ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Saturday, August 29, 2020

የትምህርት ሚኒስቴር ላለፉት 27 ዓመታት በተሳሳተ ሥርዓተ ትምህርት ኢትዮጵያን እንደከፋፈለ ዳግም እንዲከፋፍል ሊፈቀድለት አይገባም።

የትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስርያ ቤት በቀዳማዊ አፄ ሃይለስላሴ ዘመን (1950ዎቹ መጨረሻ) አዲስ አበባ ልዩ ስሙ አራት ኪሎ ግንባታ ላይ ሳለ 

ኢትዮጵያ የኅብረብሔር ሀገር ነች።በዘመናት ሂደት ህዝቧ ከሰሜን ደቡብ፣ከምዕራብ እስከ ምስራቅ በንግድ፣በጦርነት፣በስደት፣በተፈጥሮ አደጋ እና በሌሎች ምክንያቶችም እየተንቀሳቀሱ እርስ በርስ ተዛምደዋል፣ተዋልደዋል።ይህ በታሪካችን የነበረ ዕውነታ ነው።በምሳሌነት የዝዋይ ደሴት ነዋሪዎችን ብንመለከት ከላይ የተጠቀሰው የህዝብ የአኗኗር ታሪክ አንዱ ማሳያ ነው።በዘጠነኛው ክ/ዘመን የተነሳችው እና አያሌ አብያተ ክርስቲያናትን ያቃጠለችው ዮዲት ጉዲትን ሸሽተው ታቦተ ፅዮንን ይዘው የተሰደዱት ካህናት እና አብሯቸው ከተለያየ የኢትዮጵያ ክፍል የመጣው ሕዝብ በዝዋይ ደሴት ሰፍሮ ነበር።ታቦተ ፅዮን ስትመለስም ከመላው ኢትዮጵያ የመጣው ሕዝብ ግማሹ ስመለስ ሌላው እስካሁን ዝዋይ ደሴት ቀርቷል።በእዚህም መሰረት በዝዋይ ደሴት ከሁሉም የኢትዮጵያ ክፍል የተውጣጡ ቃላት በአንድነት የፈጠሩት ዘዬ የተሰኘ መግባብያ ፈጥረው ይኖራሉ።በመሆኑም የዘዬ ሰዎች ዛሬም ሲናገሩ ከጉራግኛ፣ከአማርኛ፣ከትግርኛ እና ከሌሎችም የተቀየጡ ቃላት መስማት የተለመደ ነው።

ኢትዮጵያ እንዲህ ነች።እርስ በርሷ የተጋመደች፣የተዛመደች እና የተጣመረች ነች።ይህ ሁኔታ የአንዱ ስልጣኔ የተለየ፣የሌላው ዝቅ ያለ ብሎ መውሰድ የሚቻልበት ሁኔታ የለም።በእያንዳንዱ የኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ያለፈው የህዝቡ ታሪክ የራሱ የሆነ በዘመናችን የሚጠራው የዲሞክራሲም እንበለው የመንግስት ስርዓት ወይንም የአካባቢ አስተዳደር ዘይቤ አለው።ለሺህ ዓመታት የነበረው የነገሥታቱ የንግስና ስርዓትም ሆነ የኦሮሞ ገዳ ስርዓት፣ፍትሐ ነገሥትም ሆነ ሕገ መንግስታዊ ስርዓት ሁሉም በኢትዮጵያ ምድር ያለፉ ናቸው እና በሚገባ መጠናት፣በቂ ምርምር ማድረግ እና መመርመር ይፈልጋሉ።

ይህንን የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ ያላገናዘበ በግብታዊነት የተወሰነ ውሳኔ በሚመስል መልክ የትምህርት ሚኒስቴር የገዳ ስርዓት በአዲስ አበባ እና በኦሮምያ ክልል ከ2013 ዓም የትምህርት ዘመን ጀምሮ እንዲሰጥ መወሰኑን ነሐሴ 23/2012 ዓም የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን በምሽት ዜና እወጃው ላይ  ማስታወቁን ለማወቅ ተችሏል። 

ይህ ውሳኔ ግን በራሱ ብዙ ጥያቄዎችን ያስነሳል።በመጀመርያ ደረጃ የገዳ ስርዓት የኢትዮጵያ ተማሪዎች መማር የለባቸውም የሚል ተቃውሞ በደረቁ ያነሳ የለም።በእዚህ ፅሁፍም ላይ ይህ አይደለም የሚንፀባረቀው። የትምህርት ሚኒስቴር የወሰነበት ሂደት እና አፈፃፀሙ ግን በራሱ ብዙ ጥያቄ ያጭራል።የትምህርት ሚኒስቴር በመላ ሀገሪቱ ውስጥ የሚሰጡ ትምህርቶችን ወጥነት ባለው መልክ እንዲሰጡ የማድረግ ግዴታ አለበት።በአንድ ሀገር ውስጥ ሁለት እና ሶስት አይነት ትምህርት እየሰጠ ትውልድ የሚነጣጥል ተግባር መስራት በራሱ ወንጀል ነው።እዚህ ላይ አንድ መርሳት የሌለብን ጉዳይ የገዳ ስርዓት ታሪክ በኢትዮጵያ ሁሉም ትምህርት ቤቶች እና ዩንቨርስቲዎች በዘመነ ደርግም ሆነ በቀዳማዊ አፄ ሃይለስላሴ ዘመን  በታሪክ ትምህርት ውስጥ  ራሱን በቻለ ምዕራፍ ተሰጥቶት ተማሪዎች ይማሩት ነበር።ይህ አሁን ያልነበረ የሚመስላቸው ካሉ ተሳስተዋል።ኢህአዴግ ስለ ገዳ ማውራት የጀመረ የሚመስላቸው አይጠፉም።ደርግ በኢትዮያ የብሔር ብሔረሰቦች ኢንስቲትዩት ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ አስጠንቶታል። ሆኖም ግን ደርግም ሆነ በአፄ ኃይለ ስላሴ ዘመን በታሪክ ትምህርት ውስጥ ገብቶ ተማሪዎች እንዲማሩት የተደረገው ሀገር በሚከፋፍል አንዱ የእናት ልጅ ሌላው እንጀራ ልጅ በሚመስል እና በሚነጣጥል መልኩ አልነበረም። በወቅቱ ትምህርቱ ትምህርቱ የሚሰጠው  የኢትዮጵያ ታሪክ ትምህርት የሚማሩ ኢትዮጵያውያን ከአክሱም እስከ ሞያሌ፣ከጅጅጋ እስከ ጎንደር በታሪክ ትምህርት ውስጥ የሌላውን የኢትዮጵያ ታሪክ ሲማሩ ራሱን በቻለ ምዕራፍ የገዳ ስርዓትን  በዝርዝር በሚያስረዳ መልኩ ከሌላው የኢትዮጵያ ታሪክ ጋር በአንድነት ነበር። 

የሰሞኑ የትምህርት ሚኒስቴር በተናጥል አስተምራለሁ ያለው ትምህርት ግን የገዳ ስርዓት የሚባል ትምህርት ለብቻው ለአዲስ አበባ እና ለኦሮምያ ክልል እሰጣለሁ የሚል ነው። እዚህ ላይ ጥያቄው የኢትዮጵያ ትምህርት ሚኒስቴር እንዲህ እየነጠለ የእየብሄረሰቡን ትምህርት በትምህርት ካሪኩለም ውስጥ በማስገባት እና ለየብቻው እየሰጠ ይዘልቀዋል? ወይንስ ለገዳ ስርዓት ብቻ ነው የተፈቀደው? ለምንስ ነው የኢትዮጵያ የተለያዩ የዲሞክራሲ ባህሎች በአንድነት ተሰብስበው በእዚሁ ስር የገዳ ስርዓትም ገብቶ ኢትዮጵያውያን በሙሉ እንዲማሩ የማይደረገው? ኢትዮጵያ ለዘመናት የተዳደረችበት ለዓለም አቀፍ ሕግም ያበረከተችው ፍትሐ ነገስት የሚባል ስርዓት እንዳላት የትምህርት ሚኒስቴር አልሰማም? ከገዳ ስርዓት ጋር ለምንድነው ኢትዮጵያውያን የማይማሩት? መማር አይጎዳም።ተማሪዎች ዛሬ የሀገራቸውን የነበረ እና የዳበረ የማሕበራዊ እሴቶች ታሪክ ማወቃቸው ነገ የተሻለውን አውጣጥተው ዘመኑን በዋጀ መልኩ ለሀገራቸው አዲስ ሃሳብ እንዲያፈልቁ ይረዳል።

የትምህርት ሚኒስቴር ዋና መስርያ ቤት አዲስ አበባ (አራት ኪሎ) 

በመሆኑም ትምህርት ሚኒስቴር የገዳ ትምህርትን ለብቻው ለአንዱ ክልል እሰጣለሁ ከማለት ይልቅ ኢትዮጵያውያን በሙሉ በአንድ ማዕድ የገዳ ስርዓትን ጨምሮ ሌሎች የኢትዮጵያ እሴቶች ለምሳሌ ፍትሐ ነገስት፣የኮንሶ ባህላዊ እሴቶች፣የአክሱም ጥንታዊ ስርዓቶች፣የሐረር እና የጅማ የንግድ ባህሎች ሁሉ ያካተተ ስርዓተ ትምህርት ቀርፆ ሁሉንም ኢትዮጵያን እንዲያስተምር ሕዝብ ግፊት ሊያደርግበት ይገባል። የትምህርት ሚኒስቴር ላለፉት 27 ዓመታት በተሳሳተ እና በከፋፋይ የትምህርት ፖሊሲ ኢትዮጵያን እንደከፋፈለ ዳግም እንዲከፋፍል ሊፈቀድለት አይገባም።የትምህርት ሚኒስቴር የተሰጠውን ርዕይ፣ተልዕኮ እና እሴቶች ብሎ ላስቀመጣቸው ገዢ ሃሳቦች ተገዢ እንዲሆን ደግመን ልንነግረው ይገባል።

ከእዚህ በታች የትምህርት ሚኒስቴር ርዕይ፣ተልዕኮ እና እሴቶችን እንመልከት እና አሁን እየነጠለ እና እየከፋፈለ ለመስጠት የምሞክረው ትምህርት ምን ያህል ከራሱ ጋር እንደሚጣላ መመልከቱ በቂ ነው። ፍትሃዊ የትምህርት አሰጣጥ ማለት የሁሉንም ያቀፈ ትምህርት ለሁሉም ኢትዮጵያዊ መስጠት እንጂ እየነጠሉ ብሔሮች የራሳቸውን ታሪክ ብቻ እንዲያጠኑ መወሰን አይደለም።ትምህርት ድንበር የለውም።በትምህርት የአሜሪካንን ታሪክ እያጠናን የአክሱምን የመንግስት ስሪት ወይንም የጎንደርን የቤተ መንግስት ስርዓት ለጅማ እንዳያውቅ ማድረግ ወይንም የአባ ጅፋርን የቤተ መንግስት ስርዓት እና የገዳ ስርዓትን ለወሎ እና ለጎጃም ተማሪ እንዳያውቅ ማድረግ በርሱ የትምህርትን መሰረታዊ መርህ የሚፃረር ተግባር ነው።

የትምህርት ሚኒስቴር  የተቀመጠለት ርዕይ

ብቁ ዜጋ የሚያፈራ፣ ጥራትና ፍትሃዊነት ያረጋገጠ የትምህርትና ስልጠና ስርአት በቀጣይነት መገንባት ነው!

