ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Saturday, November 28, 2020

የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እና የትግራይ ሕዝብ ታሪክ ሰርተዋል! አሁን ርዝራዥ ህወሓት ማኅበራዊ ሚድያው ላይ ሊያስነሳቸው የሚችላቸውን ሶስት ቀዳዳዎች ቀድመን እንወቅ!

ዛሬ ህዳር 19/2013 ዓም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ከ600 ኪሎሜትር በላይ በእግሩ ተጉዞ የመቀሌ ከተማ እና የትግራይ ክልልን ከህወሓት ነፃ አውጥቷል።ይህ ድል የትግራይ ሕዝብ ህወሓት እንደሚለው ሳይሆን ለዲሞክራሲ፣ለፍትሕ እና ለእኩልነት ያለውን ፅኑ ፍላጎት የመከላከያ ሰራዊቱን በማክበር አሳይቷል።በእዚህም የትግራይ ሕዝብ ባለፉት 25 የዘመቻ ቀናት ውስጥ ድምፁን ከፍ አድርጎ ለኢትዮጵያ ሕዝብ አሰምቷል።ከሁሉም ደግሞ ነፃነቱ  በነፃ አውጪ የመጣ ሳይሆን የሁሉም የጋራ በሆነው በመከላከያ ኃይል መምጣቱ እንደሀገር ትልቅ ቁም ነገር አለው።በእርግጥ በእዚህ ዘመቻ ላይ የዓማራ እና የአፋር ልዩ ኃይሎች ቢካፈሉም በዋናነት የመከላከያ ሰራዊት የመራው እና ያጠናቀቀው መሆኑ እንደ ሀገር ትልቅ መልዕክት አለው።ይህንን ለመዘርዘር ብዙ ማለት ይችላል።አሁን ጊዜ ስለሌለ አልፈዋለሁ።

አሁን ርዝራዥ ህወሓት ማኅበራዊ ሚድያው ላይ ሊያስነሳቸው የሚችላቸውን ሶስት ቀዳዳዎች ቀድመን እንወቅ! እነርሱም 

1ኛ) በዓማራ ስም የማኅበራዊ ሚድያ በመክፈት ዓማራ አሸነፈ በሚል የሚፎክሩ ድምፆች በማብዛት የትግራይን ሕዝብ ለማበሳጨት መሞከር፣

2ኛ) በኦሮሞ ስም በተከፈቱ ማኅበራዊ ሚድያዎች ስም በዓማራ ላይ የሚፎክሩ ድምፆች ማብዛት እና 

3ኛ) በመንግስት ባለስልጣናት በተለይ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ ከቀድሞ የበለጠ ዘመቻ ማካሄድ የሚሉት ናቸው።

ስለሆነም ከላይ የተጠቀሱትን ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ሁሉም ጥንቃቄ ከማድረግ ባለፈ መሬት ላይ መሰራት ያለባቸው፣የሕዝብ ስሜት፣ሃዘን፣መቃቃርን የሚያርቁ ስራዎች ላይ በቶሎ መሰማራት አስፈላጊ ነው።

ይህ በእንዲህ እያለ  ለኢትዮጵያ ብዙ የመሰከሩ፣የተሰደዱ እና የተሰዉላት ምስጋና እንደሚገባቸው ሳንረሳ፣ዛሬ  ኢትዮጵያ ባለችበት ፈታኝ ጊዜ ለሰጡት ብቃት ላለው አመራር ለጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ታላቅ ምስጋና ይገባቸዋል። 

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ 







Thursday, November 26, 2020

Ethiopian Government has already started to provide humanitarian aid to internally displaced people in Tigray Region

Gudayachn News

Ethiopian Government today announces providing Humanitarian aid to the Tigray region under the control of the National army, has already started.The latest press release from the Prime Minister, Abiy Ahmed's office explained that the emergency food,drinking water, medicines and other non-foodstaf items are also providing to internally displaced people in the region.


The  PM press release  in Amharic also elaborated, the special committee from different Federal offices is currently on action and as the result four refugee camps are establishing.


The latest press release concluded its statement by emphasizing  as the government is highly interested to cooperate and coordinate its humanitarian works with all aid organizations including the United Nations agencies.



