ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Monday, March 27, 2017

የዓለም ባንክን የሚገዳደር የእስያ መሰረተ ልማት እና መዋለ ንዋይ ባንክን ቻይና እያጠናከረች ነው።

ጉዳያችን/ Gudayachn
መጋቢት 19፣2009 ዓም ( march 28,2017)

የእስያ መሰረተ ልማት እና መዋለ ንዋይ ባንክ ቦርድ አባላት 
(Foto: AIIB)

በአለማችን ላይ መሰረታዊ የምጣኔ ሀብት መዋቅር ከመቀየር አንፃር የገንዘብ ተቋማት ያላቸው ሚና ቀላል የሚባል አይደለም።ላለፈው ግማሽ ክ/ዘመን እና በተለይ ከ 1980 ዎቹ እንደ ´አውሮፓውያን አቆጣጠር ማለትም ከሶቭየት ህብረት መበተን በኃላ የዓለም ባንክ እና የዓለም የገንዘብ ድርጅት ተፅኖ በአፍሪካ፣ላቲን አሜሪካ እና ሩቅ ምስራቅ ሀገሮች ውስጥ ቀላል አልነበረም።በተለይ በ1990ዎቹ ውስጥ የነበረው የዓለም ባንክ መዋቅራዊ ለውጥ ፕሮግራም ኢትዮጵያን ጨምሮ የብዙ አፍሪካ ሀገር ህዝቦችን ሕይወት አመሰቃቅሎ እና ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል።የመዋቅራዊ ለውጥ መርሃ ግብሩ ጉድለት በእራሱ በዓለም ባንክ የተወቀሰው በርካታ ማኅበራዊ፣ምጣኔ ሃብታዊ እና ፖለቲካዊ ቀውስ ካስከተለ በኃላ መሆኑ ሌላው ህመም ነበር።

ባለፈው ዓመት መጀመርያ ላይ ከወደ ቻይና የተሰማው የግዙፍ ዓለም አቀፍ ባንክ ምስረታ ግን አዲስ ታሪክ ይዞ መጥቷል።ከአንድ ዓመት ከሶስት ወራት ዝግጅት በኃላ እንደ ኤውሮፓውያኑ የጊዜ ቀመር በጥር ወር 2016 ዓም በሩን የከፈተው የእስያ መሰረተ ልማት እና መዋለ ንዋይ ባንክ (Asian Infrastructure Investment Bank - AIIB)መሰረታዊ ፍልስፍናው ግልፅነት፣ተጠያቂነት፣ከጥገኝነት የፀዳ እና አረንጓዴ ልማትን መሰረት ያደረገ እንደሆነ ይናገራል።

በሌላ በኩል ባንኩ የዓለም ባንክ ላለፉት አመታት ሲወቀስባቸው የነበሩትን የሀገሮች የተጭበረበረ የምጣኔ ሀብት እድገት ሪፖርት ማውጣት እና ሙስና የመሳሰሉትን ጉዳዮች በእዚህ ባንክ እንዳይታዩ ከወዲሁ መሰረት የጣለ ይመስላል።በመሆኑም የባንኩ ቀዳሚ መመርያ መልካም አስተዳደር (Good governance) መሆኑን እና የተሳሳተ ሪፖርት ይዞ መውጣት ፈፅሞ እንደማይታሰብ ባንኩ በመተዳደርያው ላይ ያትታል።ይህ ምን ያህል ተአማኒነት አለው? የሚለው እራሱን የቻለ ጥያቄ ነው።እርግጥ በሙስና ደረጃ ቻይና የተሻለ ወሳኝ እርምጃ የምትወስድ ሀገር ነች።ይህንን ግን አፍሪካ እና ላቲን አሜሪካ ሀገሮች ላይ ታደርገዋለች ወይ? የሚለው ጥያቄ እራሱን የቻለ መልስ ይፈልጋል። 
"ቀን እባብ ያየ ምሽት ላይ በልጥ ይደነብራል" ነው ነገሩ እና የቻይና "ስግብግብነት" የሚታይበት የአፍሪካን ምጣኔ ሀብት የመቆጣጠር አባዜን ላለፉት አስር አመታት የተመለከተ ሰው ሚዛናዊነትን መጠበቅ ባይችል አይፈረድበትም።

