያ በድንበር በኩል ለመግባት የሱዳንን መንግስት ጠይቀው እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።ሆኖም የሱዳን መንግስት በድንበር ውጥረቱ ምክንያት በመኪና ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን ለደህንነታቸው ጥሩ አለመሆኑን እንደገለጠላቸው የቱርኩን አናዶል ዜና ወኪልን ጠቅሶ ሚድል ኢስት ሞኒተር ዛሬ ማምሻውን ገልጧል።አምባሳደሩ በአሁኑ ጊዜ ወደ አዲስ አበባ በሰላም መብረራቸው እና መግባታቸው የሄው ምንጭ የፀጥታ ምንጮቹን መሰረት አድርጎ ገልጧል።

ዜናውን በተመለከተ የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር መስርያ ቤት ያለው ነገር የለም።የአምባሳደሩ ወደ ኢትዮጵያ መመለስ እና ካርቱም ለአምባሳደሩ የፀጥታ ስጋት መሆኗ በራሱ ጥያቄ ቢሆንም በሁለቱ ሀገሮች መካከል ያለው ግጭት በቶሎ እንዲፋጠን የሚፈልጉ የውጪ ኃይሎችም ሆኑ ከትግራይ ሸሽተው ካርቱም የሚገኙ የቀድሞው ህወሓት ቡድን ደጋፊዎች በአምባሳደሩ ላይ አንዳች ዓይነት ጥቃት ከመፈፀም እንደማይመለሱ መገመት ቀላል ነው።

ኢትዮጵያ የሱዳን የኢትዮጵያን ድንበር መውረር ምክንያት የሦስተኛ ሀገር እጅ እና በሱዳን በውስጥ ኃይሎች ፉክክር ጭምር የሚከናወን በመሆኑ ጉዳዩ በዲፕሎማሲ እንዲፈታ ጥረት አድርጋለች።ሆኖም ግን ይህ የኢትዮጵያ ትዕግስት አንድ ምሽት ላይ እንደሚያበቃ እና ድንገተኛ ማጥቃት ኢትዮጵያ ልትፈፅም እንደምትችል የብዙዎች ግምት ከመሆን አልፎ በሱዳናውያንም መሃል ከባድ  ፍርሃት ፈጥሯል።

ይህ በእንዲህ እያለ የእስራኤል ደህንነት ሚኒስትር በሱዳን ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ሰኞ ካርቱም መግባታቸው ተሰምቷል።ሚኒስትሩ ከሱዳን መከላከያ ሚኒስትር እና የደህንነት ሹሞች ጋር መነጋገራቸው ለማወቅ የተቻለ ሲሆን።የተነጋገሩበት ጉዳይ ግን ግልጥ አልተደረገም።ሆኖም ሀገሪቱ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ውጥረት በተመለከተ ሊሆን እንደሚችል ለመገመት ቀላል ነው።ሚኒስትሩ ዛሬ የአንድ ቀን ጉብኝት ካደርጉ በኃላ በተመሳሳይ ቀን ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን ለማወቅ ተችሏል።

===================
============
ማስታወቂያ 
============
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Sunday, January 24, 2021

ሰበር ዜና - በሱዳን ትናንት እና ዛሬ ከፍተኛ ተቃውሞ ሰልፍ ነበር።ሀገሪቱ አዲስ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ያሰጋታል

በካርቱም የእዚህ ሳምንት አመፅ መንገዶች በወጣቶቹ እንዲህ ተዘግቶ ነበር።
Photo = AFP

የጉዳያችን ልዩ ጥንቅር   
======================
በሱዳን ትናንት ቅዳሜ ጥር 15/2013 ዓም ከፍተኛ ተቃውሞ ሰልፍ ነበር።ሰልፈኞቹ በኦምዱርማን አል-አርባይን ጎዳና እና በርካታ ሰፈሮችን በመዘዋወር መንገዶችን ዘግተው ጎማዎችን አቃጥለዋል ፡፡በማዕከላዊ እና ደቡብ ካርቱም ሰሜን አቅራቢያ ባሉ አከባቢዎች ተመሳሳይ ተቃውሞዎች ተካሂደዋል ፡፡ሰልፈኞቹ በሽግግር መንግስቱ ኢኮኖሚያዊ ዕቅዶች ላይ መፈክሮችን በማሰማት በዳቦ እና በነዳጅ እጥረት የተነሳ ተቃውሟቸውን አሰምተዋል።መንግስት የዳቦ ዱቄት ላይ ድጎማ እያደረገ ቢሆንም ቀውሱ ከመባባሱ በላይ በደርዘን የሚቆጠሩ መጋገርያዎች መክሰራቸው እና ከገበያ ውጪ በመሆናቸው ንግዳቸውን ለመዝጋት መወሰናቸው ነው የተሰማው።