የትምህርት ሚኒስቴር የተሰጠው ተልእኮ

የትምህርት ዘርፉን የማስፈጸም አቅም በመገንባት፣ የብቃት መለኪያዎችን በማውጣትና በማስጠበቅ፣ ደረጃውን የጠበቀ ትምህርትን በማስፋፋት፣ እንዲሁም ተግባሮቻችንን በህዝብ ግንኙነት ስራ በማገዝ ጥራት ያለው ውጤታማና ፍትሃዊ የትምህርትና ስልጠና ስርአትን ማረጋገጥ ነው፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር እሴቶች

- ውጤታማነት
- ጥራት
- ፍትሃዊነት
 -አሳታፊነት
 - አርአያነት
 -የአላማ ጽናት
 - ልቆ መገኝት

================////===========================

Thursday, August 27, 2020

''እንዴት አንድ ሰው ፈጣሪዬ ብሎ በሚጠራው ፈጣሪው የተፈጠረ ብሎ የሚያምነውን ሰው በዕምነት ስላልመሰለው ብቻ በፈጣሪው ሥም ያርዳል?'' - አቶ ዓለማየሁ ብርሃኑ ከባሌ እና ከአርሲ ጉብኝታቸው ባለፈው ሳምንት እንደተመለሱ ለጉዳያችን የተሰማቸውን ፅፈዋል።ሙሉውን ያንብቡ።

አቶ ዓለማየሁ ብርሃኑ

እኔ ባደግሁበት አካባቢ በልጅነት አዕምሮአችን እየሰማን ያደግነው አባቶቻችን ነገ ለሚያደርጉት ነገር ሲቀጣጠሩ በጠዋት ለመገናኘት የቀጠሮ ሠዓት የሚያደርጉት "ጠዋት አላህ ወአክበር ሲል" እንነሳ ይባባሉ ነበር፡፡ ከዚህም ባሻገር እንደዛሬው ሰዓት ባልነበረበት በዚያ ዘመን ጠዋት ክርስቲያን አባቶቻችን ወደ ቤተ ክርስቲናቸው ለመሄድም የመስጊዱን አዛን ቀስቅሶ እንደሚያበረታታ 'በጎ ቀስቃሽ' ይጠቀሙበት ነበር።ምክንያቱም አንዱ የአንዱን እምነት አክብሮ የሚኖርበት የፍቅር ዘመን ስለነበር፡፡
ታዲያ! በዚህና በሌሎችም ምክንያቶች ከእስልምና እምነት ተከታይ አብሮ አደግ ጓደኞቻችን ትርጓሜውን ስንጠይቅ 'ኣላህ ታላቅ ነው' ማለት እንደሆነ ይነግሩን ነበር፡፡ ይህ ቃል እንግዲህ ለጨዋዎቹ የእስልምና አማኞች ክብር ያለው ቃል እንደሆነ ከትርጓሜው መረዳት ይቻላል፤ ለክርስቲያኑም ከላይ እንደጠቀስኩት ይህ ቃል በጎ ቃል ሆኖ ኖሯል፡፡ዛሬም ኢትዮጵያውያን ተከባብረው በሚኖሩበት ቦታ ሁሉ ከመስጊድም ሆነ ከአብያተ ክርስቲያናት የሚወጡ የማንቂያ ድምፆች እንደተከበሩ አሉ ይህ ቃል ግን ዛሬ በምሥራቅ ኦሮሚያ ላሉ ክርስቲያኖች የሰቀቀን ቃል ሆኗል። ክርስቲያኖችን በአደባባይ የሚገድሉ በእስልምና ስም የሚንቀሳቀሱ እና የንፁሃንን ደም የሚያፈሱ ይህንኑ ''አላህ ወአክበር'' የሚሉትን ቃላት እየተጠቀሙ ነው።
በሰኔ 23 እና 24/2012 ዓም በአምስቱ የኦሮሚያ ዞኖች በአካባቢው በሚገኙ የዕምነቱ ተከታይ ነን በሚሉ የመንግስት ባለሥልጣናትና ፖሊሶች ድጋፍ በተደረገው ክርስቲያኖችን የማጥፋት ዘመቻ ላይ ይህ ቃል እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ በሰፊው በሥራ ላይ ውሏል። ግን ለበጎ ተግባር ሳይሆን አብሮ የኖረን ህዝብ ንብረት ለማውደምና ለመስረቅ በተለይም ደግሞ ዕምነት የሌለው ሰው እንኳን ያደርገዋል ተብሎ የማይገመት አሰቃቂ ግድያን በወንድም ላይ ለመፈፀም ነው፡፡ እኔም በባሌና አርሲ የደረሰውን ጉዳት ለማየት ባለፈው ሳምንት ከሄደው ቡድን ጋር ተጉዤ ነበርና ከተጎጂዎቹ በአካል ተገኝተን በሰማነው መሠረት ሰው በህይወቱ እያለ እጅ ሲቆርጡ ዓይን ሲያወጡ፣ አጋርፋ ላይ የአእምሮ ዝግመት ያለበትን ወጣት ጭንቅላቱን ቀጥቅጠው በማጅራቱ ሲያርዱትና መሰል አስነዋሪ ተግባራትን ሲፈፅሙ ሁሉ "አላህ ወአክበር" እያሉ እንደነበር ከጉዳቱ የተረፉት ሃዘን በተሞላ አንደበት ተርከውልናል ፡፡
ይህ ነገር አዲስ አይደለም ሠዎች በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ከክርስቲያኑ ሃጫሉ ሞት ጋር ያያይዙታል። ነገር ግን ይኼ ታቅዶ የተሰራ ዛሬ ብቻ ሳይሆን ከአስር ዓመት በፊትም በጅማ ዙርያ በሻሻ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያንም በተመሳሳይ እልቂት ሲፈፀም ይሄው ቃል እየተጠራ ነበር።በቅርቡ በጥቅምት/2012 ዓም ተመሳሳይ ድርጊት በተፈፀመበት እና ከ80 በላይ ንፁሃን ሕይወት በጠፋበት እልቂት ወቅትም ይሄው ቃላት የተደጋገመ መፈክር ሆኗል፡፡ የድሮ አልቃሽ አባቷ ሞቶባት በዓመቱ ባሏ ለሞተባት ሴት ስታላቅስ "ያምናን ቀን አማሁት ላፌ ለከት የለው፤ መጣ የዘንድሮው እጅ እግር የሌለው፡፡" አለች አሉ፡፡ እኛም ታዲያ 'ከካቻምናም አምና ከአምናውም ዘንድሮ፤ እያስጠላኝ መጣ የዚች ዓለም ኑሮ' እንድንል በክርስቲያንነታችን እየተገፋን ነው፡፡ እንዴት አንድ ሰው ፈጣሪዬ ብሎ በሚጠራው ፈጣሪው የተፈጠረ ብሎ የሚያምነውን ሰው በዕምነት ስላልመሰለው ብቻ በፈጣሪው ሥም ያርዳል? እንዲህ ዓይነት የዕምነት አስተምህሮ አለ ብሎ መቀበል በዕውነቱ ይከብዳል። በተለይ ጠላትህን ውደድ በሚል አስተምህሮ ለተገራው ከአዕምሮ በላይ ነው፤ ግን ደግሞ እየሆነ ያለው ዕውነታ ይህ ነው፡፡
እዚህ ላይ ታዲያ የኔ ጥያቄ በተለይ ለዕውነተኞቹ የእስልምና አማኞች በርዕሱ ላይ እንደጠቀስኩት 'አላሁ አክበር' ትርጉሙ ተለወጠ እንዴ? የሚል ነው፡፡ እኔ ይወክሏችኋል ብዬ ባላምንም እናንተም በምታመልኩበት አምላካችሁ ሥም ነውና እየተገደልን ያለነው ለምን ዝም አላችሁ? አምናችሁበት በውስጣችሁ ደስ እያላችሁ? ወይንስ ከናንተው ወገን ያለሃፍረት 'እዚህም ቤት እሳት አለ' በሚል ዓይነት ማስፈራሪያ የምናስጮኸው አናጣም ብለው ሊያስፈራሩን የሚሹት ሠዎች እናንተም ላይ የሚያሳድሩት ስውር ደባ ይኖራቸው ይሆን? በእርግጥ ኃይማኖትን የተረዱ ጥቂት ዕውነተኛ ኡስታዞችና ህሊናቸውን ለዕውነት አስገዝተው ስለዕውነት ድርጊቱን በማውገዝ በፊት ለፊት በግላቸው ያወገዙትን ዋጋ ማሳጣት አልፈልግም፡፡ በሌላም በኩል በሱማሌ ክልል ደርሦ በነበረው ጥቃት በይፋ ድርጊቱን በማውገዝና ይቅርታ በመጠየቅ በጋራ ለማቋቋም ጥረት ያደረጉትን የክልሉን ፕሬዝዳንት ሙስጠፌንና የሶማሌ ሙስሊም የሃገር ሽማግሌዎች ዓይነት ሠዎች ባሉበት ሃገር ከዚህ ትምህርት መውሰድ ሲገባ ዛሬም 'አምላክ ታላቅ ነው' እያሉ አምላክ የፈጠረውን በማረድ ለማባረር መሞከር መጨረሻው ላያምር ይችላልና ቆም ብለን ብናስብበት ጥሩ ነው፡

እንደኔ ግን እነኚህ ሠዎች ለክርስትና ብቻ ሳይሆን ሳያምኑበት የሚያምኑበት አስመስለው ዓላማቸውን ማራመጃ ላደረጉት ለእስልምናም ውሎ አድሮ አደጋነታቸው አይቀሬ ነው፡፡ ስለዚህ ሁሉም በጋራ ሊያወግዘው የሚገባ ሃይማኖት ተኮር እኩይ ተግባር ነው፡፡ ይህ ሲባል የሚያቅራቸው የመንግስት ሹማምንትም ለዕውነታው ዕውቅና ሰጥተውና ይፋ ይቅርታ ጠይቀው ለመፍትሔው አብሮ መስራት ይሻላል እንጂ የሐይማኖት አይደለምና ዕውነትን አትናገሩ ብሎ ሚዲያዎችን ለማገት መጣሩ ለማንም አይጠቅምም፡፡ ቤተክርስቲያን በተለይ ባለፉት ሁለት ዓመታት 'ለምጣዱ ሲባል…' በሚለው ሃገራዊ ብሂል መሠረት ብዙ መከራዎችን ዋጥ አድርጋ መታገሷን ታሪክ ይመዘግበዋል፡፡ አሁንም ይልቅ የደህንነት ሥጋት ያለባቸውን የዴራ ወረዳ ክርስቲኖች ቤት ንብረታቸው መውደሙ እየታወቀ ከተጠለሉበት ቤተ ክርስቲን ያለምንም ዝግጅት እንዲወጡ የሚያስገድዱ የወረዳ ሹማምንት ዕውነት ለመንግስት ጥሩ ሥም እየሰሩ ነው? ወይስ ያላለቀ ተልዕኮ ያላቸው ሠዎች ዛሬም ይኖሩ ይሆን? አሁንም የኦሮምያ ክልል ይህንን ፈትሾ ለዜጎች የደህንነት ዋስትና የመስጠት ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል፡፡
አምላክ እንደአባቶቻችን በፍቅር የምንኖርበትን ጊዜ ያምጣልን፡፡
ዓለማየሁ ብርሃኑ ነኝ

Monday, August 24, 2020

Why do the majority of Ethiopians support the visionary and talented PM Abiy Ahmed of Ethiopia?

Abiy Ahmed the winner of 2019 Nobel Peace Prize

================
In Ethiopia, extremists under the cover of Oromo ethnicity, killed over 200 people only within only three days following the famous musician Hachalu Hundessa assassinated on June 29,2020.The massive killing innocents was followed by destroying their properties and business centers. In Oromia region cities and rural areas like Shashemene,Arsi, Bale and Harar were typically targeted areas.Most of the victims were also being killed only because of their religion of christianity.The massive killing acts of innocent civilians were motivated by extremists social mediators residing in Europe (including Norway),Canada and USA. The social media motivators who need to load their non-humanity and savage ideas and acts on Ethiopian people are also accusing Abiy by demonstrations in Europe,USA and Canada streets.These are the people who opposed the legal action that the Abiy government is taking now. Their fear is that if law and regulations are approved in Ethiopia, their extreme plan will not be functional.

Contrary to extremists, the majority of Ethiopians including the Oromo region at home and abroad support all necessary actions that Abiy is taking now. Law and regulations are a key factor for any country's peace and stability.Here the paradox we should know is that Abiy himself is from Oromo ethnic.However extremists are calling themselves ‘’Oromo’’ more than the PM. The situation is a little bit 'funny'.Because even if the main objective of the extremists is to run extremism, they still attempt to use the cover of Oromo ethnicity.Ethnicity issues are not considered as a major issue to be leader in Ethiopia.However, the stand for humanity and respecting the legal framework matters a lot.

Europe and US policy makers and Governments must understand well the real cause and situation in Ethiopia.In Ethiopia, currently almost all regions including the Ethiopian-Somali region, Amhara, Gambella and Afar are so peaceful and busy doing their day to day development activities. The only problem is in extremists' temporary field, some parts of the Oromia region.

Therefore, the international community must stand with Abiy and his government. Because the horn of Africa peace and stability could be assured only through the modern and visionary leader of Abiy. It should be clear also the International community is not only expected to support Abiy's government, it is also very vital condemning extremists running hidden agenda within Oromo ethnicity.

Last but not least, we need to notice that Abiy is not only the hope of Ethiopia stability but he is also the right person to serve as a key bridge for the future political,Economic and Social relations between Africa and the rest of the world. So it is unquestionable, majority of Ethiopians will continue to support Prime minister Abiy Ahmed (Phd) administration. Yes! there are a number of challenges that his government is facing. Poverty, the past regime ethnocentric policy and corruption are the major one.These are also huge problems to other parts of the world.It is not unique only for Ethiopia. The difference is that Ethiopia is in huge transition process to tackle the problems.Now! the pre-most issue to Ethiopia and the Abiy's government is to control the extremists' move in any form both violently and spreading fake news on social media.The government is becoming successful to control illegal acts of the extremists.Therefore it is not vague why Ethiopians continue to support Abiy. They have a very good reason to do so.He is taking key measures to assure law and order in the country. It is quite clear that peace and stability are the key important issues of any government. Particularly, Ethiopia's peace and stability is the guarantee for the horn of Africa and the Middle East.

