ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Wednesday, December 30, 2020

እናት ፓርቲ የምርጫ ሰሌዳ አስመልክቶ የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተሞች ምርጫ ከሀገራዊ ምርጫው ጋር አብሮ እንዲደረግ የሚጠይቅ ደብዳቤ ለምርጫ ቦርድ መላኩን ጉዳያችን አውቃለች።

የተከበራችሁ የጉዳያችን ተከታታዮች፣ከእዚህ ደብዳቤ በተጨማሪ የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ምርጫ በተመለከተ ከሁለቱ ከተሞች ተፅዕኖ ፈጣሪነት አንፃር የተለያዩ ሃሳቦች ከተለያዩ ሰዎች እንደሚሰጡ ጉዳያችን ተገንዝባለች።ከእነኝህም ውስጥ የሚከተሉት ይገኙበታል።እነርሱም - 
1) የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተሞች ምርጫ ከሀገራዊ የተለየ ማድረጉ የሌሎቹ ውጤት ከታወቀ በኃላ የሁለቱን ከተሞች ብዙም አስፈላጊ እንዳይሆን ያደርገዋል፣
2) የለም፣የሁለቱ ከተሞች ምርጫ ውጤት የሌላውን ይወስናል፣
3) የሁለቱ ከተሞች ምርጫ ከሀገራዊው መለየቱ ሌላው ጋር የመረጡ መልሰው አዲስ አበባ እና ድረዳዋም መጥተው እንዲመርጡ ዕድል ይሰጣል።ይህም ለፅንፍ ኃይሎች የማጭበርበር በር ይከፍታል።
4) የሁለቱን ከተሞች ምርጫ መለየት ለፅንፍ ኃይሎች ዕድል ስለሚሰጥ ለሁከት በር ይከፍታል፣ወዘተ የሚሉ ሃሳቦች ይነሳሉ።
በመሆኑም የምርጫ ቦርድ ለእነኝህ ጉዳዮች በቂ ምላሽ ከወዲሁ በመስጠት ጉዳዩን ማጥራቱ ሃገራዊ ጥቅም አለውም።
ከእዚህ በላይ ያለው ጉዳያችን ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሰማችው ነጥቦች ናቸው እንጂ የእናት ፓርቲ ደብዳቤ ጋር ግንኙነት የለውም።
===========
ከእዚህ በታች የእናት ፓርቲ ለምርጫ ቦርድ የፃፈው ሙሉ ደብዳቤ ነው።



No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...