በእዚህ መሰረት የዳቦ መጋገሪያዎች ባለቤቶች  በድጎማ የሚገኘውን ዱቄት ተጠቅመው የሚጋግሩት ዳቦ  ከ 2 ፓውንድ በአንድ ዳቦ ወደ 5 ፓውንድ ለማሳደግ ጥያቄ አቅርበው ነበር ፡፡አመፁ በዛሬው ዕለትም የቀጠለ ሲሆን ፖሊስ አስለቃሽ ጭስ መርጨቱ ለማወቅ ተችሏል።በእዚህ ተቃውሞ የካርቱም ዋና የደም ስር የተሰኘውን 60ኛው ጎዳና ለትራፊክ ዝግ እንዲሆን ተገዶ ነበር።መንግስት በበኩሉ የሽያጭ ዋጋ በኪሎግራም ላይ የተመሠረተ እንዲሆን የሚወስን መስፈርት ለመቀየር መወሰኑ ነው የተሰማው፡፡መንግስት በሌላ በኩል በሬስቶራንቶችና በካፍቴሪያዎች ላይ ከተደረገ ሌላ ዘመቻ በተጨማሪ ክብደቱን በትክክል መያዙን ለማረጋገጥ በመዲናዋ መጋገሪያዎች ላይ የክትትል ዘመቻዎች እንደሚያደረግ አስታውቋል፡፡

በሚያዝያ 2020 (እ.ኤ.አ.) የካርቱም መንግስት  በድጎማ የሚገኘውን የዳቦ ዋጋ ከ 1 ፓውንድ በአንድ ዳቦ ወደ 2 ፓውንድ ከፍ ማድረጉ ይታወሳል ፡፡ምንም እንኳን አንዳንድ ጠንካራ ኢኮኖሚያዊ እርምጃዎች የወሰደ ቢሆንም የአሁኑ የሱዳን የሽግግር መንግስት የግል ዳቦ ጋጋሪዎች የሚጠቀሙባቸውን ዱቄት ለጋጋሪዎች በቅናሽ ዋጋ እንዲደርስ አሁንም ድጎማ እያደረገ ነው፡፡ ይህም ሆኖ ግን መንግስት በመሃል የሚገኙ አቀባባዮች የሚሄዱበትን የሙስና መንገድ መዝጋት እንዳልቻለ ነው የሚነገረው።ይህ በእንዲህ እያለ በሱዳን በአሁኑ ጊዜ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ እጥረት መኖሩ ነው እየተነገረ ያለው። በእዚህ ምክንያት ሀገሪቱ ከውጭ የምታስመጣቸው እቃዎች ላይ የራሱን ተፅኖ ፈጥሯል።አንድ የሁለተኛ ደረጃ ዩኒፎርም የለበሰ ወጣት ለዴይል ሜል በሰጠው ቃል በትምህርት ቤት ለቁርስ የሚሆን ዳቦ ማግኘት አልቻልንም ብሏል።

በ2019 ዓም እኤአ በዳቦ ዋጋ የተነሳው ተቃውሞ ኦማር አልበሽር ከስልጣን እስከመውረድ አድርሶ እንደነበር ይታወሳል።አሁን ደግሞ የኮሮና ቫይረስ ባለበት ረጅም የዳቦ ሰልፍ ለሰዓታት መቆም ከመብራት መቆራረጥ ጋር ተደምሮ ለሕዝቡ ትልቅ የራስ ምታት ሆኗል።60 ቢልዮን ዶላር ዕዳ ያለባት ሀገር ባለፈው ወር ብቻ የዋጋ ግሽበቷ 269 በመቶ በላይ መድረሱ ሀገሪቱ ወደ ከፍተኛ ቀውስ እየመራት ነው።ይህ በእንዲህ እያለ በቅርቡ የአሜሪካ ግምጃ ቤት ፀሐፊ ስቴቨን ምኑቺን ወደ አንድ ቢልዮን ዶላር ውዝፍ እዳ ከዓለም ባንክ ለማቅለል አንድ ዓይነት የመግባቢያ ሰነድ መፈራረሟ እና ከአሜሪካ አስመጪ እና ላኪ ባንክ ጋር ሌላ የአንድ ቢልዮን ዶላር ስምምነት መፈራረሟ ለማወቅ ተችሏል።በሌላ በኩል የጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ መንግስት አሜሪካ ለረጅም ጊዜ በሱዳን ላይ ጥላው የነበረው ሱዳንን በጥቁር መዝገብ ውስጥ ያስገባው እቀባ መነሳቱ ለሱዳን ምጣኔ ሀብት መነቃቃት ይፈጥራል ተብሎ ተጠብቆ ነበር።

በሌላው የሱዳን ክፍል ዳርፉር በእዚህ ሳምንት ውስጥ በተከሰተ አዲስ ግጭት 10 ሕፃናትን ጨምሮ 250 ሰው መገደሉ ተሰምቷል።በእዚሁ ግጭት 100 ሺህ ሰው ከቤቱ የተፈናቀለ ሲሆን ከ3 ሺህ በላይ የሚሆኑት ወደ ምስራቃዊ ቻድ መሰደዳቸውን የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ኮሚሽን መረጃ ያሳያል።የዳርፉር ግጭት በያዝነው አዲስ ሚሊንየም መጀመርያ ዓመቶች ላይ ከተጀመረ ወዲህ ከ300ሺህ በላይ ሕይወት የቀጠፈ ሲሆን ወደ 2 ነጥብ 5 ሚልዮን ሕዝብ ደግሞ ተፈናቅሏል።