Getachew Bekele
Editor, Gudayachn


ጉዳያችን ሚድያ፣ኮሚኒኬሽን እና ምክር አገልግሎት 

Gudayachn Multimedia, Communication and Consultant
Gudayachn Multimedia, Kommunikasjon og Konsultent 

Saturday, August 22, 2020

በውጪ ሀገር የሚኖሩ የዝምተኞች እና የዳር ተመልካች ኢትዮጵያውያን መብዛት አገርን ዋጋ እያስከፈለ ነው።ሁኔታው የፅንፍ ኃይሎች በተሳሳተ መንገዳቸው እንዲቀጥሉ 'ዕድል' ሰጥቷቸዋል።


>> በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እውነታውን ለሚኖሩበት ሀገሮች ሚድያዎች በመግለጥ እና በመፃፍ  ከምን ጊዜውም በላይ ሊተጉ ይገባል።
>> የኢትዮጵያ ኤምባሲ ማኅበረሰብም ሆነ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ለውጪ መንግሥታት በውጪ ሀገር ሆነው የፅንፍ ፖለቲካ የሚያራምዱ ኃይሎች እኩይ ተግባር ማጋለጥ አለበት። 

እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ከ1992 እስከ 1995 ዓም የቦስንያ ጦርነት ተብሎ የሚታወቀው የመካከለኛው አውሮፓ እልቂት ከ25 ሺህ እስከ 30 ሺህ ንፁሃን ሕይወት ተቀጥፎበታል።እልቂቱ የታጀበበት አንዱ አሳዛኝ ክስተት ደግሞ ከፍተኛ የሐሰት ፕሮፓጋንዳ ቀድሞ እየተነዛ እውነቱን ለመሸፈን የተደረገው አሳዛኝ ጥረት ነው።

በኢትዮጵያ በኦሮሞ ስም የሚነግዱ የፅንፈኛ ኃይሎች በአሁኑ ጊዜ እየፈፀሙ ያለው ወንጀልም በአውሮፓ ከተፈፀመው ወንጀል ጋር ተመሳሳይ ነው።ይሄውም በውጪ የሚኖሩ በኦሮሞ ስም የፅንፍ ኃይሎች በሚያደርጉት ቅስቀሳ ሳቢያ በሀገር ውስጥ የንፁሃን መገደል ምክንያት መሆናቸውን ለመሸፈን በማኅበራዊ ሚድያ እና በሰልፍ ቀድመው በመጮህ እውነታውን ለመሸፈን መሞከር አሁን የያዙት አንዱ ስልት ነው።

የፅንፍ ኃይሉ አሁን በኦሮምያ ባለው የስልጣን ተዋረድ ውስጥም ተሸሽጎ የፅንፍ ኃይሉ በንፁሃን ላይ ያደረሰውን የግድያ እና የንብረት ማውደም ተግባር ለመሽፋፈን የተደረገው ጥረት በግልጥ ታይቷል።ይህንንም ክፍተት በመጠቀም በውጪ ያለው የፅንፍ ኃይል በኢትዮጵያ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ በመሸፈን የኦሮሞ ማኅበረሰብን እንደ ማኅበረሰብ ለማጥቃት የሚደረግ ተግባር እንዳለ በማስመሰል በሰልፍ፣የተለያዩ ፅሁፎችን በውጪ ሀገር ለሚገኙ ጋዜጦች እና ድረ ገፆች በመፃፍ እና ለፓርላማ አባላት በቀጥታ ትውተር በመፃፍ ሁሉ የተሳሳተ መረጃ እንዲደርስ ለማድረግ ጥረት አድርገዋል።

ይህ በእንዲህ እያለ በውጪ የሚኖሩ በከፍተኛ የሙያ እና የአቅም ደረጃ ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የዳር ተመልካች መሆናቸው እና ዝምታቸው በኦሮሞ ስም ለሚነግዱ የፅንፍ ኃይሎች በተሳሳተ መንገዳቸው እንዲቀጥሉ 'ዕድል' ሰጥቷቸዋል።በእርግጥ የፅንፍ ኃይሎችን የተሳሳተ ትርክት እና የሐሰት ዜናዎች ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለማጋለጥ ከሰላማዊ ሰልፍ እስከ የተለያዩ ጋዜጦች ላይ በመፃፍ ለኢትዮጵያ ድምፅ የሆኑ መኖራቸው ይታወቃል።ሆኖም ግን በውጭ ሀገሮች ከሚኖረው ከፍተኛ አቅም ያለው ኢትዮጵያዊ አንፃር የዝምተኞች እና ዳር ተመልካቾች መብዛት ኢትዮጵያን ዋጋ እያስከፈላት ነው።

የፅንፍ ኃይሎች በኢትዮጵያ ላለው የንፁሃን እልቂት ተጠያቂ እና ምክንያት መሆናቸውን በመሸፈን ያደረጉት መጮህ የአሜሪካን ምክር ቤት አባላትን እስከ ማሳሳት ደርሷል።በእርግጥ የአሜሪካ ምክር ቤት እውነተኛው መረጃ ሳይገባው ቀርቶ ነው ለማለት አይቻልም።የምክር ቤት አባላቱ ከ200 በላይ የሚሆኑ ንፁሃን በግፍ የተገደሉበት አንዱ መነሻ በአሜሪካ ጭምር የሚኖሩ የፅንፍ ኃይሎች ቅስቀሳ መሆኑን ያውቃሉ።ሆኖም ግን ስለ ንፁሃኑ መገደል አንዳች አልተነፈሱም።ይህ ሁኔታም በራሱ የምክር ቤት አባላቱ የሌላ የአሜሪካ የውጪ ፖሊሲ ማስፈፀምያነት የሰሞኑን የኢትዮጵያ ሁኔታ ለመጠቀም የሞከሩ ይመስላል።የምክር ቤቱ አባላት የኢትዮጵያን የአንድነት ጉዳይ ከዲሞክራሲ እና ከሰብዓዊ መብት መርሆዎች አንፃር ብቻ እየተነተኑ ለማቅረብ ከሞከሩ በራሱ አደጋ ነው። 

ይህ በእንዲህ እያለ ግን በመጨረሻ መሰመር ያለበት ጉዳይ በውጪ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ለውጪ መንግሥታት የማስረዳት ታሪካዊ ኃላፊነት ከምንግዜውም በላይ በእነርሱ ላይ መውደቁን ሊረዱት ይገባል።ለእዚህም ያስተማረቻቸውን ሀገር ሳይመሰክሩላት በዝምታ ድባብ የሚኖሩ የዳር ተመልካች ኢትዮጵያውያን የታሪክ ተወቃሽ እንዳይሆኑ ከምንጊዜውም በላይ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት መነሳት ይገባቸዋል።በእዚህም መሰረት የፅንፍ ኃይሎችን ተግባር እና በውጪ በሀገር ቤት በንፁሃን ላይ የእልቂት ተግባር እንዲፈፀም የሚቀሰቅሱትን ሁሉ ከተግባራቸው እንዲታቀቡ እውነታውን በእየሃገራቱ ለሚገኙ የቴሌቭዥን ጣቢያዎች፣የድረ ገፅ እና የህትመት ጋዜጦች፣የፓርላማ አባላት እና ፖሊሲ አውጪዎች ሁሉ የማስረዳቱን ኃላፊነት መወጣት አለባቸው።ከእዚህ በተጨማሪ የማኅበራዊ ድረ-ገፆቻቸውን በመጠቀም ለቀሪው ዓለም እውነታውን ለማሳወቅ መድከም ይገባቸዋል።

ከእዚህ በታች እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ነሐሴ 21/2020 ዓም የአሜሪካ ምክር ቤት አባላት በኢትዮጵያ በፅንፍ ኃይሎች የሚፈፀመውን የጥፋት ተግባር ባላገናዘበ መልኩ በኢትዮጵያ ባለው የውስጥ ጉዳይ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በስልሳ ቀናት ሪፖርት እንዲያቀርብ የጠየቁበት ደብዳቤ ነው።የብዙ ኢትዮጵያውያን ዝምታ እና የዳር ተመልካችነት እንዲህ ኢትዮጵያን እንደሚያስጠቃ መረዳት ይገባል።


===========================//////=====================

Friday, August 21, 2020

GERD is meant to connect millions to power grid. Scholars’ in Norway present papers on GERD


The Ethiopian herald News Paper
August 20 , 2020
BY STAFF REPORTER
Addis Ababa
**************************
(EPA)
ADDIS ABABA - Over sixty-million rural people who have no access to electricity are counting down the days to the first energy generation of the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD).
Ethiopian Common Forum in Norway held a discussion and paper presentation on GERD last Saturday in cooperation with the GERD Support Group in Norway.
In his keynote speech, Ethiopian Ambassador to Sweden and other Nordic countries Diriba Kuma said this in a forum envisaged to inform the Norwegian government, officials, journalists, and the Ethiopian community in Norway.
Diriba underscored that Abay (the Nile) touches 70 percent of the livelihood of the population of Ethiopia and represents 2/3 of Ethiopia’s surface water potential, while over 70 percent of energy generation potential is in this river.
Indicating that 25 million people of Ethiopia are living under the poverty line, and 65 million people of Ethiopia have no access to electricity, he said: “Our citizens are waiting for the completion of the dam.” The government of Ethiopia has taken practical steps to negotiate and discuss all important matters since the inception of the project as these are the way out of the dispute, he said, adding that the GERD has no significant impact on the flow of Nile to downstream countries.
He also expressed a strong belief that under the auspicious of South African President Cyril Ramaphosa’s leadership the three countries would resolve the outstanding issues. Elaborating on the rationale of the forum, Dr. Mulugeta Bereded Zelelew, one of the paper presenters, said Egypt’s attempt to internationalize the GERD project with massive media coverage has been with full of bias and misleading information.
Group of GERD support Team in Norway did analysis into the media coverage, and decided to lay bare Egyptian fabrications with scientific evidence, he added. In his paper, entitled:GERD Project and its Significance for Ethiopia and the Region, he refuted Egyptian claim which is presenting Ethiopia as it has abundant rainfall arguing that the rainfall in Ethiopia is erratic and rushes to the rivers due to the nature of the topography. Hence, there is little time for the water to infiltrate into the soil and remain as residual moisture for sufficient time. It is to be noted that the major rivers of Ethiopia are trans-boundary.
Under normal rainfall year, as much as 5 – 10 million or more Ethiopians are chronically food insecure, he said, adding that 80-85% of the total volume occurs during the major rainy season and water storages are necessary to prolong water availability. Concerning the view that GERD is “an existential threat” to downstream countries of the Nile, he said: “Historical records thought us that Egypt and Sudan which have high storage capacity per capita have more resilience to drought management.”
In severe multi-year droughts, a basinwide drought management plan is required to optimize the competing water uses in the three countries and the three countries should take a shared responsibility to mitigate drought, according to him.
For his part, Dr. Admasu Gebeyehu, Professor of Practice in Water Resources Engineering,indicated that the great majority, 92.4 percent, of the share of energy supply is waste and biomass. He said the share of oil and hydropower is 5.7 percent and 1.6 percent respectively.
The bulk of energy source, 98 percent, in Norway is electricity production from a renewable energy source, he said, noting that Norway is in a unique position in the global perspective while Ethiopia is also in the same position in an African perspective with regard to hydropower potential.
The difference between Ethiopia and Norway is, Norway has gone a lot in the production of energy while Ethiopia has started going through the same path, he added.He also put the contribution of Ethiopia to Nile which stands at 77 BCM or 86 percent of the waters of the Nile.
However, his analyses have proven that Ethiopia’s water storage is insignificant as compared to Sudan and Egypt. Egypt has the Aswan High Dam with a storage capacity of 149.5 BCM while a series of dams in Sudan have boosted the Sudanese storage capacity.
Senior Ugandan Water Engineer Dr. Emmanuel Jjunju (PhD) also presented his work titled: ‘Victoria And Albert Nile Countries’interests On Nile Water Resources’. Jjunju touched up on issues ranging from colonial agreements to the recent basin-wide document, the Cooperative Framework Agreement (CFA).
He said almost all Nile Basin countries are at low level in human development with an exception of Egypt. If you want to take all these countries to the level of Egypt, for instance, it requires the countries lot of work. And it cannot come by without energy.
As electricity is a very big driver of development, be it education, telecom or what have you, countries ought to do a lot in this regard.
Mentioning that hydropower is the most feasible and affordable source of energy to the countries such as Uganda, Burundi and Kenya, he said most of the hydro potential of Uganda, 6,950 MW, is within the Nile basin.
He added that his country, Uganda, go to expensive alternative sources of energy that cost 0.16-0.20 USD cents/ Kh which is not really affordable. The benefits of GERD to downstream countries was discussed thoroughly with the presentations of scientific evidence, it was learnt.
================////============

Thursday, August 13, 2020

Nordmenn er invitert til Webinar-presentasjon og diskusjoner om Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) / Norwegians are invited to Webinar presentation and discussions on the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD)


Gudayachn Report

August 14,2020

Senior Hydrologists and water resource Engineers webinar presentation and discussions on creating awareness about the Great Ethiopian Renaissance Dam (GERD) on the Blue Nile River to be held on Saturday, August 15,2020 between 11 am to 1 pm. 