ባጠቃላይ ግን የዓለም ባንክን የሚገዳደር ግዙፍ ከጀርባ በቻይና የተደገፈ ነው የተባለ የገንዘብ ድርጅት አድማሱን እያሰፋ ነው።አባል ሀገሮቹ ከአውሮፓ እንደ ጀርመን እና ደንማርክ፣ሩስያ ከመካከለኛው ምስራቅ እንደ ኢራን እና እስራኤል ከሩቅ ምስራቅ ቻይና እና ህንድ እንዲሁም አውስትራሊያ አህጉርን ጨምሮ እና ካናዳ እና ሌሎች ሀገሮችን አካቶ አቅሙን እየገነባ ነው።አሜሪካ እና ጃፓን አባልነት ላለመግባት ያንገራገሩበት ይሄው ባንክ እንግሊዝ፣ስዊዘርላንድ፣ግብፅ እና በቅርቡ ደግሞ ኢትዮጵያን በአባልነት ተቀብሏል።ዋና መስርያ ቤቱን በቻይና ዋና ከተማ ቤጂንግ ፋይናንሻል መንገድ ቁጥር ቢ9 ያደረገው ይሄው ባንክ በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ ብዙ ሀገሮችን ወደ አባልነት እያሰባሰበ ነው።

ከእዚህ በታች በባንኩ እድገት እና የምዕራቡ ዓለም በተለይ የአሜሪካ ስሜት ዙርያ የተደረገ አጭር የቪድዮ ውይይት ነው።

የውይይት ርዕስ : -  "አሜሪካ ለምን በእስያ መሰረተ ልማት እና የመዋለ ንዋይ ባንክ መጠናከር ስጋት አደረባት? " የሚል ነው።
Why is the US so threatened by the rise of the AIIB? 
Video source: World Finance Video 









ጉዳያችን GUDAYACHN

 www.gudayachn.com

Friday, March 24, 2017

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመጪው ሳምንት አዲስ በረራ ወደ ኦስሎ፣ኖርዌይ ይጀምራል። Next week Ethiopian Airlines will start new flight to Norwegian capital, Oslo. Neste uke vil Etiopia Flyselskaper starte et nytt fly til Oslo.



ጉዳያችን/Gudayachn
መጋቢት 14፣2009 ዓም (March 23,2017)
=================
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ስካንዲንቭያን ሀገሮች የሚያደርገውን በረራ የኖርዌይ፣ኦስሎን በመጨመር ከፍ እንዳደረገ በድረ-ገፁ ላይ ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።Three new flights to three new destinations (በሶስት ቀናት ውስጥ ሶስት አዳዲስ መዳረሻዎች) በሚል ርዕስ ስር ያወጣውን መግለጫ የዓለም አቀፍ የዜና አውታሮች እየተቀባበሉት ይገኛሉ።በእዚሁ መግለጫው ላይም መጋቢት 26-28/2017 እኤአ አየር መንገዱ ወደ ኦስሎ፣አንታናናሪቭ እና ቪክቶርያ ፎል በረራ እንደሚጀምር ይገልፃል። 

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአግልግሎት ጥራቱን ጠብቆ ዘመን ተሻጋሪ እንዲሆን የብዙ ኢትዮጵያውያን ምኞት ነው።አየር መንገዱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚታዩበትን አስተዳደራዊ ጣልቃ ገብነቶች እና የሰራተኞቹን ብሶቶች በአግባቡ እንዲያዳምጥ እና ተወዳዳሪነቱን እንዲጨምር አሁንም የብዙ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ያላሰለሰ ምክር እና ምኞት ነው።




ከእዚህ በታች አየር መንገዱ በእዚህ ሳምንት አጋማሽ ላይ ያወጣው መግለጫ ነው።




Three new flights to three new destinations in just three days
March 22, 2017
Africa’s largest airline group, Ethiopian Airlines, is delighted to announce that it has finalized preparations to launch flights to three new destinations – Victoria Falls, Oslo and Antananarivo – within three days, 26-28 March 2017.
....to read more click here 



ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

Thursday, March 23, 2017

ሰበር ዜና - Breaking News Ethiopia - የተባበሩት አረብ ኢምሬት አምባሳደር ትናንት መከላከያ ሚኒስቴር መስርያ ቤት ታይተዋል ድርጊቱ ያልተለመደ ነው።UAE Ambassador makes extraordinary meeting with chief of staff of Ethiopian Army



ጉዳያችን/ Gudayachn 
መጋቢት 14፣2009 ዓም (March 23,2017)
(የአማርኛ ፅሁፍ ከእንግሊዝኛው ስር ያንብቡ )

On March 22, 2017, United Arab Emirates - UAE Ambassador to Ethiopia, Gazi Abdullah Al Mahri,  makes extraordinary meeting  with chief of staff of Ethiopian Army General Samora Yenus with in Ethiopian ministry of defence premises. Even if the meeting was given a cover of " discussion on terrorism", Gudayachn can learn as many questions are arising around the meeting. First of all, the UAE Ambassador did not keep his diplomatic protocol to meet the chief of staff. Because the concerned office to arrange such meeting in Ethiopia was ministry of Foreign Affairs. Secondly, the meeting was not disclosed to other high officials in the country. Non confirmed news from Addis are reporting as there is power straggle among high military officials. In the past few days, top urgently needed corrupt officials were leaving the country legally with the assistance of corrupt immigration officials exit visa from Ethiopia. 