በሱዳን በአሁኑ ጊዜ በተከፋፈለው የጦር ኃይሉ እና በሽግግሩ መንግስት መሃል ያለው ልዩነት ከምንጊዜውም በላይ እያፈጠጠ ነው። የጦር ኃይሉ በራሱ መንገድ የመሄዱ አንዱ ማሳያ የኢትዮጵያን ድንበር መጣሱን የሽግግር መንግስቱ ባለስልጣናት ባይደግፉትም ጦሩ ግን በራሱ መንገድ ሄዷል።አሁን በሱዳን እየሆነ ያለውን አጠቃላይ ሂደት ላይ ሃሳባቸውን እንዲሰጡ ጉዳያችን የጠየቀቻቸው የሱዳን ምሑር ሁለት ስጋት እንዳለባቸው ገልጠዋል።አንደኛው ወገን ለውጡ እራሱ የመጣው አልበሽርን ገለል አድርጎ ሱዳን በአሜሪካ የተጫነበትን ዕቀባ ማስቀረት እና መልሶ የአልበሽር ደጋፊዎች በወታደራዊ መፈንቅል ተመልሰው ወደ ስልጣን እንዲመጡ የማድረግ ዕቅድ ቀድሞውንም ተይዟል የሚሉ ሲሆን።ሌላው ወገን ደግሞ የጦር ኃይሉ መኮንኖች በመካከለኛው ምስራቅ ባላንጣ ሀገሮች አንፃር ስለተቀራመቷቸው በእነኝህ ሀገሮች ሴራም አንፃር በሱዳን አሁን ያለውን የሽግግር መንግስት ለመፈንቀል እንቅስቃሴ እንደሚኖር ጥርጣሬ አላቸው።

ለማጠቃለል ሱዳን በቀውስ ውስጥ የምትንገዳገድ ሀገር ሆናለች።በውስጥ ያለው ቅራኔ በመካከለኛው ምስራቅ የገመድ ጉተታ ውስጥ የጦር ሹማምንቶቿ ገብተዋል።የሽግግር መንግስቱ ደግሞ የምጣኔ ሃብቱን ማረጋጋት አለመቻሉ ብቻ ሳይሆን የዳርፉር ችግር ከማጡ ወደ ድጡ እየሄደ ነው።ይህ በእንዲህ እያለ ሀገሪቱ አሁን ከሚታየው በላይ በግብፅም ሆነ በሌላ የውጭ ኃይል የበለጠ የምትዘወር ሀገር ሆና መቅረቧ ያልተረጋጋ የውጪ ፖሊሲ መኖር ብቻ ሳይሆን፣ከቀልቧ ጋር ያልሆነች ምድር ብትሆን ሊደንቅ አይገባም። የሱዳን ዓይነት አጀንዳ የተሸከመ ሀገር ጠባይ ከእዚህ ያነሰ ሊሆን አይችልም።ከእዚህ ሁሉ ጋር አሁን ያለው የሽግግር መንግስት እየሰከነ መጥቶ የጦር ኃይሉን ከነውጠኛ መኮንኖች አፅድቶ በእዚህ ዓመት ይደረጋል የሚባለው ምርጫ ከተሰካ ሱዳን ወደ አዲስ ዘመን እየተሸጋገረች ነው ማለት ነው።የሱዳን በእዚህ መልክ መረጋጋት ወጥ የሆነ የውጭ ፖሊሲ በተለይ ከምስራቃዊ ጎረቤቶቿ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጋር የሰከነ ግንኙነት እንዲኖራት ያደርጋታል።ከሁሉም በላይ በዓባይ ግድብ ላይ የምታነሳውን በራሷ ጥቅም ላይ የመቆም አባዜ በተላቀቀች ነበር።ሱዳንን ከመፈንቅለ መንግስት ይሰውራት? ወይንስ አይሰውራት? ጥያቄ ነው።ለኢትዮጵያ የሽግግር መንግስቱ ቢረጋጋ እና የጦር መኮንኖቹን ቢቆጣጠር የተሻለ የሚሆን ይመስላል።አሁን የጦር መሪዎቹ የሽግግር መንግስቱን በመናቅ በራሳቸው የሚቦርቁባት ሀገር ሆናለች።እነኝህ መኮንኖች ወደ ስልጣን ቢመጡ ከጥቅሙ ጉዳቱ ለአፍሪካ ቀንድ አይተርፍም ማለት አይቻልም።ምክንያት - ከአሁኑ በባሰ በውጭ ኃይሎች የምትዘወር ምድር መሆኗ ሊብስ ይችላል።
=================


Wednesday, January 20, 2021

Western media’s federal govt bias in coverage of Tigray conflict


By Getachew Melaku

  • Much of the comments on western media both about TPLF and the federal government exhibit a significant bias, partisanship, and downright inaccuracies.

The all-out conflict between the federal government and the Tigray regional state administration has given us an occasion to reflect on biases and blinkers that surface in the practice of journalism. The military campaign that started on 4 November after forces from the Tigray People Liberation Front (TPLF) attacked the federal army’s Northern Command has deservedly received a great deal of attention. There has been extensive media coverage of the military clashes, including aerial bombardments and attacks directed against civilians and the displacement of civilians. However, much of the comments on western media both about TPLF and the federal government exhibit a significant bias, partisanship, and downright inaccuracies. Journalists writing on the issue have exaggerated at best, invented at worst, to denigrate the federal government, while going to great lengths to cast its opponent TPLF in a positive light.