Ethiopian Common Forum in Norway is a coordinator of a webinar presentation and discussion.The meeting will be attended by Ethiopian Ambassador for Nordic countries, His Excellency Ambassador Diriba Kuma, and Norwegian professionals from different  offices including Norwegian  Ministry of Foreign Affairs.


Here below, you will find the webinar link.You are invited to attend the meeting.

Date and time: Aug 15, 2020 11:00 AM Oslo

Topic: special discussion of creating awareness about the Great Ethiopian Renaissance Dam (GERD) on the Blue Nile River

Please click the link below to join the webinar:

https://us02web.zoom.us/j/82883949861


Monday, August 10, 2020

አዲስ የተመሰረተው ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕብረት (International Orthodox Tewahedo Alliance - IOTA) በሰሞኑ በኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ላይ የደረሰውን ጭፍጨፋ የአካል እና የስነልቡና ጉዳት እንዲሁም የንብረት መውደም የሚያወግዝ መግለጫ አወጣ።



የመግለጫውን ሙሉ ይዘት ይዘናል


አዲስ የተመሰረተው ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕብረት (International Orthodox Tewahedo Alliance - IOTA) በሰሞኑ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስቲያኖች ላይ የደረሰውን ጭፍጨፋ  የአካል እና የስነልቡና ጉዳት እንዲሁም የንብረት መውደም አስመልክቶ ጠንካራ መግለጫ አውጥቷል።በኢትዮጵያ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በሕጋዊ መንገድ በመንቀሳቀስ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስቲያኖችን መብት፣ደህንነት እና መልካም ዕሴቶች ላይ ለመስራት በቅርቡ የተመሰረተው እና በአሜሪካን ሀገር ሕጋዊ ምዝገባውን ያጠናቀቀው  ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕብረት (International Orthodox Tewahedo Alliance - IOTA) በዋናነት በችግርም ሆነ በመልካም ጊዜ  የቤተ ክርስቲያኒቱ ድምፅ በውጪ ሀገር ባለው ማኅበረሰብ በሚገባ አለመደመጡን ከግንዛቤ በማስገባት የተመሰረተ ለመሆኑ ድረ-ገፁ በዋናነት በእንግሊዝኛ የተዘጋጀ መሆኑን በመመልከት ለመረዳት ይቻላል።


ድርጅቱ በድረገፁ ላይ እንደሚያስነብበው ዋና ተልዕኮው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናንን ሁለንተናዊ ተደማጭነት ማጉላት መሆኑን ሲገልጥ እንዲህ አስቀምጦታል ‘’Our mission is to empower the Ethiopian Orthodox Tewahedo believers and communities’’ በሌላ በኩል ድርጅቱ ርዕዩን አስመልክቶ የገለጠበት ዓረፍተ ነገር ደግሞ ‘’ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እና ተከታይ ምእመናኖቿ ካለምንም ጥቃት እና መሸማቀቅ ዕምነታቸውን የሚገልጡባት ዓለም መፍጠር’’  ‘’To create a better world where Ethiopian Orthodox Tewahedo Churches and believers can be self-sustained to freely practice their faith without intimidation and persecution’’ የሚል ነው። 


ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕብረት (International Orthodox Tewahedo Alliance - IOTA) ሰሞኑን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን እና ንብረታቸው ላይ የደረሰውን ጥቃት አስመልክቶ ያወጣው መግለጫ፣የድርጅቱን ድረ-ገፅ ማስፈንጠርያ (ሊንክ) እና ኢ-ሜይል ከእዚህ በታች ያገኛሉ -

Press Release – International Orthodox Tewahedo Alliance (IOTA) 

On June 29 and 30, following the assassination of renowned artist Hachalu Hundessa, violent protests took place across Ethiopia. These acts of terror occurred in selected cities and towns across ten provincial zones (Eastern and Western Arsi, Eastern and Western Hararge, Eastern Showa, Southwestern Showa, Jima, Balle, Harar and Metu, and two federally administered cities: Addis Ababa and Dire Dawa. Within the two days of violence, 239 lives, mostly civilians and Orthodox Christians are known to have been killed. According to government authorities, approximately 328 houses, mostly of ethnic minorities and Orthodox Christians, 44 hotels, 6 factories and 14 government buildings have been burned down or destroyed. The International Orthodox Tewahedo Alliance (IOTA) strongly condemns the killing of innocent citizens and destruction of their properties throughout the Oromia administrative region in Ethiopia. 

These destructions are generally characterized as protests and spontaneous responses to the death of the artist; however, the coordination level of the destruction indicates a premeditated and well-orchestrated execution by an organized group that seeks to target Orthodox Christians. These organized groups have taken hold of some elements of the government to promote these persecutions and deny justice. Some high-level government officials are downplaying and denying these genocidal crimes. Without credible and transparent investigation of these crimes, the country is on the brink of an unimaginable genocide. 

IOTA denounces the authorities’ abdication of their sacred duty to protect and defend the defenseless, the hateful rhetoric and incitement of ethnic and religious violence by the media, political activists and organizations. We support the current measures the federal government is taking to combat such actions and hope that there will be a transparent and fair trial for the accused. 

We call on the Ethiopian government to protect and defend innocent citizens, rehabilitate those displaced from their homes and those affected by these heinous and gruesome acts of terror and bringing the perpetrators to justice. Finally, we call on the international community to pay close attention to these recurring violent and targeted crimes against Orthodox Christians and ethnic minorities, and support the protection of justice for innocent victims. 

Respectfully,

Office of IOTA 

+++++++++++++++++++++

የድርጅቱ ድረ-ገፅ = https://iotaethio.org/

ኢ-ሜይል = office@iotaethio.org 



Saturday, August 8, 2020

የኦሮምያ ክልል ባለስልጣን በዓለም ዓቀፍ ወንጀል መጠየቅ አለባቸው -በኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች ላይ በአሰበ ተፈሪ ፣መኢሶ እና የአሰቦት የደረሰው ጭፍጨፋ (ቪድዮ)

-  እንጨት ሸጠው ያሳደጉ እናቷን ልትረዳ በባህር በኩል አረብ ሀገር ደርሳ ያፈራችውን ንብረት እንዴት እንዳወደሙት፣

- እራሱን ለማዳን ወደ ፖሊስ ጣብያ ሸሽቶ ሲሄድ ፖሊሶቹ እራሳቸው የገደሉት፣

- ባለቤቱ እና የአምስት ዓመት ልጁ ፊት የታረደው አባት፣ልጁ አሁን የአዕምሮ ህመምተኛ ሆኗል፣
- አስከሬን አነሳህ ተብሎ አሁንም ፖሊስ እየፈለገው ያለ ክርስቲያን 
- ቤተክርስቲያን ስረዳ የነበረ ለፍልሰታ በየዓመቱ ለሚያስቀሱ ሁሉ ንፍሮ የሚያድለው ምዕመን ታርዷል።


Thursday, August 6, 2020

የአቶ ሽመልስ አብዲሳ ዓይኞች የታረዱ ክርስቲያኖችን አንገት አሁንም ማየት አልቻሉም።ዛሬም በቃለ መጠይቃቸው ስለ ላም እና ጊደር ተረት እየተረቱ እና በ150 ዓመት የውሸት ትርክት ድክመታቸውን ሊሸፍኑ ይሞክራሉ።

አቶ ሽመልስ አብዲሳ 

የሰው ልጅ አንገት በካራ ተቀነጠሰ፣እርጉዝ በስለት ሆዷ ተቀደደ እየተባሉ የአስተዳደር ድክመታቸውን  በላም እና ጊደር ተረት ለመሸፈን ይሞክራሉ።በያዝነው ሳምንት አጋማሽ በኦቢኤን ቴሌቭዥን ቀርበው መግለጫ የሰጡት የኦሮምያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ በቃለ መጠየቃቸው ላይ አሁንም በጎሳ ፖለቲካ የኦሮሞ ህዝብን ስሜት በመኮርኮር ቅጥ የለሽ የክልል አስተዳደር ሥርዓታቸውን ሊሸፋፍኑ እየሞከሩ ነው።በእዚሁ ቃለ መጠየቅ ላይ እስካሁን ምን ሰሩ? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ ከአንድ ዓመት በፊት በኮሚቴ የተሰራውን ከሱማሌ ክልል የተፈናቀሉትን መመለስ ከጠቀሱ በኃላ በድፍኑ በርካታ ፕሮጀክቶች ተመርቀዋል በማለት አልፈውታል።በእርግጥ በክልሉ ውስጥ የተፈጠረው የሰላም እጦት ከክልሉ አልፎ ለኢትዮጵያም አደገኛ ሁኔታ መጋረጡን በራሱ እንደ አንድ የኦሮሞ መኩርያ ነጥብ አድርገው ሊያጎሉትም ሞክረዋል።
በኦሮምያ የተነሳው የፀጥታ ችግር ምክንያቶቹ እንደርሳቸው አገላለጥ ላለፉት ክ/ዘመናት ኦሮምያን የበዘበዙ ናቸው ካሉ በኃላ ችግሩ 'ድንበሩን እንዲያልፍ' ያደረጉት አሁንም ለ150 ዓመታት የተበተቡት ናቸው ብለዋል።በመቀጠል የኦሮሞ ሕዝብ ስልጣኑን አግኝቷል፣ባገኘው ስልጣን መጠቀም አለበት ብለዋል።ላለፉት 150 ዓመታት ኦሮሞ የተሸነፈው ከውስጣችን ተላላኪ ፈረስ ስላለ ነው ብለዋል።በመቀጠልም ላሚቷ፣ጊደሯም፣ወተቷም፣አሬራውም አሁን በእጃችን ነው ሲሉ በእዚሁ ቃለ መጠየቃቸው ላይ ተደምጠዋል። 

አቶ ሽመልስ በእዚህ ቃለ መጠየቃቸው  ትውልድ ከማቀራረብ ይልቅ የሚያራርቅ ጉዳይ ላይ ማተኮራቸው አሳፋሪ የመንግስት ባለስልጣን ያደርጋቸዋል።ኢትዮጵያ ላለፉት 150 ዓመታት ውስጥ የነበረችበትን የፊውዳል፣የፊውዶ-ቡርዣ እና የደርግ ዘመን (የሶሻሊስት ርዕዮት) አስተዳደር ሁሉ በአንድ ከረጢት ውስጥ ከትተው የኦሮሞ ሕዝብ ለ150 ዓመታት ሲበዘበዝ ነበር የሚለው ትርክታቸው ፈፅሞ ውሸት ነው።ይህ ተራ የስሜት መኮርኮር ሙከራ ከመሆን አያልፍም።

በእዚህም አቶ ሽመልስ ምን ያህል የታሪክ ዕውቀታቸው ብዙ የሚቀረው መሆኑን ያሳያል። እዚህ ላይ አፄ ሃይለስላሴም ሆኑ ኮለኔል መንግስቱ እነማን እንደሆኑ አለማወቃቸውን ያሳብቅባቸዋል።ከ150 ዓመቱ ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆነውን የመሩት እነርሱ ናቸው።ሁለቱም ደግሞ ከኦሮሞ ቤተሰብ የሚወለዱ ናቸው።አቶ ሽመልስ በምናብ የፈጠሩት ብዝበዛ ተራ የብሔር ስሜት ኮርኩረው ነገሮችን ለማድበስበስ ነው የሞከሩበት መንገድ ከመሆን አሁንም አያልፍም።ላለፉት 150 ዓመታት ለምሳሌ በፊውዳል ስርዓት ውስጥ ጭሰኛ ወሎ ውስጥ እንደነበረ ሁሉ ወለጋም ውስጥ ነበር።የወለጋው ባላባት ከወለጋ የወጡ ደጃዝማች እና ፊታውራሪዎች እንደሁኑ ሁሉ በወሎ እና ጎንደርም ተመሳሳይ ነበሩ።በ1967 ዓም የካቲት 25 የወጣው መሬት ላራሹ አዋጅ ደግሞ ይህንን የፊውዳል ስርዓት ስያንኮታኩት ወለጋ ያለው ገበሬም መሬት እንደተመራ ሁሉ ለጎንደሩም ተመርቷል።ኦሮሞ በተለየ የተበዘበዘበት የቱ ጋር ነው? 