It is over six months, since the state of emergency was declared in Ethiopia. The declaration could not improve the security condition and uprising of the mass against the brutal TPLF government. On the other hand, It is known as TPLF army is under pressure of fighting with Patriotic Ginbot 7 and KEFAGN rebel forces in Amhara region. This week the rebel groups announced as they got significant victory over TPLF army in the North west part of the country. 
==================================
የተባበሩት አረብ ኢምሬት አምባሳደር ትናንት መከላከያ ሚኒስቴር መስርያ ቤት ታይተዋል ድርጊቱ ያልተለመደ ነው። 
===================================
ጀነራል  ሳሞራ የኑስ አዲስ አበባ የሚገኙትን የተባበሩት አረብ ኢምሬት አምባሳደርን ትናንት ፅህፈት ቤታቸው ጠርተው ማነጋገራቸውን አንድ የመካከለኛ ምስራቅ ድረ-ገፅ ገልጧል። አምባሳደር ጋዚ አብዱላህ አል ማሃሪ (Gazi Abdullah Al Mahri) ከሳሞራ የኑስ ጋር የተናጋገሩት ስለ ሽብርተኝነት የምትል ከሶስት መስመር ያልበለጠ ዜና የዘገበው ዜና ለምን አምባሳደሩ ፕሮቶኮሉን ጠብቀው በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በኩል እንዳልተነጋገሩ ያለው ነገር የለም።አምባሳደሩ ከጀነራል ሳሞራ የኑስ ጋር የተነጋገሩት መከላከያ ሚኒስቴር መስርያ ቤት ድረስ በመሄድ ነው።

አምባሳደሩ መከላከያ ሚኒስቴር መስርያ ቤት ድረስ ሄደው ከሳሞራ የኑስ ጋር መነጋገራቸው በሚስጥር እንደነበር እና መከላከያ ውስጥ ያሉ ሰዎችም አለመስማታቸው እየተሰማ ነው።ድርጊቱ ያልተለመደ ነው።ጉዳዩ በኢትዮጵያ የጦር ሰራዊቱ አመራር እና ባለስልጣናት መካከል የስልጣን ፍትግያ መጀመሩን የሚያመላክት መሆኑ እየተሰማ ነው።በሌላ በኩል ጀነራል ሳሞራ የኑስ የጠቅላይ ሚኒስትሩንም ሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን ስልጣን በዘለለ መንገድ የእራሳቸውን ግንኙነት ከአምባሳደሮች ጋር እያደረጉ ነው የሚሉ ወገኖችም አሉ።

ሰሞኑን እንደሚታወቀው የሕወሓት መንግስት ከአርበኞች ግንቦት 7 እና ከፋኝ ጦር ጋር በተለያዩ ቦታዎች ውግያ እንዳደረገ እየተነገረ ነው።የአርበኞች ግንቦት 7 እና ከፋኝም የበላይነት እንደተቀዳጁ በእዚህ ሳምንት መጀመርያ ላይ አሳውቀዋል።አርበኞች ግንቦት 7 ባልተለመደ መልኩ " ኢትዮጵያውያን ሚናቸውን የሚለዩበት ጊዜ ላይ ደርሰናል" የሚል ሃሳብ ያለው ጠንከር ያለ መግለጫ አውጥቷል።




ጉዳያችን GUDAYACHN 

 www.gudayachn.com

Wednesday, March 22, 2017

የኦስሎ ዩንቨርሲቲ ምሩቁ የሱማሊያው አዲሱ ጠቅላይ ሚንስትር ማናቸው? ጠ/ሚሩ የካቢኔ አባሎቻቸውን ትናንት አስተዋውቀዋል። Somalian PM announced his cabinet ministers.