The standard line used by the Western media such as Reuters, BBC, VOA, DW was that “Prime Minister Abiy Ahmed, Africa’s youngest leader and the recipient of a 2019 Nobel Peace Prize, launched a military offensive against his own people in the Tigray region”, in a typically clear-cut ‘good-versus-evil’ frame. The ‘evil’ side personified in a single figure of Abiy Ahmed. “His country is – at the very least – on the verge of civil war. Why has he chosen military force to resolve his dispute with Tigray?” asked Andrew Mueller of The Foreign Desk, the current affairs program on online radio station Monocle 24. This would have been a fair question had the Tigray leadership had been an innocent player and an irreproachable body. Disengaging the events from the broader issues relative to the conflict and disregarding the provocations TPLF has been mounting against the federal government for the past two years, the western media chose to focus on the PM, taking the liberty to label and demonize him as “the Nobel Peace Prize Winner turned Belligerent Warmaker”, while representing TPLF as an innocent victim, often in an insidious way.

The steps TPLF has been taking to sabotage Prime Minister Abiy Ahmed’s rule in ways that harm the economy and the transition process has been overlooked by the media, even though a cursory look around suggests that. At least, that claim by the federal administration of justifying the offensive as the struggle to counter the continuing sabotage should have got fair coverage. However, the journalists, for some reasons, chose to reflect only TPLF’s storyline, unwittingly reinvigorated by so-called scholars who have picked up “facts” that were actually not facts to being with.

Most of the media glossed over the causes for the long-standing and simmering tensions between the federal government and TPLF that came with the coming of Abiy Ahmed.  The so-called analysts have used an overblown piece of rhetoric to describe the situation in the country, not even bothering to show a semblance of neutrality and non-partisanship. “We are not on the brink of civil war, Ethiopia is in the midst of a civil war,” said Kjetil Tronvoll, head of the think tank Oslo Analytica and professor of peace and conflict studies at Bjørknes University in Oslo, Norway.

The Norwegian scholar who never cared to hide his blatantly pro-TPLF position has been interviewed as much as once a week about his predictions. He told, for example, VOA that “The conflict between the federal authorities and TPLF might be the straw which breaks the camel’s back.”  “You have the potential of a serious, serious weakening of central authorities in Ethiopia. It is an extremely dire situation and I think it is very hard to see that things will return back to normality as it was before the conflict. The divisions are running too deep for that.”

The observation, limited and flawed though it is, are cited by many media houses. The whole country falling into civil war disregarded facts in favor of hyperbole. So much so that, the US ambassador to Ethiopia Michael Raynor responded by saying that, “the rest of the country actually remains quite calm at present; no indications of anyone taking up comparable actions elsewhere, and in fact the opposite”.

But the western media was not only attempting to make the Prime Minister look like a villain who single-handedly provoked the conflict. But also they have been paying homage to the battle-hardened TPLF leaders and forecasting victory for the group, by selecting sources, angling, and using the narrative devices of frames. Borrowing similar words from each other, they talked about TPLF’s rich experience in the battle that could guarantee a more apparent victorious outcome for TPLF. For instance, Reuter’s East Africa deputy bureau chief, Maggie Fick, who signed a piece “Battle-hardy Tigray back in spotlight as Ethiopia conflict flares”, made a large number of claims that run counter to the situation on the ground. She cited “Ethiopia expert” Alex de Waal as saying that Abiy may have underestimated the Tigray leaders’ skills at both politics and war. “The Tufts University academic recalled the words of Tsadkan Gebretensae, a Tigrayan who once commanded Ethiopia’s army against Eritrea, in a conversation with him: “War is primarily an intellectual activity,” she wrote.

Mary Harper, BBC’s Africa Editor spoke at length with Monocle’s The Foreign Desk, saying that “the Tigrayans don’t make up a big percentage of the Ethiopian population, but when you think about the war that they fought in the 1980s and early 90s to dislodge the former dictatorial ruler Mengistu Hailemariam, they are a group of people who are battle-hardened, they are used to fighting. Given the fact that they also dominated the government from 1991 until the rise of Abiy Ahmed in 2018, they have military resources, they have military know-how, the old generation is part of military culture, they are going to be a match for the forces of the federal government in terms of their battle-hardened mentality. They are not going to be an easy force to deal with.”

The celebrated London-based business daily, Financial Times, even headlined one of its articles, “Tigray crisis: ‘They know how to fight and they can do it ’til the end.’” The quote was ascribed to certain Samahagn Genet, a former soldier who, aged 17, handled bombs in the Ethiopian army during the war with Eritrea.

Of course, subsequent events have shown that those predictions were way off the mark. The TPLF leadership was far from the invisible force portrayed by the journalists, as the federal forces had defeated the group, seizing major Tigrayan cities including Mekelle in a short span of time. The TPLF forces were in defeat and disarray on the battlefield, even though to this day the journalists and so-called analysts continue to spin it by claiming that the TPLF leaders returned to the mountains to launch a guerrilla war against the federal government.