የድምፃዊ ሃጫሉ ግድያ ተከትሎ በአርሲ፣ሐረር፣ባሌ፣ዝዋይ እና ሻሸመኔ በንፁሃን ላይ በደረሰው አሰቃቂ ግድያ እና የንብረት ዘረፋ የክልሉ የፀጥታ አጠባበቅ፣የልዩ ኃይል ከፅንፈኞች ጋር መተባበሩን በምስክርነት የሚያነሱ ተጠቂዎች እየተናገሩ፣ሰው በአደባባይ በስለት መታረዱ እርጉዝ ሴት በስለት መገደሏ ባጠቃላይ ከ200 ያላነሱ ኢትዮጵያውያን በተለይ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት  ተከታዮችን እንዳጠቃ እያወቁ ዛሬም የሰለቸ የ150 ዓመት ትርክት ውስጥ ለማብራራት መሞከራቸው የሚመሩትን ሕዝብ አለማወቃቸውን ያመለክታል።

የአቶ ሽመልስ አብዲሳ የኦሮምያ አመራር በክልሉ የሚያስተዳድረውን ሕዝብ እኩል የማስተዳደር እና በአንድ ዓይን የማየት ከፍተኛ ችግር እንዳለበት በክልሉ የሚኖሩ አሁን ድረስ የሚያማርሩት ጉዳይ ነው።በእዚህም ሳቢያ በርካቶች መጤ እየተባሉ እንደ ሁለተኛ ዜጋ የሚኖሩባት ክልል የሆነችው የኦሮምያ ክልል በአሁኑ ጊዜ ኢንቨስተሩ እየለቀቀ ወደ ሐዋሳ፣ባህርዳር እና ደብረብርሃን እየሸሸ እና ከፍተኛ የካፒታል ሽሽት እየታየ አቶ ሽመልስ ግን ብዙ ፕሮጀክት ገንብተናል እያሉ ነው።

የአቶ ሽመልስ ሌላው የአስተዳደር ድክመታቸው ማሳያ ደግሞ ሰሞኑን በአርሲ፣ሐረር፣ባሌ፣ዝዋይ እና ሻሸመኔ በንፁሃን ላይ በደረሰው አሰቃቂ ግድያ እና የንብረት ማቃጠል እና ዘረፋ ተከትሎ ለደረሰው ጥፋት የሃዘን መግለጫም ሆነ በቦታው ሄደው ያላፅናኑት አቶ ሽመልስ ከሰብዓዊነት ስሜት በራቀ መልኩ ለችግሩ መቀረፍ ያደረጉት የጎላ እንቅስቃሴ አለመታየቱ ብዙዎችን ግራ አጋብቷል።ባድምፃዊ ሃጫሉ ሞት ተከትሎ እንባቸው እየወረደ መግለጫ የሰጡት አቶ ሽመልስ የ200 ሰው ሕይወት በአሰቃቂ ሁኔታ ማለቁ እንዴት  አልተሰማቸውም? ይህንን ያህል ንፁሃን ሕይወት ከጠፋ ገና በአንድ ወር ውስጥ የሰጡት መግለጫ ላይ የተበላሸ እና በአድሎ እና በፅንፈኞች የተበላሸውን አስተዳደራቸውን ለመሸፈን ያልሰሩትን እንደሰሩ ማቅረባቸው እና አሁንም ሕዝብ ከህዝብ የሚለያያ የውሸት የታሪክ ትርክት በመተረክ ለመሸፈን መሞከር ከተጠያቂነት ለማምለጥ የሚደረግ ሙከራ ከመሆን አያልፍም።

=================/////================


"Yoom Darba Laata" | "መቼ ይሆን የሚያልፈው" ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ኦሮሞዎች በሰሞኑ የኦሮምያ ጭፍጨፋ ጉዳት ደርሶባቸዋል። በኦሮምኛ ብሶታቸውን የሚናገሩ ክርስቲያኖችን ቪድዮ ይመልከቱ።

ምንጭ = ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቭዥን ሐምሌ 30/2012 ዓም 
Source =MK TV August 6/2020 


ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com

ከእንቁጣጣሽ በፊት የኢትዮጵያ ሕዝብ እና መንግስት በአንድነት 7 ጉዳዮችን ካሳኩ ለኢትዮጵያ ቀጣይ እርምጃ መንገድ ጠራጊ ነው


የኢትዮጵያ ጉዳይ የመንግስት ብቻ ኃላፊነት ወይንም የሕዝብ ብቻ ጉዳይ አይደለም።ሁለቱ ተናበው እና ተቀናጅተው መስራት አለባቸው።ስለሆነም ከእንቁጣጣሽ በፊት ኢትዮጵያ 7 ጉዳዮችን ሕዝብ እና መንግስት በአንድነት ካሳኩ ለኢትዮጵያ አንድ እርምጃ ነው ብዬ አስባለሁ። 

1) የብሔር ዘውግ ፖለቲካ ለፅንፈኛ አክራሪ እስልምና መጋቢ መሆኑን ማቆም አለበት።ይህ በተለየ መልኩ በኦሮምያ ይታይ እንጂ በሁሉም ክልሎች በተለያየ መጠን አለ።በኦሮምኛ ተናጋሪ ክልል በተለይ በቄሮ ስም የሚንቀሳቀስ አደረጃጀትም ሆነ ስብስብ በፅንፈኛ አክራሪ እስልምና የተጠለፈ መሆኑን በግልጥ መነገር ብቻ ሳይሆን የጥላቻው ዋና አቀጣጣይ መሆኑ መታወጅ እና ወደ ማስተካከል ሥራ መሄድ፣ የክልሉ አመራር የአፈፃፀም አቅሙ ዝቅተኛ በመሆኑ መስተካከል የሚገባው የአስተዳደር አካል በቶሎ መቀየር አለበት።

2) በኢትዮጵያ ከገጠር እስከ ከተማ ሁሉም በየአካባቢው ማኅበረሰቡ እራሱን ከማናቸውም የቡድን ጥቃቶች ለመከላከል አዳዲስ አደረጃጀቶችን መፍጠር አለበት።የጋራ ችግር በጋራ ጥረት ስለሚፈታ።ለእዚህ በቅርቡ የአዲስ አበባ ሕዝብ ያሳየው የጋራ የመከላከል ሥራ ተጠቃሽ ነው።እዚህ ላይ ሕዝብ እራሱ የአካባቢ ጥበቃ መርጦ እንዲያደራጅ መንግስት የመነሻ ሃሳብ እና መተዳደርያ ደንብ ሊያወጣለት ይችላል።ሕዝብ ጠባቂውን ሲመርጥ ማንን እንደሚመርጥ ያውቃል።አደረጃጀቱ ብሔራዊ ስያሜም ያስፈልገዋል።ደርግ አብዮት ጠባቂ፣ኢህአዴግ ሰላም እና መረጋጋት እንዳለ የአሁኑ የለውጥ ኃይልም ለአደረጃጀቱ አዲስ ስያሜ ያስፈልገዋል።

3) በትግራይ ህወሓት አሁን ያሉት አመራሮች በህወሓት ስምም ሆነ አልሆነ ለአዲስ እና የለውጥ ወጣቶች አስረክበው የክልሉ ሕዝብ ከዓማራም ሆነ ከሌላው ሕዝብ ጋር ሲያቃቅሩ የነበሩ ጉዳዮች በቶሎ በዕርቅ እና በኢትዮጵያዊነት መንፈስ መፍታት መቻል አለባቸው። አሁንም ህዝብን ከህዝብ እያጣሉ ያሉት የህወሓት አመራሮች ናቸው።ህወሓት ከምር አሁን ያሉትን መሪዎች በወጣት እና ዘመናዊ አስተሳሰብ በያዙ ወጣቶች መተካት አለበት።

4) አዲስ አበባ የአዲስ አበባን ስነ ልቦና፣ዓለም አቀፍ ማዕከልነት እና ማኅበራዊ መስተጋብር ሁሉ ያገናዘበ ግን ደግሞ እጅግ  ከሁሉም የኢትዮጵያ ሰራዊት በዋናነት ግን ከተሜ የሆነ እና የከተማን ስነልቦና የሚያውቅ ዘመናዊ የሆነ  ልዩ የወታደራዊ-ፖሊስ (ወፖ) በቶሎ ሊኖራት ይገባል።

5) ፈድራሊዝምን የሚያከብር ነገር ግን የጎሳ ፖለቲካን የሚያኮስስ ግልጥ ዘመቻ ህዝብን ማዕከል አድርጎ መከፈት አለበት።ዘመቻው የጎሳ ፖለቲካን እስከመቅበር ግብ ሊያደርግ ይገባል።ዘመቻው ከመገናኛ ብዙሃን እስከ የትምህርት ካሪኩለም ድረስ መዝለቅ አለበት።አሁን ከልብ የመጀመርያው ጊዜ ነው።

6) የህዝቡን ስነ ልቦና፣አብሮነት፣ተስፋ እና ፍቅር የሚያጎለብቱ ልዩ ልዩ መርሃግብሮች መቅረፅ እና ወደ ሥራ መግባት።እዚህ ላይ በሁሉም ክልልሎች የሚጀመሩ የስፖርት ጨወታዎች፣ሕዝብን ወደ አንድ መድረክ እንዲሳብ የሚያደርጉ የጋራ የኪነጥበብ ስራዎች እና መንፈሳዊ አገልግሎቶች ሁሉ በሚገባ ተዘጋጅተው የህዝቡን ስነ ልቦና ከፍ ማድረግ አለባቸው።

7) የኢትዮጵያ ራድዮ እና ቴሌቭዥን የዜና፣የመርሃግብር ይዘት እና የትኩረት አቅጣጫ ለውጥ ማድረግ።
አሁን ያሉት የመንግስት ሚድያዎች የዜና ትኩረት፣የመርሃግብር ይዘት እና የትኩረት አቅጣጫ በገጠርም ሆነ በከተማ ከሚኖረው ሕዝብ ጋር የተሰናሰለ አይደለም።ሃሳቡን በአጭሩ ለመግለጥ፣አሁን ባለንበት ዘመን አደጉ በተባሉ ሀገሮችም የሚታዩ አቀራረቦች አሉ።የመጀመርያው አቀራረብ ለምሳሌ የአንድ ቤተሰብ ውሎ እንዳለ ሳይቀነስ እና ሳይጨመር ማቅረብ።ጧት ሲነሱ፣ልጆች ፊታቸውን ሲታጠቡ፣ሲያወሩ፣ወዘተ እውነተኛው የህዝቡ ስሜት ምንም ያልተጨመረበት ንግግሮች ውስጥ ይነበባሉ።ፍቅር፣ማኅበራዊ ችግሮች፣የመጪው ትውልድ ስሜት ሁሉ በእንዲህ ዓይነት ያልተቀባቡ ግን እንደወረደ በሚተላለፉ ዝግጅቶች ይታወቃል።ያንን ተመልክቶ መተንተኑን ለሕዝቡ ተዉለት።ይህ ምሳሌ ነው።ሌሎቹ ይዘቶች እና ዜናዎች ላይ የገጠሩ ሕዝብ እንዲሰማው ሆኖ ነው የሚቀርበው? ሁሉ መፈተሽ አለበት።የብዙ ችግሮች ውጤት የሚድያዎች የረጅም ጊዜ የተበላሸ አቀራረብ ውጤትም ጭምር ነው።

ሰባቱም ተግባሮች  ከእንቁጣጣሽ በፊት ስራቸው ከግማሽ በላይ መሄድ ይችላል።
==============/////================
ከታሪክ ማኅደር ቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ የእንግሊዟን ንግስት ኤልሳቤጥ ለመጎብኘት ሄደው ያጌጡት በኦሮሞ ፈረሰኛ ጎፈሬ ነበር።

Wednesday, August 5, 2020

የሻሸመኔ፣አርሲ፣ዝዋይ፣ሐረር እና ባሌ የሰሞኑ ጭፍጨፋ እና የንብረት ማውደም ወንጀል ምንጩ፣ዓላማው፣የመንግስት ምላሽ እና በመፍትሄነት ወደፊት መደረግ ያለበት።

በሻሸመኔ ከደረሰው ውድመት በከፊል 

ጉዳያችን ልዩ ወቅታዊ 

ሰሞኑን የድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ ሰኔ 23 እና 24/2012 ዓም በሻሸመኔ፣አርሲ፣ዝዋይ፣ሐረር እና ባሌ በተለየ መልኩ በኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች ላይ የግፍ ግድያ እና የንብረት ማቃጠል ወንጀል ተፈፅሟል።ወንጀሉ  የተፈፀመባቸው በምእራብ አርሲ ዞን በአርሲ ነገሌ እና ዶዶላ ከተማና ወረዳ፣ በሻሻመኔ፣ ኮፈሌ፣ አዳባ ፣ ዶዶላ፣ ሻላ፣ ቆሬ እና አሳሳ ወረዳዎች፣በዝዋይ እና በባሌ አጋርፋ  እና ሐረር ነው።በእዚህም መሰረት እስካሁን ከ200 በላይ ንፁሃን ሲገደሉ በሚልዮን የሚቆጠር ንብረት ወድሟል።ወንጀለኞቹ በመንጋ እየከበቡ ንፁሃንን የገደሉበት አገዳደል ህሊና የሚፈትን ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያዊ መሆን በራሱ ወንጀል ነው የሚል መልዕክት የያዘ እና በቀጥታ ከውጭ የተቀዳ ይመስላል።በተለይ የንብረት አወዳደሙ በራሱ ልዩ ስልጠና የታከለበት እንጂ ተራ የብስጭት ውድመት እንዳልሆነ የዓይን ምስክሮች እማኘንታቸውን እየገለጡ ነው።

የወንጀሉ ምንጭ ምንድነው?