በትግራይ ክልል የመከላከያ ሠራዊቱ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች የሰብአዊ እርዳታ እየቀረበ ነው፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት
*************

በትግራይ ክልል የመከላከያ ሠራዊቱ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች የሰብአዊ እርዳታ እየቀረበ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት አስታወቀ።

የፌዴራል መንግስት በትግራይ ክልል ለሚገኙ ዜጎች የሚያስፈልገውን የሰብአዊ እርዳታ ለማድረስ ትኩረቱን ሰጥቶ እንደሚሰራም አስታውቋል።

መንግስት በቀጣይም ከአጋር ለጋሽ ድርጅቶች ጋር በመተባበር የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው ያስታወቀው።

በክልሉ በተለይ ከመኖሪያቸው ለተፈናቀሉ ዜጎች የሚያስፈልጋቸውን ድጋፍ በአፋጣኝ ለማድረስ የሰላም ሚኒስቴር ከሌሎች የፌዴራል ተቋማት ጋር በጋራ እየሰሩ መሆኑ ተገልጿል።

በዚህም የምግብ፣ የመጠጥ ውሃ፣ መድሀኒት እና ሌሎች ምግብ ነክ ያልሆኑ አቅርቦቶችን የፌዴራል መንግስቱ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች በመጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ ለሚገኙ ተፈናቃዮች ማቅረብ ተጀምሯል።

በስፍራው በአሁኑ ወቅት ስደተኞችን ተቀብሎ ለማስተናገድ የሚሆኑ አራት መጠለያ ጣቢያዎች ለማቋቋም እየተሰራ ሲሆን ይህን ለማስተባበር የተቋቋመው ኮሚቴም ዜጎችን በፍቃዳቸው መልሶ ለማቋቋም እንደሚሰራ ተገልጿል።

መንግስት የተሰደዱ ኢትዮጵያውያንን መልሶ ለማቋቋም እና የተባበሩት መንግስታት ኤጀንሲዎችን ጨምሮ ከሁሉም ዓለም አቀፍ የተራድኦ ድርጅቶች ጋር በጥምረት ለመስራት ያለውን ቁርጠኝነት አረጋግጧል።

Wednesday, November 25, 2020

ቢቢሲ እንግሊዝኛ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ያላሉትን ለጥፎ የኢትዮጵያ የመረጃ ማጣርያ ያዘው Ethiopian Gov't Fact-Checker Accuses BBC of Disinformation for Misquoting Prime Minister

Please find the English version under the Amharic.

ቢቢሲ እንግሊዝኛ  ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ያላሉትን ለጥፎ የኢትዮጵያ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ማጣርያ ያዘው።ቢቢሲ ከየት እንዳመጣው ባልታወቀ ፅሁፍ ላይ በገፁ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ''የፈለገው ይሙት'' አሉ የሚለውን የውሸት ዜና ጨምሮ በገፁ ላይ ለጥፎ የነበረ ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስት መረጃ ማጣርያ ከደረሰበት እና ውሸቱን ካጋለጠ በኃላ ከገፁ ላይ ማንሳቱ ለማወቅ ተችሏል።ለንፅፅር ቀደም ብሎ ተለጥፎ የነበረው ዜና እና የመንግስት መረጃ ማጣርያ ሐሰት መሆኑን ጠቅሶ የፃፈውን ከስር ይመልከቱ።

The Ethiopia State of Emergency fact-checker today accused BBC’s Monitoring service for spreading disinformation for statements to Prime Minister Abiy Ahmed.The fact-checker said that the PM has never uttered such statement.

BBC monitored news was posted as if the PM said the war in Tigray region will go on regardless of civilian casualties which has never said by the PM.

Late after hours, Gudayach could realized as the BBC monitored news was deleted.But the matter is so serious and many African countries are watching the action seriously.For your easy information, please find both posts here below. 

* The new development is that BBC monitoring excuses for the mistake (please find the excuse tweeter also here below)

Add caption





Saturday, November 21, 2020

The operation to maintain law and order will have a positive effect on future horn stability

The Ethiopian Herald Newspaper,Addis Ababa, Ethiopia

November 18/2020

BY GETACHEW BEKELE DAMTEW

The Ethiopian government’s operation to maintain law and order has continued for the second week. Government sources, quoted by Reuters, disclosed that when the TPLF (Tigray People’s Liberation Front) junta fled from Alamata town, they have taken 10,000 prisoners with them to an unknown place. Shockingly, last week, the junta committed ethnic mass killing on 500 innocent Amharas in Mai-Kadra town as has confirmed by Amnesty International and the UN called the incident an international war crime.

On the other hand, some local and international media outlets in the west are trying to mislead their followers regarding the situation. However, to clearly understand the situation, it is quite important to understand the background of the real political, social and economic situations of Ethiopia for the past three decades and the recent reform taking place in the country since Prime Minister Abiy Ahmed came to power some two and half years ago.

The Background of TPLF

It was in 1991 that TPLF changed itself from a rebel group to the leader of one of the ancient countries in Africa, Ethiopia. For long, the TPLF dominated the now-dissolved ruling coalition, the Ethiopian Peoples’ Revolutionary Democratic Front (EPRDF) and as soon as they grabbed state power, they tried to divide Ethiopia by supporting the establishment of ethnocentric political parties and ideology. The EPRDF is a coalition of pseudo ethnic parties that represent Amhara, Oromo and southern nations and nationalities, their establishment was meant to aid TPLF’s objectives and goals.

During those turbulent times, almost all genuine opposition parties and independent media outlets were banned as they were labeled ‘terrorists’ by parliament and judicial body. The reports of international human rights groups and journalists’ associations including Amnesty International and International Association of Journalists as well as the US government’s annual reports repeatedly published the grave human and democratic rights violations in Ethiopia under the TPLF.

TPLF’s 27 years rule can be characterized by ethnic hatred, divisions, clashes and intimidations. As a result, thousands were displaced, killed and sent to prison only for their views.

The miserable situation did not manifest in political and social life only. The country’s economy was almost fully under the control of a few ethnocentric pro-TPLF groups. Endowment Fund for the Rehabilitation of Tigray (EFORT) was one of the giant ethnocentric business organizations in Africa according to its former Managing Director Sibhat Nega’s interview with Voice of America’s Amharic Service. Here we should note that the rehabilitation fund has not been rehabilitating the people of Tigray. Rather, its sole purpose has been strengthening the financial muscle of the clique in the TPLF.

The injustice and the oppression gave birth to rebellion movements and uprising within the youth in Amhara, Oromia and Southern Nations, Somali and other nations in Ethiopia. The youth started to protest against injustice and systematic marginalization. Strong but peaceful protests in Oromia state, peaceful demonstration and armed movements in Amhara state combined with the strong resistant movement in the Diaspora brought about change in Ethiopia. That is why former Prime Minister Hailemariam Desalegn resigned on March 27, 2018, opening the door for the coming to power of Abiy Ahmed and the introduction of an overall reform in the country.

The journey in the last two years

Since March 2018, Ethiopia has experienced dramatic political, economic and social changes. Almost all political prisoners were released; all exiled political parties came back home. Previously banned newspapers, television stations and even blogs were allowed to legally operate in Ethiopia. Restrictive laws and regulations that dealt with Non-Governmental Organizations (NGOs), charities and civil societies were amended to give more space for freedom. The country is also opening up its door for privatization. On top of all these, the country has made peace with Eritrea, ending its two decades of hostile relations. As a result of his peace initiatives, PM Abiy won the 2019’s Nobel Peace Prize.

TPLF’s defiance to accept the change, conspiracy to destabilize Ethiopia and the Horn

Being a legally registered political party, TPLF has not chosen a legal path. Rather, it continued to engage in a conspiracy to destabilize the country as a response to losing power. In the past two years, it has become a major security threat to Ethiopia and the Horn of Africa region as a whole. It has been conspiring to instigate ethnic

 clashes in different parts of the country particularly in the western and southern parts. It has also allocated a huge amount of fund for its anti-peace activities.

With a view to instigate protests, the junta even sponsored the assassination of prominent individuals, including that of Ethiopian Afan Oromo singer Hachalu Hundessa last June. But the government tried to exercise patience in dealing with the junta. However, TPLF continues to violate the constitutional order as well as the basic legal, political and military rules of the nation.

We can mention so many incidents where the TPLF junta violated the law of the land. And it is possible to mention here a few instances where the junta totally violated the constitution and the law of the land. First of all, back in August, it conducted a sham regional election without the consent of the National Electoral Board, an institution constitutionally mandated with dealing with such issues. In fact, the government postponed the elections due to be held back in May/June at both the federal and state/regional level to prevent the spread of COVID-19.

Secondly, in addition to its massive negative propaganda against the central government, TPLF started to threaten sovereign neighbouring countries like Eritrea and Sudan. As a result, the Eritrean President Isayas Afeworki’s government discussed the issue repeatedly with its Ethiopian counterpart and the Intergovernmental Organization of the Horn of Africa (IGAD) has been following the situation seriously.

The TPLF junta has been trying to destabilize the region by interfering and undermining the activities of Ethiopia’s federal government which has a long reputation of playing a constructive role in the region. For instance, trespassing the federal government’s and the Ministry of Foreign Affairs’ authority, the junta tried to write letters to neighbouring countries and other the international partners of Ethiopia.

The Premier tried to tolerate all these with the intention of not disturbing national and regional peace. But, the junta interpreted the patience the other way round and once again engaged in a barbaric act. In an act of betrayal, the junta recently orchestrated an attack against the North Command base of the Ethiopian Army in Mekelle. As the Prime Minister put it, with this action, the TPLF crossed the last point of redline.

Hence, the operation to maintain law and order in Tigray region should be seen as an effort from the government’s side to ensure regional stability in the Horn of Africa.

The past week has shown us what the TPLF could do to destabilize the region if the government remained patient and reluctant to enforce rule of law. Its rocket attack towards Gondar city and Bahir Dar, the latter of which is the regional capital of Amhara state, as well as Asmara, the capital of Eritrea clearly demonstrate how the TPLF is a threat of regional stability.

The Ethiopian Herald November 18/2020

https://www.press.et/english/?p=30621# 


Saturday, November 14, 2020

ህወሓት በጎንደር እና ባሕርዳር ላይ የፈፀመው የሮኬት ጥቃት ለኢትዮጵያ መንግስት አምስት ጥቅሞችን ይዞ ይመጣል።

ጉዳያችን / Gudayachn
ኅዳር 5/2013 ዓም (ኖቬምበር 14/2020 ዓም)



ትናንት ምሽት በባሕርዳር  እና ጎንደር አየር ማረፍያ አካባቢ ላይ  ከህወሓት የተወረወረው ሮኬት መሆኑን መንግስት ተናግሯል::ውርወራው ግን በባህርዳር በተለምዶ መኮድ አካባቢ፣በጎንደር ደግሞ አዘዞ አካባቢ የተፈፀመው ውርወራ ይህ ነው የተባለ ጉዳት አለማድረሱ እና በቀጣይ ዝርዝር መረጃ መንግስት እንደሚሰጥ ገልጧል።

አሁን በጉግል ምልከታዬ መሰረት ከመቀሌ እስከ ጎንደር ያለው እርቀት  በመኪና መንገድ 559 ኪሜ ሲሆን በአየር ላይ ወደ 240 ኪሜ ነው::ከመቀሌ ባሕርዳር ደግሞ በመኪና 615 ኪሜ ሲሆን በአየር ላይ 310 ኪሜ ነው:: የሕወሃት ሮኬት ቀድሞም መንግስት እንደተናገረው እስከ 300 ኪሜ ገደማ ነው::

የሮኬት ጥቃቱ ህወሓት ከመደበኛ ተዋጊነት ወርዳ ወደ ሐማስ መሰል ሽብርተኝነት መውረዷ በግልጥ የታየበት ነው።በትግራይ ውስጥ መሬት ላይ ያለውን ውጊያ መቆጣጠር ስላልቻሉ የመጨረሻ ያላቸውን ኃይል አሟጠው የመጠቀማቸው ማሳያ ነው።የሮኬቶቹን አጠቃቀም በተመለከተ ከግብፅ ወይንም ከሌላ የጠላት ሀገር በስልክ እና ቪድዮ የተደገፈ ድጋፍ ተደርጎላቸው ይሆናል።ይህ ግን አሁንም መሬት ላይ ያለውን የጦርነቱን እውነታ አይቀይረውም።ምክንያቱም መሬት ላይ ያለው ሁኔታ የኢትዮጵያ ሰራዊት የህወሓትን ጁንታ ቡድን ወደ ጠበበ ኮርነር እያስገባው ከመሆኑ በላይ የነዳጅ እስከ ስንቅ አቅርቦቱ እየተመናመነ ነው።ይህም በመሆኑ በትናንትናው ዕለት የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ኮሚሽን መጋዘንን ሰብሮ ለስደተኞች የመጣውን እህል መዝረፉን እና ወደ 90 የሚጠጉ የድርጅቱን ሰራተኞች ማገቱን ኢሳት ከተባበሩት መንግሥታት ባገኘው አስተማማኝ ምንጭ ገልጧል።የእዚህ የሮኬት ጥቃት ዓላማዎች ሊሆኑ የሚችሉት ሁለት ናቸው።እነርሱም -የመጀመርያው ህወሓት የሞት አፋፍ ላይ አይደለሁም፣አለሁ ለማለት ሲሆን።ሁለተኛው ዋናው ዓላማው ግን በዓማራ ክልል እና በሌሎች የኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች ላይ ሕዝብ ጥቃት እንዲፈፅም ግጭት ለመፍጠር ነው።በእዚህም የትግራይ ሕዝብ ውስጥ ለመወሸቅ ዋስትናውን ለማረጋገጥ ነው።ስለሆነም ህዝቡ አሁንም በጥንቃቄ መሄድ አለበት።