Incidents like this of course would strengthen the already existing prevalent doubts about the accuracy of the Western press among Ethiopians about their own country, as was it described by a Twitter user, Biruk Terrefe who said that “the grotesquely simplified, misinformed, partial outputs by reputable media outlets and armchair analysts/”experts”, makes me question everything I thought I knew about other spaces/conflicts/countries”.

What has become clear from this incidence is that how media organizations, even well-intentioned some of them could be, could take sides in the complex conflict and, in some cases, encourage even greater polarisation in the country’s political system. Eager to defend the “underdog”, reporting has begun to be conflated with opposition to the ruling regime, and not represent its views and the facts as seen from it. Nicole Stremlau in her book, Media, Conflict, and the State in Africa says that those journalists that present the strongest opposition pieces in the media are often held up by international organizations as the bearers of democracy and many have become adept at manipulating the organizations and gaining undeserving support. “The discourse of human rights advocacy groups has been adopted and reinterpreted by many journalists, yet in practice, only some share their priorities. Along with listening in on less obvious spaces, a more nuanced understanding of the complex roles journalists have in the nation-building process rather than what is normally defined for them is required,” Nicole writes.

But this also emphasizes how important it is for Ethiopians to have their own media in the battle to tell their own stories accurately and reappropriate their own public sphere. There is a need to establish and support local media institutions to disseminate news about events affecting the country and counteract biased and stereotypes prevalent in the western press. Above all, the government should lift the repressive political situation for the public to have serious internal debate and criticism. And also there is a need to invest in media literacy to combat misinformation and myths which confuse and mislead public debate.

This article is published under a Creative Commons Attribution-NonCommercial 4.0 International licence. Please cite Ethiopia Observer prominently and link clearly to the original article if you republish. If you have any queries, please contact us at ethiopiaobserver@protonmail.com. Check individual images for licensing details.

Thursday, January 14, 2021

ኦነግ ሸኔ በመተከል ቢሮ ከፍቶ እየሰራ መሆኑ ተነገረ።የመተከል እልቂት አሁንም መፍትሄ አላገኘም።




የቤንሻንጉል ክልል ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቶማስ በሕዝቡ ላይ እየደረሰ ስላለው መከራ ምን እያደረጉ ነው?

ባለፈው ዓመት የካቲት/2012 ዓም  አዲስ አበባ የሚገኘው ኢትዮ ኤፍ ኤም በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል መከላከል ዘርፍ ም/ል ኮሚሽነር ነጋ ጃራን ጠቅሶ የኦነግ ሸኔ የታጠቁ አካላት ወደ ክልሉ ገብተው ንብረት አቃጥለው እና ዘርፈው ሸሽተዋል ብለዋል።ዜናው አክሎም  ድርጊቱ የተፈጠረው ጥር 25 ቀን 2012 ዓ.ም በአሶሳ ዞን ውስጥ ባባሲ ወረዳ ውሽማ ጥርጊጊ የሚባል ቀበሌ ላይ ቁጥር 1 እና ቁጥር 2 የሚባሉ ቦታዎች ነው ይላል።ከዚህ በፊትም ይላል ዘገባው በዚህ ቀበሌ ይኖሩ የነበሩ 4 ሰዎች አካባቢውን ለቀው የሄዱና በኋላም የኦነግ ሸኔ ቡድን የተቀላቀሉ ነበሩ፡፡የኋላ ኋላ እነርሱን ጨምሮ ወደ 28 የሚደርሱ የታጠቁ ሀይሎች በ25/5/2012 ዓ.ም ወደ ቀበሌው መጥተው የቀድሞውን የቀበሌ ሊቀ መንበር አቶ አደም ጉምዛ የተባለውን ግለሰብ ያገኙታል፡፡እኚህን የቀድሞ ሊቀመንበር ባገኙ ሰዓት በወቅቱ የነበራቸው ፍላጎት የጦር መሳሪያና ከዚህ በፊት የተሰበሰበ ግብር አለ እርሱን ማምጣት አለብህ ብለው በጠየቋቸው ሰዓት ምንም እንደሌለ በመንገር ይመልሷቸዋል፡፡በኋላም የዚህን ሰውዬ 6 ቤቶች አቃጥለው 3 ኩንታል ቦሎቄ ፤ ሁለት ኩንታል ጤፍ 1 ኩንታል ጥቁር አዝሙድ ግማሽ ኩንታል ተልባና ሁለት ኩንታል ኑግ በሳት ማቃጠላቸው ተገልጿል።በዛው ቀበሌ ውስጥ ያገኙትን የኢትዮጵያና የክልሉን ሰንደቅ አላማ በማቃጠል ከሚኒሻዎችና ከግለሰቦች ላይ መሣርያዎች ነጥቀው አመለጡ ይላል አምና የተለቀቀው ዜና።

