Thursday, July 3, 2014

''ይህ ልብ የሚሰብር ዜና ነው በምንም ዓይነት አንገት የሚሰብር ግን አይደለም።በእዚህ አንገቱን የሚሰብረውን ሰው ያክል አንዳርጋቸው የሚፀየፈው ሰው የለም።አንዳርጋቸውን እኔ አውቀዋለሁ።ወያኔዎች እሱን በመያዛችን እናገኛለን የሚሉት ነገር ካለ ምንም ነገር አያገኙም።አንዳርጋቸው ትግሉን አንድ ምዕራፍ አሻግሮት ጨርሷል።አመራር ማብቃት ያለበትን ወጣቶችን አብቅቷል።አሁን ሂድ ጨርሰናል ተብሎ ለንደን መኖር ጀምሯል።ከአሁን በኃላ ብንወድቅም እየታገልን ነው የምንሞተው ብንሞትም እየገደልን ነው የምንሞተው።አሁን ጌሙ ተቀይሯል። ዛሬ ብዙ ሰዎች ሲያለቅሱ ሰምቻለሁ ግን አንዳርጋቸውን የምትወዱት ከሆነ አንዳርጋቸው የታገለለትን ዓላማ ነው መውደድ ያለባችሁ አንዳርጋቸውን አይደለም።አንዳርጋቸው ለቅሶ አይደለም የሚፈልገው አሁን አንዳርጋቸው የጀመረውን ትግል ዳር የሚያደርሱ ታጋዮች ነው የሚፈልገው።'' ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የግንቦት 7 ንቅናቄ ሊቀመንበር ዛሬ የተናገሩት (ቪድዮ)



ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

No comments:

በጠ/ሚ/ዐቢይና ሙ/ጥ/ዲ/ዳንኤል ላይ በውሸት ወሬ የዘመቱት ''አፈ-ጊንጦች'' በቴዲ አፍሮ ዘፈን ሊሸሸጉ ሲሞክሩ የኢትዮጵያ ሕዝብ እየሳቀባቸው ነው።

ጠ/ሚ/ዐቢይ አሕመድ እና ሙ/ጥ/ዲ/ዳንኤል ክብረት በታላቁ የዓባይ ግድብ ምርቃት ቀን። ======== ጉዳያችን ምጥን ======== አፈ ጊንጥነቱ እና የውርደት ካባው ''አፈ ጊንጥነት'' የሚለውን ...