የሱማልያው አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚስተር አሊ ካይረ


ጉዳያችን/ Gudayachn 
መጋቢት 13/2009 ዓም (March 22,2017)

የሱማልያው አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚስተር አሊ ካይረ በጠቅላይ ሚኒስትርነት ከተመረጡ እና በፓርላማ ስልጣናቸው ከፀደቀ ገና ሶስተኛ ሳምንቱን ቢይዝም አዲሱ ካቢናቸውን መስርተዋል።
የመጀመርያ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በሞቃዲሾ እንደጨረሱ የሚነገርላቸው ጠቅላይ ሚኒስትር 1994 ዓም እኤአ በኖርዌይ ዋና ከተማ በሚገኘው የኦስሎ ዩንቨርስቲ ተማሪ የነበሩ እና በሱማሌ ተማሪዎች ህብረት እንቅስቃሴ ጉልህ አስተዋፅኦ እንደ ነበራቸው ለማወቅ ተችሏል። 

በኦስሎ ዩንቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ እና ´ማይነራቸውን´ ሶሾሎጂ የጨረሱ ሲሆን በመቀጠል በኤደንበርግ ቢዝነስ ኮሌጅ( Edinburgh Business School) የማስተርስ ዲግሪ አግኝተዋል። ከምርቃት በኃላ ሚስተር አሊ ካደር ወደ ኦስሎ ተመልሰው በአንደኛ ደረጃ መምህርነት በመቀጠል ደግሞ በኖርወጅያን ስደተኞች ካውንስል (Norwegian Refugee Council) ዋና መስርያ ቤት ውስጥ በአስተባባሪነት ሰርተዋል።በመሃል ለግል ሥራ ካቆሙ በኃላ ተመልሰው ወደ  የኖርወጅያን ስደተኞች ካውንስል መስርያቤት ውስጥ በመግባት ለ9 ዓመታት በማገልገል እስከ ሪጅናል ዳይሬክተርነት ደረጃ  ደርሰው ነበር።በመስርያ ቤቱ ውስጥም በምስራቅ አፍሪካ በተለይ ሰሜናዊ  ኬንያ ውስጥ ሰርተዋል።

በሰሜን ኬንያ በኖርወጅያን የስደተኞች ካውንስል ኃላፊ በነበሩበት ወቅት በነበረው የፀጥታ ችግር የተለያዩ ሃገራት የስራ ባልደረቦቻቸውን በሞት  ያጡ ሲሆን በኃላፊነታቸው ሳብያ የፀጥታ ሁኔታው በሚገባ እንዲጠበቅ አላደረጉም ተብሎ መስርያቤታቸው ሲከሰስ እርሳቸውም በዋናነት  በኖርዌይ ፍርድ ቤት ፊት ቀርበው ነበር።በመቀጠል የሚስተር አሊ ካይረ የስራ መስክ ያመራው  በእንግሊዝ ካምፓኒ ´ሶማ ኦይል´ (Soma Oil) ውስጥ ነበር። ሚስተር አሊ ከእዚህ ወር መጀመርያ ጀምሮ የሱማሌ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነዋል።በትናንትናው እለት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አዲሱን ካቢኔ አስተዋውቀዋል።

በአዲሱ ካቢኔ ውስጥ ስድስት ሴት ሚኒስትሮች ተሹመዋል።ይህ ሁሉ ሆኖ የሱማሌ ሁኔታ ግን ገና መረጋጋት ይጎድለዋል።በትናንትናው እለትም ወደ ቤተ መንግስት የሚያመራ መንገድ ላይ በቆመ አንድ አውቶብስ ላይ የተጠመደ ፈንጅ ፈንድቷል።አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ከአሁኑ የሕወሓት አስተዳደር ጋር ያላቸው ግንኙነት የተቀዛቀዘ መሆኑን የሚናገሩ አሉ።ለእዚህም ማስረጃ የሚያደርጉት በሱማሌ የተሾሙ ሹማምንት የመጀመርያ ጉዞ የሚያደርጉት ወደ ኢትዮጵያ ሲሆን ሚስተር አሊ ግን የመጀመርያ ጉዟቸውን ያደረጉት ወደ ሳውዲ አረብያ መሆኑን ነው።


የፕሬዝዳንት አሊ አዲሱ ካቢኔ አባላት ስም ዝርዝር ከእዚህ በታች ይመልከቱ። 


Somalia’s Premier Hassan Ali Khayre on Tuesday announced his cabinet ministers.
Mr. Khayre made the announcement at a press conference in the Somali capital, Mogadishu.