ይህ ዜና ከተዘገበ አንድ ዓመት ሊሆነው ቀናት ነው የቀሩት።ዜናው ግን በቤንሻንጉል ጉሙዝ እየተፈፀመ ያለ የፍጅት ተግባር እንጂ የኦነግ ሸኔ ተግባር ብዙም አይነገረም።ኦነግ ሸኔን በተመለከተ እስካሁን በኦሮምያ ክልል የሚነገረው ይህንን ያህል የኦነግ ሸኔ ጀሌ ተገደለ ወይንም የእዚህ አካባቢ ሕዝብ ኦነግ ሸኔን ተቃውሞ ሰልፍ ወጣ የሚል ነው።ብዙዎች ተገደሉ የሚባለው የኦነግ ሸኔ ቁጥር ላይ ጥርጣሬያቸውን ይገልጣሉ።ለእዚህ ጥርጣሬያቸው መነሻ የሚያደርጉት የኦነግ ሸኔ ሰዎች እራሱ ብልጥግና  ኦሮምያ ውስጥ አሉ የሚል ነው።

ይህ በእንዲህ እያለ ዛሬ ጥር 6/2013 ዓም መቀመጫውን በአሜሪካ ያደረገው የአደባባይ ሚድያ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ባደረገው ውይይት ላይ የመተከልን የሰሞኑን በጉሙዝ አሸባሪዎች የተፈፀመውን እልቂት እና የህዝብ መፈናቀል አስመልክቶ ክልሉን በሚገባ ከሚያውቁ ከመምህር አበራ ጋር በቀጥታ የቪድዮ ውይይት ላይ በክልሉ ነዋሪ በሆኑ የአማራ፣ኦሮሞ፣ሽናሻ እና አገው ላይ የደረሰው ጥቃት ያስከተለው አሰቃቂ እልቂት እና ሰብዓዊ ቀውስ አስመልክተው ልብ በሚነካ መልኩ አብራርተዋል።መምህር አበራ የቤንሻንጉል ክልልን በሚገባ እንደሚያውቁት በሥራ ዓለምም ሆነ በቅርቡ ከሳምንት በፊት ወደ ክልሉ ሄደው እንደመጡ እና የተመለከቱት ሁኔታ ሁሉ እጅግ እንዳሳዘናቸው ሲገልጡ  ከስልሳ በላይ አስከሬን በመኪና እየተጫነ መራገፉ፣በሺህ የሚቆጠር ሕዝብ በብርድ ካለምንም መጠለያ እና አንድም የክልሉ መንግስት መጠየቅ ሜዳ ላይ እንደወደቁ እና አንዲት እናት ሜዳ ላይ መውለዷን ሁሉ በሚያሳዝን አገላለጥ አብራርተዋል።ከእዚህ በመቀጠል መምህር አበራ  የኦነግ ሸኔ ፅህፈት ቤት መተከል ውስጥ መኖሩን እና ይህንንም ለሚመለከተው የመንግስት አካል በተደጋጋሚ ማመልከታቸውን ገልጠዋል። 

በመጨረሻም በእዚሁ ውይይት ላይ መምህር አበራ የክልሉ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን ጥፋት መንግስት ተገቢውን ሕግ የማስከበር ተግባሩን እንዲያከናውን መጮህ ብቻ ሳይሆን ወደተሰደዱት ወርደው ማፅናናት ይገባቸው እንደነበር የጠቀሷቸው የክልሉ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቶማስ ናቸው።መምህር አበራ ሊቀ ጳጳሱ በክልሉ ሕዝብ ላይ ለሚደርሰው እልቂት እና ስደት ድምፃቸውን አለማሰማታቸው አሳዛኝ መሆኑን አምርረው ተናግረዋል። 

በቤንሻንጉል፣መተከል  በቡለን ወረዳ በኩጅ ቀበሌ ከሶስት ሳምንት በፊት ማንነትን መሰረት ባደረገ በአራት አቅጣጫ በታጠቁ ኃይሎች በደረሰ ጥቃት  222 ኢትዮጵያውያን ከዓማራ፣ሽናሻ፣አገው እና ኦሮሞ ተወላጆች በአሰቃቂ ደረጃ ህይወታቸውን ማጣታቸው ይታወሳል።ግድያው በክልሉ ልዩ ኃይል ጭምር መከናወኑን የአይን ምስክሮች መግለጣቸው እና በግድያው ላይ አንድ አባት ዘጠኝ ልጆቻቸውን ካጡት ጀምሮ በአንድ ቤተሰብ እስከ 12 የሚደርሱ የቤተሰብ አባላት መገደላቸው እና የሞቱትን አስከሬን በግሬደር ተግዘው በጅምላ መቀበራቸው ይታወሳል።እዚህ ግድያ በኃላ  የቤንሻንጉል ክልል የፀጥታ ጉዳይ በጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ የሚመራ በአንድ ግብረ ኃይል መመራት መጀመሩ ይታወቃል።ሆኖም ግን ይህ ግብረ ኃይል ሥራ ከጀመረ በኃላ ነው የእዚህ ሳምንቱ ጥቃት  በንፁሃን ላይ የተፈፀመው።አንዳንድ የኦነግ ሸኔ ደጋፊዎች በኦሮምያ ብልጥግና ውስጥ በሕቡ እየሰሩ መሆናቸውን የሚያወሱ  ወገኖች የቤንሻንጉል ክልልም ተመሳሳይ የሎጀስቲክም ሆነ የሽፋን ድጋፍ እያገኘ እንደሆነ እና በክልሉ የሚደርሱት እልቂቶች የእዚሁ በሕቡዕ በኦሮምያ በልጥግና ውስጥ በተሸሸገው የመንግስት መዋቅር አይዞህ ባይነት ነው በማለት ይከራከራሉ። 

በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን እና የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ጉባኤ በጋራ በእዚህ ሳምንቱ የቤንሻንጉል ክልል የመተከል ዞን ጥቃት አንድ መቶ ሰዎች ሕይወት መቀጠፉን መግለጣቸውን እና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) በመተከል የደረሰውን የንፁሃን ደም መፍሰስ ማውገዙን የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥን በዛሬው የምሽት ዜና እወጃው ላይ ገልጧል።
===============
============
ማስታወቂያ 
============
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Monday, January 11, 2021

ለሁለት ወራት የሚቆይ ኢትዮጵያን እና የኢትዮጵያ የሆኑትን መልካም ነገሮች ሁሉ ለቀሪው ዓለም የማጉላት (Rising Ethiopia) የዲጂታል ዘመቻ ተጀምሯል።ኢትዮጵያውያን በያሉበት መተባበር አለባቸው።



ከስር የዘመቻው ትውተር፣ዩቱብ እና ፌስ ቡክ ሊንኮች እንዲሁም  የሦስት ወራት ፕሮግራም ያገኛሉ።
ማሳሰቢያ - ይህ ዜና ተጨማሪ መረጃዎች (updates) አሁን ተካተውበታል።

በእንግሊዝ ሀገር ነዋሪ በሆኑት ዶ/ር በላቸው ጨከነ ተስፋ በተባሉ ኢትዮጵያዊ ሃሳብ አፍላቂነት እና አስተባባሪነት ፣በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ ባሕል እና ቱሪዝም ዕውቅና የተጀመረው የኢትዮጵያን ስም ለቀረው ዓለም የማጉላት (Rising Ethiopia) ዘመቻ የተጀመረው ባለፈው እኤአ ዴሴምበር 30 ሲሆን እስከ መጪው እስከ የካቲት 21/2021 ዓም እኤአ የሚቆይ ዘመቻ ነው።በዘመቻው የዌብነር መክፈቻ ስነ ስርዓቱ ላይ ክብርት / ጽዮን ተክሉ በኢትዮጵያ በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር  የዲያስፖራ እና ኢኮኖሚ ዲፒሎማሲ ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ፣ክቡር  አምባሳደር ተፊሪ መለሰ በዩኬ እና አይርላንድ  የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር፣ክብሩ አቶ ስለሺ ግርማ የቱሪዝም ኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስክያጅ እና የኢትዮጵያ ባሕል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር ከፍተኛ አማካሪ፣መቀመጫቸውን በአፍሪካ እና እስያ ያደረጉ የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች፣የቱሪዝም እና አስጎብኚ ድርጅት ባለቤቶች እና ሌሎች ከ100 በላይ ተሳታፊዎች የተገኙ ሲሆን በእዚሁ መክፈቻ መርሃግብር ላይ የመርሃግብሩ ሃሳብ አመንጪ እና አስተባባሪ ዶ/ር በላቸው ጨከነ ተስፋ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ እምቅ የሆነ  የቱሪዝም መዳረሻ፣ የኢንቨስትመንት አማርጫ፣ የተማረ የሰው ሃይል ሀብት በሀገረ  ውስጥ እና 3.5 ሚሊዮን በላይ የሚገመት ኢትዮጵያዊ እና ትውልደ ኢትዮጵያው በመላው ዓለም ያላት ሀገር መሆኗን አብራርተዋል።

ዶ/ር በላቸው ጨከነ በእዚሁ ንግግራቸው በተጨማሪም የዘመቻው ዋና ዓላማ በኢትዮጵያ የሚገኘውን  ይህን ሀብት በውጪ የሚገኘውን ኢትዮጵያው እና ትውለድ ኢትይጵያዊ በመጠቀም ለዓለም ለማሳውቅ እና በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እደገት ጉልህ ድርሻ እንዲኖረው ያለመ መሆኑንና ከኢትዮጵያ ውጪ ያሉ የንግድ ድርጅቶችን በየአካባቢያቸው  በማስተዋወቅ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ አቅማቸውን ማጠናከረም ዘመቻው አካል መሆኑን አብራርተዋል።በመቀጠልም ዶ/ር በላቸው ኢትዮያን የማጉላት ዘመቻው አራት ዋና ዋና ክፍሎችን የያዘ መሆኑን ገልጠዋል።እነርሱም -