የሮኬት ጥቃቱ ለኢትዮጵያ መንግስት ጥቅምም አለው - ጥቅሞቹ -

1) መንግስት ለሚወስደው የሕግ ማስከበር ስራ መቀጠል አስፈላጊነትን ለዓለምአቀፍፉ ማኅበረሰብ የሚያሳምንበት ተጨማሪ በቂ ምክንያት አሰጥቶታል::ሕወሃት ከተሞች ላይ የሚተኩስ በመሆኑ ትጥቁን ማስፈታት እንዳለበት ያሳምንበታል::አንዳንድ የዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና አህጉራዊ አካላት ጦርነቱን ማቆም እና ሁለቱ ወገኖች ቢደራደሩ የሚል ሃሳብ ሰንዝረዋል።ሱዳን በኢጋድ ኃላፊነቷ ጠይቃለች።የአውሮፓ ሕብረት በበኩሉ ስደተኞች እንዳይመጡብኝ በሚል ሰግቻለሁ የሚሉ ድምፆች በድፕሎማቱ አስተያየት ተገልጧል።ጦርነቱን ብታቆሙ የሚለው ሃሳብ አንዱ መነሻ ይህንን ያህል የሚያሰጋ ኃይል አይደለም፣በቀላሉ ድርድር በቂ ነው በሚል ምክንያት ነው።አሁን ግን የኢትዮጵያ መንግስት የሚያደርገው የሕግ ማስከበር ሥራ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ እና ማንም ሊናገረው እንደማይችል፣የፀጥታ ስጋት እና የህዝብ ደህንነት ጉዳይ እንደሆነ በሚገባ ያሳምንበታል።በሌላ በኩል መንግስት ያልተመጣጠነ ኃይል ተጠቅሟል ለሚሉ አሁን አፋቸውን የሚዘጉበት ጊዜም ነው።የኢትዮጵያ አየር ኃይል ጥቃት በትግራይ የተመረጡ ቦታዎች ላይ መፈፀሙ ምን ያህል አስፈላጊ እና ተመጣጣኝ ያልሆነ ለመሆኑ ማሳያም ነው።ስለሆነም ሮኬቱ ጥቅምም ይዞ መጥቷል።

2) የዓለም መንግስታትም የእዚህ ዓይነት ሮኬት ኃላፊነት በማይሰማቸው ኃይሎች እጅ መግባቱ በራሱ ሃሳብ ውስጥ ይጥላቸዋል::ምስራቅ አፍሪካም እንዳይታወክ በሊብያ፣ሶርያ እና የመን የተሰራው ዓይነት ስሕተት ተሰርቶ አካባቢው እንዳይታወክ ከመንግስት ጎን በመቆም መንግስት ሁኔታዎችን እንዲቆጣጠር ለመደገፍ በውስጥ እንዲሰሩ ያስገድዳቸወዋል::ርግጥ ነው ይህ ዓይነቱ ዕሳቤ እነግብፅን አይመለከትም::ሆኖም የምስራቅ አፍሪካ መታወክ የዓለም አቀፍም ሆነ የአፍሪካ ቀንድ አሸባሪዎችን እንደሚያነቃቃ የሚያውቁ ሃያላኑ መንግሥታት አሁን ጉዳዩን ትኩረት ይሰጡታል።የአውሮፓ ሕብረትም ቀድሞ ትግራይ ላይ በሚደረገው ውግያ ስደተኛ ፈራሁ እንዳላለ አሁን ወደ ከተሞች የሚወረወሩ ሮኬቶች መኖራቸው የበለጠ ስደተኛ ያመጣል የሚል ስሌት ውስጥ ይገባል።ስለሆነም መንግስት የትግራይ ጦርነትን መጨረሱ ጥቅም እንዳለው በሚገባ ያምናል። 