The names of the new ministers are:

  1. Abdi Farah Juha – Interior Minister
  2. Yousuf  Garad Omar – Minister of Foreign Affairs
  3. Mohamed Abukar Islow – Minister of National Security
  4. Jamal Mohamed Hassan – Minister of Planning
  5. Abdirahman Duale Beyle – Minister of Finance
  6. Khadija Mohamed Dirie – Minister of Youth and Sports
  7. Abdirahman Omar Osman – Minister Of Information
  8. Maryan Qasim Ahmed – Minister of Humanitarian Affairs and Disaster Management
  9. Abdirashid Mohamed Abdullahi – Minister of Defence
  10. Abdirahman Dahir Osman – Minister of Education and Higher Education
  11. Abdirahman Hosh Jibril – Minister of Constitutional Affairs
  12. Maryan Aweys Jama – Minister of Ports and Aviation
  13. Abdi Anshur Hassan – Minister of Posts and Technology
  14. Sheikh Nur Mohamed Hassan – Minister of Livestock
  15. Khadro Ahmed Duale – Minister of Trade and Industry
  16. Abbas Sheikh Abdullah Siraaji – Minister of Public Works and Rebuilding
  17. Abdirashid Mohamed Ahmed – Minister of Petroleum and Mineral Resources
  18. Said Hussein Eid – Minister of Agriculture
  19. Fawzia Yusuf Haji Nur – Minister of Health and Social Welfare
  20. Hassan Hussein Haji – Minister of Justice
  21. Saleh Ahmed Jama – Minister of Labour and Employment
  22. Salim Aliyow Ibrow – Minister of Electricity and Water
  23. Iman Abdullahi Ali – Minister of Religious affairs
  24. Deqa Yasin Haji Yousuf – Minister of Women and Human Rights
  25. Abdirahman Abdi Hashi – Minister of Fisheries and Marine Resources 
  26. Mahad Ahmed Guled – Deputy Prime Ministe  

Six of the new ministers are women.

The new cabinet ministers will face a confidence vote in the parliament next days, according to the Somalia’s constitution.



ጉዳያችን GUDAYACHN 

 www.gudayachn.com

Monday, March 20, 2017

በሰለሏት ሀገር ላይ አምባሳደርነት ከተሾሙት ኢትዮጵያዊው ዶክተር አስማማው ቀለሙ ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ (ኦድዮ)

ምንጭ : - ሸገር ኤፍ ኤም ራድዮ " ሸገር ካፌ" ፕሮግራም


ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Saturday, March 18, 2017

A complicated hero in the war on dictatorship by Samantha Power (video)

Samantha Power is an author and diplomat who served as the United States Ambassador to the United Nations from 2013 to 2017. Power began her career by covering the Yugoslav Wars as a journalist. From 1998 to 2002, she served as the Founding Executive Director of the Carr Center for Human Rights Policy at the Harvard Kennedy School, where she later became the first Anna Lindh Professor of Practice of Global Leadership and Public Policy. She was a senior adviser to Senator Barack Obama until March 2008, when she resigned from his presidential campaign after apologizing for referring to then-Senator Hillary Clinton as "a monster."

Power joined the Obama State Department transition team in late November 2008. She served as Special Assistant to the President and Senior Director for Multilateral Affairs and Human Rights on the National Security Council from January 2009 to February 2013.

Samantha Power studies US foreign policy, especially as it relates to war and human rights. Her books take on the world's worst problems: genocide, civil war and brutal dictatorships. She's the author of a famous memo (in policy circles) suggesting that US foreign policy is utterly broken -- that the United States must return to a human rights-centered foreign policy or risk its prestige and respect in the world community.

Source: TED.com
    
Please note: - This speech was made in 2008 



ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Sunday, March 12, 2017

አሳዛኝ ዜና - በአዲስ አበባ ከልዩ ልዩ ስፍራዎች ቤታቸው በመንግስት የፈረሰባቸው ሰዎች ተጠግተው የሚኖሩበት አካባቢ በደረሰ የቆሻሻ ክምር ናዳ የበርካታ ሰዎች ሕይወት ጠፋ (ፎቶዎች ይዘናል)

Ethiopia - A landslide in the capital, Addis Ababa, kills over 46 people and over 50 are highly injured. Many children's current condition is not yet known. The number of casualties is increasing every time. The report is not yet finalised. 
The place is known by the residence of   people who have been force fully pushed and displaced by the government from different part of Addis Ababa´s residential areas.
በአዲስ አበባ ከልዩ ልዩ ስፍራዎች ቤታቸው በመንግስት የፈረሰባቸው ሰዎች እና ገቢያቸው ዝቅተኛ የሆኑ ነዋሪዎች ተጠግተው የሚኖሩበት አካባቢ በተለምዶ ቆሼ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የቆሻሻ አፈር ናዳ ተንዶ ከ40 በላይ በሚጠጉ ቤቶች ላይ በማረፋ ከ46 በላይ ሰዎች ሲሞቱ ከ50 በላይ ሰዎች ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው ሆስፒታል ገብተዋል፡፡ በርካታ ህፃናትም በአደጋው ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የአደጋው ዘገባ ገና እየተጠናከረ ሲሆን የሟቾች እና የተጎዱት ቁጥር እንዳይጨምር ተፈርቷል።ቢቢሲ በአካባቢው ከ150 በላይ ሰዎች በአካባቢው እንደነበሩ እና አያሌ ቤቶች በቶን በሚመዘን የቆሻሻ ክምር መቀበራቸውን ገልጧል። በቅርቡ በአዲስ አበባ ለእረጅም ጊዜ በነዋሪዎች የተያዙ ቦታዎች ላይ የነበሩ ነዋሪዎች እየተፈናቀሉ እንደነበር እና ብዙ ሺዎች ለጎዳና ላይ ሕይወት መዳረጋቸው ይታወሳል።የተቀሩት ደግሞ ዛሬ አደጋ ወደደረሰበት ቦታ ሄደው በቀን በሚያገኙት ገንዘብ እየተከራዩ እና የላስቲክ መጠለያ እየሰሩ መስፈራቸው ይታወቃል።  ለሞቱት ነፍሳቸውን በገነት ያኑርልን።

"የሞቱት ቁጥር ከ200 በላይ ይሆናሉ።እውነቱ እየተነገረ አይደለም" አዋዜ የደረሰው መልዕክት 
የአለምነህ ዋሴን ዘገባ ከእዚህ በታች ያዳምጡ። 



ከእዚህ በታች የምትመለከቱት አደጋው በደረሰበት አካባቢ የተገኙ ፎቶዎች ናቸው።



Above single photo is from BBC (ከእዚህ በላይ ያለው ፎቶ ብቻ ከቢቢሲየተወሰደ)






ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Friday, March 10, 2017

የሕወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ውሳኔ የወጣት ዮርዳኖስን ሕይወት እንዴት እንዳመሳቀለው (እውነተኛ ታሪክ እና ቪድዮ)

እውነተኛ ታሪክ 
ጉዳያችን/ Gudayachn 
www.gudayachn.com 
====================
ዮርዳኖስ ከንግድ ሥራ ኮሌጅ በባንክ እና ፋይናንስ ተመርቃ ሥራ ከያዘች አንድ አመቷ ነው።እንደተመረቀች ሥራ የያዘችው ከኮሌጁ ጎን የሚገኘው ባለ አስራ አንድ ፎቁ የቤቶች እና ቁጠባ ባንክ ነው።ዮርዳኖስ ከስራ በኃላ ቢያንስ በሳምንት ሁለት ቀናት መርካቶ የሚገኘው ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን የመዝሙር ጥናት ትሄዳለች።በእየሳምንቱ ቅዳሜ ከሰዓት በኃላ በ8 ሰዓት ላይ በቤተ ክርስቲያኑ የሰንበት ትምሕርት ቤት አዳራሽ የሚዘጋጀው ጉባኤ ከሌሎች የስራ ባልደረቦቿ ጋር መዝሙር ታቀርባለች።ዮርዳኖስ ስለ ብሔር፣ኤርትራ ስለሚባል ሀገር የምታውቀው ነገር የላትም።እቤት አባት እና እናቷ ስለ ፖለቲካ ሲያወሩ ከመስማት በቀር ነገሩ አይገባትም።ለእርሷ ጧት ሥራ መግባት ከስራ በኃላ ከቦርሳዋ ውስጥ የማይለያትን ነጠላዋን ተከናንባ ቤተ ክርስቲያን ተገኝታ ትምህርት መማር ወይንም በመዝሙር ማገልገል ነው።