በመጀመሪያው ክፍል ማለትም ከታህሳስ 21(Dec 30) - ጥር 14(Jan 24)  እምቅ የኢትዮጵያን የቱሪዝም  መዳረሻነት እና ድንቅ የሆነውን ባህላችን  የምናስተዋውቅበት ጊዜ ሲሆን  በእነዚህ ሶስት ሳምንታት የኢትዮጵያ ታሪካዊ ቦታዎች፣ መንፈሳዊ በዓላት፣ ወንዞች እና ሐይቆች፣ ተራሮች፣ የዱር እንሰሳት፣ ሙዚየሞች፣ ኪነ ጥበባችን፣ አለባበሳችን እና አመጋገባችንን ለዓለም በማሕበራዊ ሚድያዎች በሰፈው የምናስተዋውቅበት ይሆናል በእነዚህ ሳምንታት ኢትዮጵያዊያን የባህል ልብሳቸውን እንደአመቺነቱ በሥራ ቦታቸው ለአንድ ቀን በመልበስ እና ፎቶአቸውን በማጋራት፣   ትናንሽ ስጦታዎችን ለሌው ማህብረሰብ በመሰጠት ኢትዮጵያን በቀላሉ የሚያስተዋውቁበት ነው። በዚህ ሳምንት የኢትዮጵያ አየር መንገድም በሰፊው ይተዋወቃል። ኢትዮጵያ የጎብኚዎች አማርጭ እንድትሆነ በሰፈው ይሰራል።


በሁለተኛ  ክፍል  ከጥር 15 (25 Jan) - ጥር 22 (31 Jan) ድረስ  ከኢትዮጵያ ውጪ በየሀገሩ ያሉ የንግድ ድርጅቶችን በየአካባባያቸው ባሉ ኢትዮጵያዊያን የሚተዋወቁበት ሳምንት ነው ይሄውም ኢትዮጵያዊን በዓለም አቀፍ ደረጃ በያሉበት ብቁ እና ተወዳዳሪ ድርጅቶች እንዲኖራቸው ያግዛል  


የኢትዮጵያዊያን ተወዳዳሪ መሆን ወደ ሀገር ቤትም ኢንቨስት ለማደረግ እና ከኢትዮጵያ ወደ ውጪ ለመላክ (Export) ትልቅ አቅም ይፈጥራል።  በዚህ ሳምንት ኢትዮጵያዊያን በየአሉበት ሀገር የሚያውቃቸውን  የኢትዮጵያውን የሒሳብ አማካሪዎች፣ ሱቆች፣ የሕግ ባለሞያዎች፤ ምግብ ቤቶች፣  የኢንፎርሚሸን ቴክኖሎጂ ተቋማት፣ ኮሌጆች፣ የመኪና መሸጫዎች፣ የሕክምና ተቅዋማት  አድራሻ እና ስለአገልግሎታቸው  በማኅበራዊ ሚድያ ይተዋወቃል።


ሶስተኛው ክፍል ከጥር 23 (Feb 1 ) - ይካቲት 7 (Feb 14) የኢትዮጵያ እንቨስትመንት ሳምንት ነው። በዚህ ሳምንት የኢትዮጵያን እምቅ የእንቨስትመንት አቅም በኢንዱስትሪው፣ በእርሻ በኃይል አቅርቦት፣ በማዕድን ፍለጋ ዙርያ የሚተዋውቅበት ነው። በኤምባሲዎች በኩል ውይይቶችን፣ በኢንቨስትመንት ቢሮ በኩል ደግሞ የኢንቨስትመንት አማራጮችን የሚያሳዩ ዶክምነትሪዎች ለሌሎች እንዲጋሩ ይደረጋል በኢትዮጵያም እስካሁን ኢንቨስት ያደርጉ በጎ ልምዳቸውን እንዲያጋሩ ይደረጋል። የታወቁ ኢትዮጵያዊያን  የኢንቨስት አማራጮቻችንን እንዲያስተዋውቁ ይሆናል።


የመጨረሻው እና አራተኛው ክፍል ከየካቲት 8 (Feb 15) - የካቲት 14 (Feb 21) የመስጠት ሳምንት (Giving weeks) ነው - በዚህ ሳምንት ኢትዮጵያውያን በእያሉበት በኢትዮጵያ ለሚከናወኑ መልካም ፕሮጀክቶች ማለትም  ሕዳሴ ግድብ፣ ኮቪድን ለመከላከል፣ ለበጎ አድራጊ ድርጅቶች  እና ለሌላም ፕሮጀችክቶች የገንዘብ ደጋፍ የሚያደርጉበት እና ለኢትዮጵያ የሚጠቅሙ መልካም ግንኙነቶችን የሚፈጥሩበት ሳምንት እንደሚሆን ዶ/ር በላቸው አብራርተዋል።


የኢትዮጵያን ስም ለማጠልሸት የውጭ ሚድያዎች ሳይቀሩ በተረባረቡበት በእዚህ ጊዜ፣ በሀገር ውስጥም ሆነ በመላው ዓለም የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ይህንን ዘመቻ በትዊተር፣በፌስ ቡክ፣ዩቱብ እና ሌሎችም መንገዶች ሁሉ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ሊያደርጉ ይገባል። 

ከእዚህ በታች የዘመቻው ትውተር፣ዩቱብ፣ፌስ ቡክ ሊንኮች እና የሦስት ወሮች ፕሮግራም ያግኙ።

የትውተር ሊንክ = https://twitter.com/RisingEthiopia  

የፌስ ቡክ ሊንክ= https://www.facebook.com/RisingEthiopia1/


የዘመቻው የሦስት ወሮች ፕሮግራም 

============
ማስታወቂያ 
============
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ -