ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Wednesday, October 9, 2019

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሰ ያለውን ጥፋት በተመለከተ በኦስሎ፣ኖርዌይ ቅዳሜ ታላቅ ሕዝባዊ ስብሰባ ተጠርቷል።

ጉዳያችን / Gudayachn 
መስከረም 28/2012 ዓም (ኦክቶበር 9/2019 ዓም)
+++++++++++++++++++ 
በጉባኤው ላይ መሳተፍ በርቀት ከመቆጨት ያለፈ አንድ እርምጃ ነው።
  • በኦስሎ የሚገኙ ሁለቱም አጥብያዎች ካህናት እና ምእመናን በአንድነት በስብሰባው ላይ ይሳተፋሉ።
  • ከኦስሎ ውጪ  ለሚገኙ አጥብያዎች  ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በሙሉ እንዲያውቁት መልዕክት ደርሷል።
  • ከኦስሎ ውጪ የሚመጡ ተሳታፊዎች ይኖራሉ።
በመጪው ቅዳሜ ጥቅምት 1/2012 ዓም (ኦክቶበር 12/2019 ዓም)  በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የሰሜን አውሮፓ አህጉረ ስብከት የኦስሎ፣ኖርዌይ መካነ ቅዱሳን ቅዱስ ገብርኤል ወአቡነ ተክለ ኃያማኖት ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ሰበካ ጉባኤ አስተባባሪነት  በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሰ ያለውን ጥፋት በተመለከተ ሕዝባዊ ስብሰባ ተጠርቷል። በተመሳሳይ መልኩ በሀገር ቤት ከሃምሳ ከተሞች በላይ እና በባህር ማዶ በአሜሪካ እና አውሮፓ ተመሳሳይ ጥሪዎች በሰላማዊ ሰልፍ መተላለፋቸው ይታወቃል።


በኦስሎ፣ኖርዌይ በመጪው ቅዳሜ የሚደረገው ሕዝባዊ ስብሰባ ሊቃነ ጳጳሳት፣ካህናት እና በርካታ ምእመናን እንዲሁም ከቤተ ክርስቲያኒቱ ተከታዮች ውጪ በኢትዮጵያዊነታቸው የሚገኙ እንዳሉ ለማወቅ ተችሏል።ቅዱስ ሲኖዶስ በድንገተኛ ስብሰባው ላይም የቤተ ክርስቲያኒቱ ተከታይ ያልሆኑ ሁሉ አጋርነታቸውን እንዲገልጡ ባሳሰበው መሰረት በእዚህ ጉባኤ ላይም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በእዚሁ ዓውድ የሚታይ ነው።

በመጨረሻም በኦስሎ የሚደረገው ስብሰባ በሌሎች አካባቢዎች ከሚደረጉ ሰልፎች በተለየ ምእመናን በአንድነት ስብሰባዎችን በማዘጋጀት መምከር ሌላው አማራጭ በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚደርሰውን ፈተና የመቃወምያ መንገድነት በር የሚከፍት መልካም ሃሳብ እንደሚሆን ይታመናል።

አንዲት ናት ቤተክርስቲያን አንዲት ናት (በማኅበረ ቅዱሳን የመዝሙር ልዑክ የተዘጋጀ አዲስ መዝሙር)


ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...