ከላይ በተጠቀሱት ቦታዎች የተፈፀሙት ወንጀሎች ፈጣን ምክንያቱ የሃጫሉን መገደል ያስመስል እንጂ ቀደም ብሎ በሁለት ኃይሎች የታሰበበት ለመሆኑ ምንም አያጠራጥርም።እነኝህ ሁለት ኃይሎች በፈጠሩት ጥምረት እና የመረጃ ልውውጥ መንጋውን ለማንቀሳቀስ ችለዋል። እዚህ ላይ ጥያቄው መንጋው ማን ነው? የመንጋው አንቀሳቃሾች እነማን ናቸው? የሚለው ነው።መንጋው በድምር የሚጠራው አመራሩ እና ቅርፁ በመንጋ መልክ ብቻ እንዲገለጥ የተደረገው ቄሮ በሚል ስም ቢጠራም በመንጋ የሚያንቀሳቅሱት እና የሚመታውን ኢላማ የሚመርጡለት ግን እነኝህ ሁለት ኃይሎች ናቸው።

የመጀመርያው አንቀሳቃሽ በኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ ቅርፁን እና መልኩን ሲቀይር የኖረው የፅንፈኛ የአክራሪ እስልምና እንቅስቃሴ ነው።ይህ እንቅስቃሴ በብሄር ፖለቲካ ውስጥ ተሸጉጦ በኢህአዴግ/ህወሓት ውስጥ ነበር።ይህ እንቅስቃሴ በተቃዋሚ የብሔር ድርጅቶች ውስጥም ነበር። አክራሪው ኃይል በኢትዮጵያ በተለይ በኦሮምያ የፖሊስ እና ቢሮክራሲ ውስጥ መግባቱ ጉልበት ሰጥቶታል።ይህንን ቡድን የህወሓት/ኢህአዴግ ደህንነት በሚገባ ያውቀዋል።ከአስር ዓመት በፊት ይህ ቡድን በአሰላ እና በአዲስ አበባ  ከተማ ውስጥ በግለሰቦች መኖርያ ግቢ  ውስጥ  በሺህ የሚቆጠር ገጀራ ተይዞ ነበር።ተመሳሳይ ድርጊቱ በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎችም ተገኝቷል።ምናልባት አሁን ደግሞ በጦር መሳርያ ንግድ ላይም ተሰማርቶ ይሆናል።

ቡድኑ በተለያዩ ጊዜዎች ቦግ እልም እያለ አመቺ የቀውስ ጊዜዎችን ሲጠብቅ የኖረ ነው። ከአስር ዓመት በፊት በበሻሻ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን ክርስቲያኖች ሲታረዱ፣በአሰቦት ገዳም ተደጋጋሚ ጥቃት ሲፈፀም ሁሉ ህወሓት/ኢህአዴግ ደህንነት የጉዳዩ ፈፃሚዎች ዋና ሽፋናቸው የኢህአዴግ ባለስልትናንነት እንደነበር ይታወቃል።ለምሳሌ በበሻሻ ወንጀሉ ከተፈፀመ በኃላ የሚድያ ሽፋን እንዳያገኝ ብቻ ሳይሆን  ድርጊቱን በቪድዮ ለምን ተሰራጨ? እያሉ ሲያስሩ የነበሩት የድርጊቱ በተዘዋዋሪ ተባባሪ እንደሆኑ የተጠረጠሩት የአካባቢው ባለስልጣናት ግን የኢህአዴግ አጋር ድርጅቶች አባላት ነበሩ።

ከእዚህ የፅንፍ ቡድን ጋር ህወሓት/ኢህአዴግ በስልጣን ላይ እያለች በሁለት መልኩ አጋርነት ነበራት።እነርሱም የመጀመርያው የክልል የመከፋፈል ፖሊሲ ላይ ጥሩ አስፈፃሚ በመሆናቸው እና በሌላ በኩል የኢትዮጵያ አንድነት ትሰብካለች፣መለያየት ትቃወማለች በሚል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን መጨቆን ላይ ስለሚያግዙ ነው።ስለሆነም የህወሓት/ኢህአዴግ አመራር እነኝህ የፅንፍ ኃይሎች በኢህአዴግ አባልነትም ሆነ በአጋርነት ሲደራጁ እና ሃገሩን ሲያምሱ ህወሓት/ኢህአዴግ ታበረታታ ነበር።ደህንነቱ በስልጣን እርከን ላይ እጅግ አደገኛ የሆኑ የፅንፍ እና የሽብር ቡድኖች ከሱማሌ ክልል እስከ ኮፈሌ፣ከቤንሻንጉል እስከ መቱ ሲደራጁ እያወቀ ዝም አለ።ለምሳሌ በሱማሌ ክልል ጅጅጋ የፅንፉ ኃይል ልዩ ኃይሎች ከአዲስ አበባ የመጣ ሰውን መንገድ ላይ አስቁመው መታወቂያ እየጠየቁ ካለምንም ወንጀል ያስሩ ነበር።የህወሓት ሙሰኛ ባለስልጣኖችን እስካልነኩ ድረስ የሌላው ስቃይ ለህወሓት/ኢህአዴግ ደንታ አልሰጣትም።ይልቁንም ህወሓት ጠቅልላ ወደ መቀሌ ስትገባ ይህንን የፅንፍ ኃይል እንደ መቅጫ ዱላ እንደምትጠቀምበት ተማምናበት ነበር።የቀድሞው የደህንነት ሹም አቶ ጌታቸው ሙሉ መረጃው በተለይ በፅንፍ ኃይሉ የሚጠቁ ስስ አካባቢዎችን ያውቃሉ።ስለሆነም ለሀገር ማተራመሻነት ከእነማን ጋር መስራት እንዳለባቸው ሳይወስኑ አልቀሩም።

ካለፉት ሰባት ዓመታት ውስጥ ይህ ለረጅም ጊዜ በኢትዮጵያ ውስጥ የተንሰራፋው የፅንፍ ኃይል የኢህአዴግን መንገዳገድ ከተመለከተ በኃላ ራሱን ይበልጥ ወደውጭ ያሉ የተቃዋሚ ኃይሎች ማስጠጋት ጀመረ።ከተቃዋሚ ኃይሎች ውስጥ የመረጠው ደግሞ በኢትዮጵያ አንድነት የሚያምኑትን ሳይሆን አሁንም በጎሳ ላይ የተመሰረተ ዓላማ ያላቸውን መረጠ።ከብሔርም የመረጠው በልዩ ልዩ ውስጣዊ ውጥረቶች የታወከውን የኦሮሞ የብሔር ዘውግ እንቅስቃሴን ነበር።በእዚህ መሰረት እንደ ተኩስ ማስጀመርያ የጀዋር መሐመድ የዛሬ ሰባት ዓመት በአሜሪካ ያደረገው ''ክርስቲያኖችን በሜጫ በሏቸው'' የሚለውን ንግግር እንደ መክፈቻ ስነ ስርዓት ተጠቀመበት።ጀዋር ይህንን ንግግር ሲያደርግ በአዳራሹ የተሰበሰቡ በፅንፍ ፖለቲካ አራማጅነት የሚታወቁ እና በአሜሪካ ነዋሪ የሆኑ ግለሰቦች እያደነቁ ራሳቸውን ከላይ ወደታች ሲነቀንቁለት ይታይ ነበር።

የፅንፍ አክራሪ እስልምና እንቅስቃሴ ኢህአዴግ/ሕወሃት እየደከመ መሆኑን ሲያውቅ ወደ ተቃዋሚው ጎራ በድንገት የገባ አይደለም።ቀድም ብሎ ወደ ኢህአዴግ/ህወሓት ስልጣን ሲጠጋ መውጫውን አዘጋጅቶ ነበር።ጀዋር የኦህዴድ አባል ብቻ ሳይሆን ወደ ውጭ ሀገር ለትምህርት ሲሄድ የድጋፍ ደብዳቤ ሁሉ ያገኘው ከኢህአዴጉ አባል ድርጅት ኦህዴድ ነው።ጀዋር ከኢትዮጵያ እንደወጣ ወደ ሩቅ ምስራቅ መሄዱን ቢነግረንም በእርግጥ ለስልጠና በወቅቱ የት ሀገር እንደነበረ የሚያውቀው እርሱ ነው።

የፅንፍ ኃይሉ በኦሮሞ ሕዝብ ውስጥ መሸጎጡ በተለይ የኦርቶዶክስን እና የኢትዮጵያ ሕብረትን በልዩነት የሚደግፈውን ሕዝብ ለመምታት ይመቻል በሚል እንደ ለም የዓላማ ማስፈፀሚያ የተመረጠው በተለያዩ ቡድኖች የተከፋፈለው የኦሮሞ ብሄርተኝነት ሆኖ ተገኘ።ይህ የፅንፍ ቡድን የሚያሽከረክረው በቄሮ ስም የተሰበሰበው ወጣት ይህንን ሁሉ ጉድ አያውቅም።የሚገርመው የቄሮ እንቅስቃሴ በሚደረግባቸው ቦታዎች ሁሉ ብዙ መንጋ ለማሰባሰብ የፅንፍ ቡድኑ እራሱን ደብቆ በቄሮ ውስጥ እንዳለ ሁሉ በኢህአዴግ/ህወሓት የፀጥታ አካልም ውስጥ ሆኖ ከፍተኛ እልቂት እንዲፈፀም ይሰራ ነበር።

እዚህ ላይ ከአምስት ዓመት በፊት በእዚህ በጉዳያችን ላይ እንደተገለጠው የቄሮ ኃይል በስለጠነ መልክ እንዳይደራጅ የሚፈልገው ይሄው የፅንፍ ኃይል ነው። ጀዋር በተደጋጋሚ የቄሮን አደረጃጀች ላይ ሲጠየቅ አድበስብሶ የሚያልፈው ቄሮ እንዲደራጅ እና ወደ የዜግነት ኃላፊነት የሚወስድ ኃይል እንዳያድግ ስለማይፈልግ እና ስውሩ የፅንፍ እና የጀሃድ ኃይል እየመራው እንደሆነ ስለሚያውቅ ነው።ለእዚህ አብነት መጥቀስ ይቻላል።በኦሮምያ ሚድያ ኔት ዎርክ ውስጥ የተፈጠረው ሹክቻ እና ጀዋር የፈታበት መንገድ ነው። ከለውጡ በፊትም ሆነ በኃላ በኦኤምኤን ውስጥ የተፈጠረው ሹክቻ የፅንፍ ጀሃዲስት አስተሳሰብ የሚያራምዱ እና የኦሮሞ ብሔር ዘውግ በሚያራምዱ መሃል የተፈጠረ ነበር።ከለውጡ በፊት ኦኤምኤን ጥለው የሄዱት ጋዜጠኞች እና የቦርድ አባላት መሃል እና በጀዋር የአርሲ የፅንፍ ቡድን መሃል የነበረው ልዩነት ምን እንደነበር በወቅቱ የወጡት የፃፉትን ማገላበጥ በቂ መረጃ ነው።ከለውጡ በኃላም ዋናው የፅንፈኛው ቡድን በውጭ እንዲቆይ አድርጎ ወደ ሀገር ቤት የገባው ከፊት የዘውግ አክራሪ መስሎ በውስጥ ግን የሚዘወረው በፅንፍ የጀሃዲስቶች ቡድኖች ነበር።

