Wednesday, November 2, 2016

ጥቅምት 23 የታሪካችን አካል (ቪድዮ)

ዛሬ ጥቅምት 23 ነው።እስካሁን አንድም ሐውልት ያልቆመላቸው ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ስላሴ የነገሱት የዛሬ 86 ዓመት ጥቅምት 23/1923 ዓም በአሁኑ አራዳ (ፒያሳ) የሚገኘው ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ነበር።ሃውልት ብቻ አይደለም በስማቸው የተሰየመውን ከዩንቨርሲቲ እስከ የካቲት 12 ሆስፒታል ስም እየደለዝን የእራሳችንን ታሪክ ለመፃፍ የሞከርን ጉደኞች አሁንም እኛው ነን።
ይህም የታሪካችን አካል ነው።

ንግስት መነን የመጀመርያ የልጃገረዶች ትምህርት ቤት መስራች፣የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል እና በኢየሩሳሌም ያሉ ገዳማት ያደርጉት አስተዋፅኦ ሁሉ የሚጠቀስ ታሪክ ነበራቸው።ከሁሉም የኢትዮጵያ ሴቶችን ንግስት መነን እኩልነትን ለማጠናከር የለፉ ነበሩ።ስለ ዓለም የሴቶች እኩልነት እናወራለን እንጂ የእኛዎቹን ፈላስፋዎች ማድነቅ አልፈጠረብንም።አንድ ቀን ይህንን ሁሉ ምስቅልቅል የሚያስተካክል እና ወደ እራሳችን ሀብት የሚመለከት ትውልድ ይነሳል።እስከዛው ድረስ ግን ለማያውቀው  ጠብታ ተጠራቅሞ ጋን ይሞላል እና እንዲህ የጠብታ ያህል እንነግራለን።



ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

No comments:

ወቅታዊው እና መጪው የኢትዮጵያ የፖለቲካ፣ምጣኔሃብታዊ እና ማኅበራዊ ሁኔታ በሶስት ርዕሶች ማጠቃለል ይቻላል።

  ፎቶ ፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የ2017 ዓም የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ መትከል ብሔራዊ ዘመቻ ሲከፍቱ። ========= ጉዳያችን ምጥን ======== በእዚህ ጽሑፍ ስር ሶስት ምጥን ርዕሶች ያገኛሉ። እነርሱም  አ...