3) ኢትዮጵያውያን በተለይ በዓማራ ክልል ያሉ የገፈቱ ቀድሚ ቀማሾች ከቀድሞ የበለጠ እንዲነቁ ያደርጋል።ይሄውም አካባቢያቸውን በኃላፊነት ከመጠበቅ ጀምሮ እስከ ጦር ሜዳ መፋለም ድረስ የበለጠ ያነሳሳቸዋል። 

4) የትግራይ ሕዝብ ይህንን የሮኬት ውርወራ ህወሓት የትግራይን ሕዝብ ለማስፈጀት ሌላ የእብደት ሥራ እንደሰራ እንዲያስብ ያደርገዋል።መዘዙም የበለጠ ከማስፈራቱ በላይ የአየር ክልሉን እንደፈለገ የሚቀዝፍን መንግስት በሮኬት ውርወራ ለማስፈራራት መሞከር አንበሳን ከስር በእንጨት ወግቶ የመፎከር ያህል አደገኛ መዘዝ እንዳለው ያውቃል።ስለሆነም ህዝቡ ጦርነቱ ቶሎ አብቅቶ ወደ ሰላማዊ ሕይወት እገባለሁ እያለ ሲጠብቅ የሮኬት ጥቃቱን ሲሰማ ጦርነቱ እንደሚራዘም ስለሚያስብ የህዝቡ ከዳር መመልከት እንደማያዋጣ እና የህወሓት ወንጀለኞች በቶሎ አሳልፎ መስጠት አስፈላጊነት ላይ እንዲወስን ያደርገዋል።

5) ኤርትራ ከመቼውም ጊዜ በላይ በህወሓት ላይ ዘመቻዋን በሁሉም መስክ እንድታደርግ ያደርጋታል።ኤርትራ የህወሓት ዋነኛ ኢላማ እንደሆነች ታውቃለች።ህወሓት ይህ ሮኬት አላት ማለት ለኤርትራ ቀዳሚ የፀጥታ አደጋ አለው።ስለሆነም ከእዚህ በፊት ከነበራት ውሳኔ በበለጠ አሁን የበለጠ በህወሓት ላይ የተቀነባበረ ዘመቻ አስፈላጊነቱ ላይ ትወስናለች።ሌላው ኤርትራ እና ኢትዮጵያ በጣምራ ጥቃት ከአሁን በኃላ በህወሓት ላይ ቢጀምሩም  ለማንም የውጭ ኃይል የሚያሳምኑበት በቂ መረጃ አላቸው።ይሄውም ህወሓት የሁለታችንም የፀጥታ እና የደህንነት ስጋት ነው።ሮኬት ሁሉ እየወረወረ ነው።ይህ ደግሞ ለእኛ ብቻ ሳይሆን ለሱዳንም፣ለጅቡቲም (በተለይ ኢትዮጵያ የወደብ አገልግሎት የምትጠቀምበት ስለሆነ) ስጋት ነው ማለት ይችላሉ።በእዚህም የሚቃወም አንዳች ሀገር ሊኖር አይችልም።

በመሆኑም እንደ ጉዳያችን ዕይታ የሮኬት ውርወራው እነኝህ ጥቅሞችን ለኢትዮጵያ ይዞ ይመጣል።አሁን ህወሓት ሁሉ ነገር ከእጇ ወጥቷል።በማይካድራ የፈፀመችው የዘር ማጥፋት ወንጀልን በተመለከተ የተባበሩት መንግስት ዓለም አቀፍ የጦር ወንጀል መሆኑን ትናንት ማስታወቁ ይታወቃል።

ጉዳያችን ዩቱብ ሰብስክራይብ ያድርጉ 

Sunday, November 8, 2020

Sunday, November 1, 2020