ሰሞኑን በአርሲ፣ባሌ፣ሻሸመኔ እና ሌሎች አካባቢዎች የተፈፀሙት የጭካኔ ግድያዎች እና የንብረት ማውደም ተግባር ዋና ምንጭ የእዚህ የፅንፍ ኃይል አሁንም በኦሮሞ ብሔር የዘውግ እንቅስቃሴ ውስጥ ተሸሽጎ እና እግሮቹን በመንግስት ቢሮክራሲ እና የፀጥታ መዋቅር እንዲሁም በተቃዋሚዎች ላይ አንሰራፍቶ የፈፀመው ተግባር ነው።ይህ ቡድን ከእዚህ በፊት ህወሓት/ኢህአዴግ በስልጣን ላይ እያለ የኢህአዴግ/ህወሃትን ስልጣን እስካልተጋፋ ድረስ በስውር እና በግልጥ ሲደገፍ የነበረ ሲሆን በሰሞኑ ግን የፅንፍ ኃይሉ እና ህወሓት በግልጥ የጋራ ስልት ቀይሰው በሰው ኃይል፣በገንዘብ እና በፕሮፓጋንዳ ጭምር እየተጋገዙ የሄዱበት የወንጀል ድርጊት ነው።

እዚህ ላይ የህወሓት በቀጥታ በጉዳዩ ላይ ለመግባት አሳማኝ ጉዳዮች ለማንሳት ሁለት ነጥቦችን ማንሳት ይገባል።የመጀመርያው የህዋሃት ፕሮፓጋንዳም ሆነ የውስጥ መልዕክቶች በተለይ በሻሸመኔ እና በዝዋይ የሚኖሩ የድርጅቱ አባላት ሆኑ ባለሀብቶች ለቀው እንዲወጡ ሲወተውቱ ነበር የከረሙት።ጀዋር እና በቀለ ገርባም ከድርጊቱ ሁለት ሳምንታት በፊት በተደጋጋሚ ወደ ስፍራው መሄዳቸው የአካባቢው ነዋሪዎች የሚያውቁት ነው።በሁለተኛ ደረጃ ህወሓት በኢትዮጵያ ትልቅ ጥፋት ይፈጠራል በማለት በሚድያዋ ብቻ አይደለም የለቀቀችው ከእዚህ ባለፈ ግብፅ እና ሱዳንን ጨምሮ ለበርካታ መንግሥታት ደብዳቤ ልካለች።በደብዳቤው ከሰሞኑ ''እኔ ያልኩት ካልሆነ ታዩታላችሁ'' መሰል መልዕክት የያዘ ነበር።ወንጀሉ በተፈፀመ ቀንም ሆነ በኃላ የህወሓት ሚድያዎች ሰፊ ሽፋን የሰጡት ለእዚሁ የፅንፍ ኃይል ከመሆኑ በላይ የኦሮምያ ሚድያ ኔት ዎርክ የሚያስተላልፈውን የመንግስት ንብረት አውድሙ መልዕክት በቀጥታ የስርጭት ሽፋን ጭምር በማስተላለፍ የወንጀሉ ተባባሪ ሆናለች።

ስለሆነም የችግሩ ዋና ምንጭ በኦሮሞ የብሔር ዘውግ ፖለቲካ ውስጥ የተደበቀው የቆየው የፅንፍ ጀሃዲስት ቡድን ሲሆን አጃቢዎቹ የዘውግ አራማጆቹ እና ህውሓት እራሷም ነች።ይህ በእንዲህ እያለ ግን የቅርቡ መልካም ክስተት የቄሮ እንቅስቃሴ እራሱን ከህወሓት ተንኮልም ሆነ ከጀሃድስት ቡድኑ እራሱን እያገለለ እና እየተሰራ የነበረውን ተንኮል እያወቀ መምጣቱ ነው።ለእዚህ ምስክሩ ደግሞ በቅርቡ የጀሃድስት ቡድኑ እንደለመደው በኦሮሞ የብሔር ፖለቲካ ውስጥ ተሸሽጎ የጠራው የአመፅ ጥሪ ከአንዴም ሶስቴ መክሸፉ ነው። በእዚህም የጀሃድስት ቡድኑ ለብቻው እየቀረ መሆኑን እንመለከታለን።አሁን የጀሃድስት ቡድኑ ዋና የትግል ግንባር ያደረገው የውጭ ሀገሮችን ሲሆን በውጭ ሀገሮች ''ኢትዮጵያ ትውደም'' የሚል መፈክር ከዱባይ እስከ ጀርመን ጀለዎቹን እያሰለፈ በመጮህ ላይ ይገኛል።ለእዚህ ዓይነቱ ድርጊት ደግሞ የውጭ መንግሥታትም ዝም አላሉም።በዱባይ ኢትዮጵያን ያጥላሉት የተባበሩት አረብ መንግሥታት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚልካቸው መወሰኑ በቅርቡ ተሰምቷል።

የወንጀሉ ዓላማ ምንድነው?

የወንጀሉ ዓላማ ሶስት ናቸው። እነርሱም 
1) ክርስቲያኖችን ምጣኔ ሀብታቸውን ማውደም እና ማደህየት በእዚህም በተፅኖ ስር እንዲወድቁ ማድረግ፣

2) ሁለተኛው ደግሞ ክርስቲያኖችን በመግደል እና የስነ ልቦና ተፅኖ በመፍጠር እንዲሰደዱ በማድረግ  አካባቢውን በፅንፍ ጀሃዲስቶች ቁጥጥር ስር ማዋል እና 

3) በሶስተኛ ደረጃ የኢትዮጵያን መልክ፣ታሪክ እና ማንነት ደምስሶ በአዲስ የጀሃዳዊ ታሪክ እና መንግስት መቀየር ናቸው።

እነኝህን ሁሉ ለማስፈፀም ግን ጀሃዲስቱ ቡድን በብሄር ፖለቲካ ስር ይሸጎጣል።ነገ ሌላ ዓይነት ፖለቲካ ቢመጣም በእዛ ስር ሆኖ ዓላማውን ለማሳካት የማያፍር እንደ እስስት እራሱን የሚቀያይር ለመሆኑ ያለፉ ታሪኮቹ ያሳያሉ።

የመንግስት ምላሽ 

ወንጀሉን ተከትሎ መንግስት የወሰደው እርምጃ እንደ ሻሸመኔ ያሉ ከተሞች ሙሉ የካቢኔውን እና ከንቲባውን ከማሰር ጀምሮ በሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ጀዋር እና በቀለ ገርባን ጨምሮ አስሯል። ለምሳሌ እንደ ፋና ዘገባ በ10 ወረዳዎች በደረሰ የሰው ህይወት መጥፋት፣ የአካል ጉዳት እና የንብረት ውድመት ወንጀል የተጠረጠሩ 1 ሺህ 168 ሰዎች ፍርድ ቤት ቀርበዋል።70 ተጠርጣሪዎች ሃምሌ 13 ቀን በወረዳ ፍርድ ቤቶች ቀርበው የጠየቁት ዋስትና ለጊዜው ወድቅ ተደርጎ ለመርማሪ ፖሊስ የወደመና ጉዳት የደረሰ ንብረትን በባለሙያ ለማስገመት እና በሰው ላይ የደረሰውን ጉዳት የህክምና እንዲሁም ህይወታቸው ያለፉትን የአስከሬን ምርመራ እና የምስክሮችን ቃል ለመቀበል ተጨማሪ ምርመራ ለማድረግ ፍርድ ቤቶቹ ለፖሊስ 14 ቀን ፈቅደዋል።

ከእዚህ በተጨማሪ የኦሮምያ ልዩ ኃይል ኃይል እና የፌድራል ፖሊስ የፀጥታ ሥራ በመስራት ላይ ናቸው።ለምሳሌ ከእዚህ በፊት መንገድ ይዘጉ የነበሩ ወጣቶች አሁን ካለምንም ይቅርታ የፀጥታው ኃይል እርምጃ ይወስዳል።ለምሳሌ በያዝነው ሳምንት በዶሎ መና ተመሳሳይ ድርጊት ሊፈፅሙ የሞከሩት ላይ ሰራዊቱ ወዲያው ደርሶ እርምጃ ወስዷል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይም በፓርላማም ሆነ ተፎካካሪ ፓርቲዎችን ሲያነጋግሩ የሕግ ማስከበር ሂደቱ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።በአቃቢ ሕግ በኩልም ተከታታይ ሕግ የማስከበር ተግባር እንደሚቀጥል መግለጫዎች ተሰጥተዋል።በእዚህ እርምጃ መንግስት ዘግይቶም ቢሆን ወደ ሕግ የማስከበር ተግባር በቁርጠኝነት መግባቱን ማሳየቱ ሊበረታታ የሚገባ እና ሁሉም አብሮት ሊቆም የሚገባ ጉዳይ ነው።

እነኝህ እርምጃዎች ሁሉ ግን አንድ ነገር ይጎድላቸዋል።ይሄውም በደረሰው ሰቆቃ በሚመጥን ልክ መንግስት በፌድራልም ሆነ በክልል ደረጃ ሃዛኑን አልገለጠም።እርግጥ ነው በክልልም ሆነ በፌድራል ደረጃ ያሉ ኃላፊዎች የወንጀሉ አሰቃቂነት ሳይሰማቸው ቀርቶ ነው ለማለት ያስቸግራል። ግን ሕዝብ አሁን እየጠየቀ ያለው በተለይ ጥቃቱ ኦርቶዶክሳውያንን ዓላማ አድርጎ ከመፈፀሙ አንፃር የክልሉ ፕሬዝዳንትም ሆኑ በየደረጃው ያሉ ባለስልጣናት የሃጫሉ ሞት ተከትሎ የገለጡበት ድምፀት ልክ ከሁለት መቶ በላይ ክርስቲያኖች የተገደሉበትን አረመኔያዊ ድርጊት በሚመጥን ደረጃ አለማውገዛቸው የህዝቡ መነጋገርያ አጀንዳ ነው።በእዚህም አሁንም የፅንፍ የጀሃድስቱ አካል ከወረዳ ባለስልጣን እና ፖሊስ ኃይል ባለፈ በመንግስት መዋቅር ውስጥ አለ ወይ? የሚል ግዙፍ ጥያቄ ጭሯል።ለእዚህም አሁንም መንግስት ውስጡን እስከ ወረዳ ድረስ የማጥራት ስራውን እንደጀመረው መቀጠል አለበት። ጉዳዩ የሀገር ህልውና ጉዳይም ነው።

ወደፊት ምን ይደረግ? መፍትሄውስ?

የችግሮች ሁሉ መፍትሄ መነሻ በመጀመርያ የችግሩን ምንጭ እና መነሻ ማወቅ ነው። ጉዳያችን የኦሮሞ የብሄርተኝነት የዘውግ ፖለቲካ በፅንፍ ኃይሎች መጠለፉን ከአምስት ዓመት በፊት አውስታለች።አንዳንዶች የችግሩ ዋና መሰረት የጎሳ ፖለቲካው ብቻ እንደሆነ ያስባሉ።የጎሳ ፖለቲካው በርግጥ ለስላሳ መሬት ለጀሃድስቱ ከፍቶለታል።ለእዚህም ነው የጎሳ ፖለቲካን እየኮተኮተ ለማሳደግ የጀሃድስቱ ቡድን ላይ እና ታች የሚለው።በተከፋፈለ ሀገር ላይ ጀሃድ ማካሄድ ስለሚቀለው።

በኢትዮጵያ የተከሰተው የፅንፍ ጀሃዲስቶች እንቅስቃሴ በሌሎች ሀገሮች ውስጥ ሲከሰት በነበረው የፖለቲካ ሂደት ውስጥ ተደብቆ የመሄዱ ባህሪ የተለመደ ነው።በግብፅ ሙባርክን ከስልጣን ለማውረድ የእስላማዊ ወንድማማቾች ቡድን አብሮ የትግሉ አካል ከሆነ በኃላ ውደ ስልጣን ለመምጣት የሞከረው ፍፁም ዲሞክራሲያዊ በመሰለ የምርጫ መንገድ ነበር።ይህ ሂደት ግን ዋና ፊቱን ለመደበቅ አልረዳውም።በኢትዮጵያም በቄሮ እና በኦሮሞ የዘውግ ፖለቲካ ውስጥ ተደብቆ ኢትዮጵያን ለማመስ የተነሳው የጀሃድስት ቡድን አሁን ከምንጊዜውም በበለጠ ተጋልጧል። 

በአምቦ መቀመጫቸውን ያደረጉት የኢትዮጵያ ኦሮቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ጳጳስ ከአዲስ አበባ ወደ አምቦ እንዳይገቡ ችግር ሊፈጥር በሞከረው ቡድን ዙርያ አምቦ ላይ ወጣቶች ተሰብስበው ሲመክሩ የሄዱበት መንገድ አስተማሪ ነው።አምቦ ከአምስት ወራት በፊት በነበረ ስብሰባ ላይ ማን ነው አቡኑ እንዳይመጡ ያገደ? የሚል አውጣጭኝ ላይ የተነሳው እና እርሱን ተከትሎ ለመሆኑ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቄሮ የላትም ወይ? የሚሉት ጥያቄዎች ነበሩ።በስብሰባው ላይ የተነሳውን ጥያቄ ለመመለስ በመቶዎች የሚቆጠሩ የቤተ ክርስቲያኒቱ ልጆች ግን በቄሮ ትግል ውስጥ የተሰለፉ እኛ ኦርቶዶክሳውያን ነን ደሞ ቄሮ ነን።ነገር ግን ይህንን አባታችንን እንዳይመጡ የሚከለክል ማን እንደሆነ አናውቅም! በማለት መለሱ። በመቀጠል ከውስጣቸው የጀሃድስቶች ሥራ መሆኑን ተማምነው እና ይህንን ለመዋጋት ወስነው ጳጳሱ በክብር በወጣቶቹ ታጅበው አምቦ ገብተዋል።

በመጨረሻም ወደፊት ሊደረግ ስለሚገባው ወደ የመፍትሄው ሃሳብ ስንሄድ የሚከተሉት ወሳኝ ተግባራት ሊተኮርባቸው ይገባል። እነርሱም -

1) ሕዝብ ሙሉ በሙሉ እራሱን የመከላከል መብት እንዳለው እና እራሱን ለእዚህ ተግባር በህብረት በመቆም እራሱን ማስከበር አለበት።ከአሁን በኃላ የለቅሶ እና የሃዘን እንጉርጉሮ ማንንም አይጠቅምም።ኢትዮጵያ የእኔም ነች ማንም ከሕግ ውጪ እንዲገፋኝ አልፈቅድለትም የሚል ጠንካራ ስነ ልቦናዊም ሆነ የጋራ ዝግጅት ያስፈልጋል።

2) መንግስት የፀጥታ አካላት፣የወረዳ እና የቀበሌ ኃላፊዎች ጭምር ከጀሃድስት እና የጎሳ ፅንፍ የፀዱ መሆናቸውን ማረጋገጥ እና የአካባቢ ሚሊሻ በአዲስ መልክ የሁሉንም ነዋሪ ተዋፅኦ በትክክል ባሳተፈ መልኩ ማደራጀት አለበት።

3) ሕይወታቸው ለጠፋ እና ንብረታቸው ለወደመው ሁሉ መንግስት ከህዝብ ሀብት አሰባስቦም ቢሆን ሁሉንም መልሶ የመርዳት እና ወደነበረ ኑሯቸው መመለስ መቻል አለበት።

4) የወንጀሉ አፈፃፀም፣እነማን እንደፈፀሙ  እና ከጀርባ ያሉ ኃይሎች ሁሉ የያዘ የተሟላ ሪፖርት መንግስት  ለሕዝብ ግልጥ ማድረግ አለበት። ይህ ለወደፊቱ ሕዝብ ጠላቱን ለይቶ እንዲያውቅ ይረዳል።

5) በከፍተኛ ባለሙያዎች የታገዘ ህዝብን የሚያቀራርቡ የአካባቢ ችግሮች ላይ ያተኮሩ አዳዲስ የመገናኛ ብዙሃን ያስፈልጋሉ።ለምሳሌ ለአርሲ፣ለባሌ፣ለሻሸመኔ፣ሐረር ወዘተ ቦታዎቹን በልዩ ሁኔታ ያተኮሩ ዜናዎቹ በጣም የአካባቢውን የዕለት ከእለት  ተግባራት ላይ ያተኮሩ እና የአካባቢውን ሕዝብ ጆሮ የሚስቡ ነገር ግን በማዕከል በብሮድካስት ኮርፖሬሽን ቁጥጥር ሚድያዎች ያስፈልጋሉ።ምድያዎቹ ኤፍኤም ራድዮኖች ቢሆኑ በተለይ ለአካባቢው ገጠር ስለሚዳረሱ በከተሞቹ እና በአካባቢ ገጠሮች መሃል ያሉ ልዩነቶችን  ያጠባሉ፣ማኅበራዊ ትስስሮችን ያጠነክራሉ።

የእዚህ ዓይነት ሚድያዎች በተለይ በሰለጠኑ ሀገሮች በጣም ይጠቀሙበታል።የአካባቢ ሚድያ እና ጋዜጦች በዝርዝር በመንደሩ የዕለት ከእለት ጉዳይ ላይ ስለሚያተኩሩ ያላቸው ማኅበራዊ መስተጋብር እና እርቅ የመፍጠር አቅማቸው ሁሉ በቀላሉ የሚታይ አይደለም።በተለይ እነኝህ ሚድያዎች በአካባቢው የሚኖሩ  መልካም ግለሰቦች ሃይማኖት እና ብሔር ሳይለዩ ስለሚያስተዋውቁ መከባበሩ ይጠነክራል።ሰሞኑን እንደተገደሉ የምንሰማው መልካም ሰዎች ቀደም ብሎ በነበሩ የአካባቢ ሚድያ ለገጠሩም ሆነ ለከተሜው ቢነገር ኖሮ መተዋወቁ በተፈጠረ ጀሃድስቶቹም ለመግደል ባልቻሉ ነበር። 
 
6) ሕዝብ አካባቢውን በደንብ የመቃኘት አቅሙን ማሳደግ።በአካባቢው የሚኖሩ ከመስመር የወጣ አካሄድ ያለባቸው ላይ ትኩረት የማድረግ እና የማረቅ አቅሙን ማሳደግ።

7) የተበጠሱ እና የላሉ ማኅበራዊ ዕሴቶች መቃኘት፣ማጠናከር እና ማዳበር 

8) የወጣት ማኅበራት ኃላፊነት እንዲወስዱ ማድረግ።ከስነ ምግባር ውጪ የሆኑትን በህጋዊ ቅጣትም ሆነ በምክር ማረቅ።

9) የማክሮ ኢኮኖሚው በዋናነት በሥራ ዕድል ላይ እና በገቢ ልዩነት ማጥበብ ላይ መስራት እና 

10) የትምህርት ካርኩለሙ ለጀሃድስቶች እና ለፅንፍ ብሄርተኞች እንዳይመች አድርጎ መከለስ፣መምህራን በክፍል ውስጥ የሚሉት ሁሉ  ከፅንፍ መስመሮች የወጣ መሆኑን ማረጋገጥ እና ተማሪዎች አካባቢያቸውን የምጎበኙበት መርሃ ግብር እንዲኖር ትምህርት ቤቶች ከማስተማር ሂደቱ ውስጥ እንዲያስገቡ ማድረግ የሚሉት ለአጭር እና ለረጅም ጊዜ የሚረዱ የመፍትሄ ሃሳቦች ናቸው። 
=======================////=================

Monday, August 3, 2020

በትግራይ እና በኦሮሞ ሕዝብ ስም የሚነግዱ የስልጣን ጥመኛ ቅንጡዎች አስቂኝ ጥሪ - እባካችሁ!ለስልጣናችን ሙቱልን!

አሲምባ ገስት ሃውስ መቀሌ  

ቅንጡዎቹ ሶስት ቦታዎች ሆነው ወጣንበት የሚሉትን ብሔር ድረስልን እያሉ ነው።አንድኛው መቀሌ የሚገኘው የትህነግ የአዛውንቶች አመራር ነው።ይህ ቡድን በግንብ በታጠረ ምቹ ቤት ውስጥ ተቀምጠው የተቀሩት ደግሞ በመቀሌ እና አድዋ ሆቴሎች ውስጥ ውሎ እና አዳራቸውን አድርገው ነው ምስኪኑን የትግራይ ሕዝብ ከቀረው ወገኑ ጋር እንዲጋጭ የሚወተውቱት።እነርሱ እና ልጆቻቸው በጣታቸው ሊነኩት የማይፈልጉትን ጦርነት ወጣቱ የነገ ተስፋው ጨልሞ፣ ምክንያቱ እና ግቡ በማይታወቅ የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ገብቶ እንዲያልቅ መወትወቱን ይዘውታል።የተቀሩት የአዛውንቶቹ ፍርፋሪ የለመዱት እና ከዘረፋ እስከ ልዩ ልዩ ወንጀሎች ውስጥ የተነከሩት ደግሞ በአውሮፓ እና አሜሪካ ተቀምጠው በማኅበራዊ ሚድያ በትግራይ ሕዝብ ላይ የሚሰራውን ወንጀል ለመሸፈን ሲሞክሩ እና እነርሱም ለአዛውንቶቹ ስልጣን ሙቱላቸው እያሉ መማፀኑን ተያይዘውታል።

ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ የትግራይ ሕዝብ እስከ ታች ወረዳ ድረስ ጦርነት የመጣበት በማስመሰል ሲያምሱት ነው የከረሙት።በአስተዳደር በደል የመጣውን የኑሮ ውድነት የጦርነት ኢኮኖሚ ውስጥ ስለሆነ የመጣ በማስመሰል ሲያታልሉት ሰንብተዋል።ትናንት ሐምሌ 26/2012 ዓም ደግሞ የትግራይ ልዩ ኃይል በመቀሌ ስታድዮም በማሰለፍ እና ሕዝብ በግድ ወደ ስታድዮሙ እንዲመጣ እና ለወቅቱ የኮሮና ወረርሽኝ በማጋለጥ ሽብር ሲነዙበት ውለዋል።

በሌላ በኩል በኦሮሞ ሕዝብ የሚነግዱት ፅንፈኛ ቅንጡዎች በአሜሪካ፣አውስትራሊያ እና አውሮፓ ተቀምጠው መንገድ ዝጉ፣የመንግስት መስርያቤቶች አቃጥሉ፣ጎማ አተንፍሱ፣ከእገሌ ብሔር ብቻ እንጀራ ግዙ፣ከቻላችሁ እንጀራ አትብሉ እያሉ እነርሱ በቅምጥል ከሚኖሩበት አውሮፓ፣አሜሪካ እና አውስትራሊያ ተቀምጠው ድሃውን የኦሮሞ ትውልድ ሕልሙን ለማጨለም እና እነርሱ ወደ ፅንፍ አስተሳሰብ በተመራ መንገድ ለስልጣን እንዲበቁ ተንበርክከው የመለመን ያህል እየተማጠኑ ነው።

ሁለቱም በኦሮሞ እና የትግራይ ሕዝብ የሚነግዱ ቅንጡዎች ግንባር መፍጠር ደግሞ አስገራሚው የወቅቱ ድራማ ነው።ድራማውን የሚጫወቱት ደግሞ ሁለቱም የተመቸ ቤታቸው ውስጥ ሆነው ልጆቻቸውን ደግሞ በውጭ ሃገራት ልከው እያስተማሩ ነው። መቀሌ ውሃ ለመቅዳት ጀርካል ኮልኩሎ የሚጠብቀው ሕዝብ፣ሽሬ ላይ አንድ እንጀራ ለማግኘት የምትዋትተው እናት፣ኦሮምያ ያለው የስራ አጡ ከተሜ ወጣት እራሱን ለማውጣት የሚያደርገው መፍጨርጨር  ሁሉ ለቅንጡዎቹ አይሰማቸውም። እነርሱ በድሃው ደም እና በአዲሱ ትውልድ ተስፋ ላይ ተረማምደው የስልጣን ጥማቸውን ማርካት ብቻ ነው ግባቸው።

ባጠቃላይ የትሕነግም ሆነ በኦሮሞ ስም የሚነግዱት የፅንፍ ኃይሎች በጋራ ያገናኛቸው የፖለቲካ ፕሮግራም አይደለም።የጋራ መገናኛ ነጥባቸው የስልጣን ጥማት እና ኢትዮጵያን ለማፍረስ ያላቸው ከንቱ ሕልም ብቻ ነው።የቅንጡዎቹ እባካችሁ ለልስጣናችን ሙቱልን ልፈፋ የሚሰማ ወጣት የለም።የትግራይም ሆነ የኦሮምያ ወጣት በጋራ በምትገነባ ሀገር ውስጥ ያለ ዘለቄታነት ያለው የጋራ ጥቅም የበለጠ እንደሆነ ያውቃል።ስለሆነም በመጀመርያ ለጥርያችሁ ምላሽ ባለመስጠት ተቃውሞውን ይገልጣል።በመቀጠል ጭቅጨቃቹ አላቆም ካለው በእናንተው በቅምጥሎቹ ላይ ይነሳል።ይህ መሆኑ አይቀርም የጊዜ ጉዳይ ነው። 

============================