ዮርዳኖስ በእንዲህ አይነት ሕይወት ላይ እያለች ነው በ1990 ዓም አንድ ምሽት በለሆሳስ ቤተ ክርስቲያን የተማረችውን መዝሙር እየመላለሰች እያዜመች ነበር አዲስ አበባ አሮጌው አይሮፕላን ማረፍያ  አካባቢ ቶታል ሶስት ቁጥር አውቶብስ ማዞርያ የሚገኘው ቤቷ የደረሰችው።የቤቷን የብረት በር ዘበኛው እንዲከፍትላት ደውሉን ለመደወል ስትል በሩ ክፍት መሆኑን ተመለከተች። በልቧ ዘበኛው ሰፈራቸው የሚገኘው ሱቅ ሲሄድ በሩን ገርበብ አድርጎ እንደሚሄድ ስለምታውቅ እንዳይዘጋበት በማሰብ መልሳ ክፍቱን ትታው ወደ ግቢው ዘለቀች።የእናት የአባቷ ግቢ ተተራምሷል። አባቷ ጋቢ እንዳደረጉ በነጠላ ጫማ፣እናቷ እረጅሙን ቢጃማ እንደለበሱ ቆመዋል ስድስት የሚሆኑ ፖሊሶች እና ሶስት ሲቪል የለበሱ ሰዎች ከእናት እና አባቷ ጋር ድምፃቸውን ከፋ አድርገው ይናገራሉ።ሶስቱ ሲቪል ከለበሱት ሰዎች ውስጥ አንዱ " ምንም ልብስ መቀየር ብሎ ነገር የለም።አሁን ሁላችሁም ወደ ቀበሌ! እዝያ ቃላችሁን ሰጥታችሁ ውሳኔው ይነገራል።የመንግሥታችን ትዛዝ ነው " አለ በትግርኛ ቅላፄ በተሞላ አነጋገር።

ዮርዳኖስ ጉዳዩ አልገባትም እናቷ ልጃቸውን ሲያዩ አቅፈዋት ማልቀስ ጀመሩ።ጥቂት ቆይቶ ግቢው በጎረቤት ሰዎች ተሞላ። ጎረቤቱ እየመጣ ዮርዳኖስን፣ወንድሞቿን እና ወላጆቿን እያየ ለቅሶውን አቀለጠው።ዮርዳኖስ የያዘችውን ቦርሳም እንድታስቀምጥ አልተፈቀደላትም በቆመችበት ከወንድሞቿ፣ወላጆቿ ጋር ወደ ቀበሌ ተወሰደች።ጉዳዩ ለካ የሕወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ኤርትራዊ ደም አለባቸው የተባሉ በሙሉ እየተለቀሙ ወደ ኤርትራ እንዲላኩ ስለተወሰነ ጉዳዩ እቤታቸው መምጣቱ ኖሯል።ዮርዳኖስ መጀመርያ ጉዳዩ የመሰላት የሆነ ወንጀል ተፈፅሞ ያንን ለማጣራት የሚደረግ እንደሚሆን አስባ ነበር።ነገሩ ሁሉ ተረጋግቶ ማታ ተመልሳ የምታጠናውን መዝሙር እና ቅዳሜ ስለሚከበረው የመንፈሳዊ ማኅበሯ ጉዳይ እያሰበች ከቤተሰቧ ጋር ፖሊሶቹ መኪና ላይ ወጣች።በልቧ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ነገሩን ሁሉ ለክፉ አታድርጉት ትላለች።ይህ ሁሉ ጉዳይ ለቤተሰቧ ችግር የማያመጣ ከሆነ በመጪው ቅዳሜ ሻማ ይዛ ልትመጣ ለመርካቶ ተክለ ሃይማኖት ተስላለች።ሆኖም ግን ዮርዳኖስ እና ቤተሰቧ በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ከቤት እንደ ቀልድ ወደ ቀበሌ እንደወጡ አልተመለሱም።የሕወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ውሳኔ ነው እና በሁለተኛው ቀን ዮርዳኖስ ከ  ወንድሞቿ እና ወላጆቿ ጋር ኤርትራ ወደተባለችው ምድር  ከተባረሩት 70 ሺዎች ውስጥ ተጨምረው ተላኩ። ዮርዳኖስ የሆነው ሁሉ ሕልም እየመሰላት አብራ ተሰደደች።ለምን እና ማን ይህንን ውሳኔ እንደወሰነ አታውቅም።

በወቅቱ ወደ ኤርትራ የተላኩት ተመልሰው ከኤርትራ ወጥተው ወደ ኬንያ፣የመን እና ሱዳን ተሰደዋል።የተሳካላቸው አውሮፓ እና አሜሪካ ገብተዋል።አንዳንዶቹ ዞረው ተመልሰው ኢትዮጵያ የመጡም አሉ። 

ዮርዳኖስ ስነ ልቦናዋም፣የተወለደችውም የምታውቀውም አዲስ አበባን እንጂ ኤርትራ የምትባል ምድር ናፍቃት አያውቅም።የማያውቁት አገር አይናፍቅም እንዲሉ።ሆኖም ግን ሕወሓቶች  እንደ ቀልድ ቢራ ፉት እያሉ የወሰኑት ውሳኔ ከቤቷ በረንዳ ላይ አስይዞ ከልጅነቷ እየመከሩ ያሳደጉ ጎረበቶቿን በእንባ እያራጨ ወደማታውቀው ምድር ገፋት። ይህ እውነተኛ ታሪክ እና እውነተኛ ስም ነው።

ከእዚህ በታች የምታዩት ቪድዮ በወቅቱ በሕወሓት ውሳኔ ከተባረሩት 70ሺዎች ውስጥ ኤርትራ ሲገቡ የነበረውን ሁኔታ ነው።የሚያለቅሱ አሉ፣ስሜታቸውን ማወቅ ያልቻሉ ነበሩ፣ግራ የተጋቡም ብዙዎች ናቸው።አንዳንዶቹ ያልተከፉ በሚመስል ስሜት እጃቸው ያወዛውዛሉ።ምናልባት ለስነ ልቦና እንደሚሆን መገመት ይቻላል እንጂ በእዚህ ወቅት ማንም ከነበረበት ቦታ ሲሄድ የእዛን ያህል ስሜት ሊኖረው አይችልም።ጉዳዩ አሳዛኝ መልኩ ያመዝናል እና።ዮርዳኖስ እና ቤተሰቧ ከእነኝህ ውስጥ ነበሩ ።ተወደድም ተጠላ የዮርዳኖስ ላይ የደረሰውን የዘመናችን የፖለቲካ ምስቅልቅል የሕወሓት የታሪክ ዶሴ ውስጥ ተፅፎ መጪው ትውልድም ሲያነበው ይኖራል።አንብቦ ምን እንደሚል አሁን ለመገመት አይቻልም።




ጉዳያችን GUDAYACHN

www.gudayachn.com

Tuesday, March 7, 2017

አርቲስቶቻችን ትውልድ እያስተማሩ ነው።የአርቲስት ሚካኤል ሚልዮን አርአያነት ያለው ተግባር።

በተለያዩ የፊልም ትወናዎቹ እና ዳይሬክተርነት የታወቀው አርቲስት ሚካኤል ሚልዮን የዘንድሮውን አድዋ በዓል በዓል እንዲሆን ካደረጉት አርቲስቶች ውስጥ ነው።አርቲስቱ በአድዋ በዓል የአባት አርበኞችን የጦር አለባበስ በመልበስ ለተተኪው ትውልድ ታሪኩን በሚገባ እንዲዘክር ከማድረጉም በላይ ከሌሎች የሙያ አጋሮቹ ጋር በመሆን ሕፃናትን ለማስተማር ላከናወነው ተግባር ሊመሰገን ይገባዋል።

ከእዚህ በታች የምታዩት ፎቶ አርቲስት ሚካኤል ሚልዮን በአድዋ በዓል አከባበር ስርዓት ላይ ትዕይንት ሲያሳይ ሲሆን ከስር በሳምንቱ መጨረሻ ላይ በሰይፉ ሾው ቀርቦ ያደረገውን አጭር ቃለ መጠይቅ ነው።

ፎቶ : - አርቲስት ሚካኤል ሚልዮን በምንሊክ አደባባይ የካቲት 23፣2009 ዓም የአድዋ በዓል ሲከበር ለበዓሉ ታዳሚ ትዕይንት ሲያሳይ 

ቪድዮ :- ሰይፉ ፋንታሁን  በኢቢኤስ ቲቪ ከአርቲስት ሚካኤል ሚልዮን ጋር ያደረገው ቃለ መጠይቅ።






አርቲስት ሚካኤል ሚልዮን በሰይፉ ሾው


ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Saturday, March 4, 2017

በቅርቡ ከተሰደዱት የቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስትያናት አስተዳዳሪ መላከ ፀሐይ ቆሞስ አባ ወልደ ትንሣኤ አባተ ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ


ከኢሳት ቴሌቭዥን የካቲት 23 እና  መጋቢት 2፣ 2017 እኤአ ስርጭቶች  ላይ የተወሰደ 
በቃለ መጠይቁ ላይ ለጥገና ተብሎ የተተከለው ብረት አብያተ ክርስትያናቱ ላይ አደጋ ማንዣበቡ እና ሌሎችም በርካታ ጉዳዮች ተነስተውበታል።
ክፍል አንድ 


ክፍል ሁለት 




ጉዳያችን GUDAYACHN

 www.gudayachn.com