Thursday, February 17, 2022

አስከሬን ከብቦ እየዘፈነ፣ሃይማኖት ከፍሎ እየፈነጠዘ እና አጼ ዮሃንስ የሞቱለትን ሰንደቅ ዓላማ እያወረደ እንደጣኦት አምልኩኝ ባዩ ሽብርተኛው ህወሓት እና የካቲት 11


  • ሽብርተኛው ህወሓት በትግራይ በህዝቡ ውስጥ ከፍተኛ ፍርሃት ፈጥሯል።ፍርሃቱ የተፈጠረው የትግራይ በህወሓት በግድ መለየት አዲስ ቅስፈት ይዞ ይመጣል የሚል ወሬ በሰፊው በትግራይ እየተዛመተ መምጣቱ መሆኑን  አስተማማኝ መረጃ ያላቸው እየተናገሩ ነው።

ጉዳያችን / Gudayachn

ዓለም ለልማት ይፋጠናል።ህዝቦች ከችግር ለመውጣት ይፍጨረጨራሉ።መሪዎች ህዝባቸውን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ ሌት ከቀን እንቅልፍ አጥተው ያድራሉ።ባለፈው ግማሽ ክፍለዘመን ውስጥ ቻይና በሚልዮን የሚቆጠሩ ዜጎቿን ከድህነት አላቃ ከመካከለኛ ገቢ እስከ ሚልዬነር አድርሳለች። ደቡብ ኮርያ ከድህነት ወጥታለች።ብራዚል እና ህንድ ድንቅ እድገት አሳይተዋል።ይህ ሁሉ የሆነው ህወሓት በደደቢት ከተመሰረተ በኋላ ነው። ዓለም በእዚህ መንገድ ሲራመድ ህወሓት ግን መሬቱን በደም እያጨቀየ፣አጥንት እየቆጠረ የኢትዮጵያውያንን መከራ አርዝሞ 27 ዓመታት ከኖረ በኋላ፣አፋር እና አማራን አጎሳቁሎ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ህዝብ አርግፎ ዛሬም ደደቢት የገባበትን 47ኛ ዓመት አስከሬን ከቦ በመዝፈን እና ሃይማኖት ከፍሎ በመፈንጠዝ ለማክበር ዓይኑን በጨው አጥቦ መጥቷል።

ህወሓት ግማሽ ክፍለ ዘመን ባለበት ብቻ ሳይሆን ቆሜለታለህ ያለውን የትግራይ ህዝብ በደም ነክሮ፣ልጆቹን አርግፎ እና ወደ የባሰ ረሃብ ውስጥ ከትቶ 47 ኛ ዓመቴን ላከብር ነው ዝፈኑልኝ እያለ ነው። የትግራይ እናቶች የዘመቱት ልጆቻቸው መሞት ምክንያት ትካዜ ላይ ቢሆኑም አስከሬን ከቦ፣ሃይማኖት ከፍሎ፣አጼ ዮሃንስ መተማ ላይ የሞቱላትን ሰንደቅ ዓላማ ከመቀሌ መንገዶች አውርዶ እንደጣኦት አምልኩኝ የሚለው ህወሓት አተርፍ ባይ አጉዳይ የሚለው አባባል የሚያጥረው ሆኗል።

ጥበብ ከመነሻውም አያውቀውም።ድንቁርና በራሱ ላይ እንደሙጃ ሰፍቶበታል። ሽብርተኛው ህወሓት በመጀመርያ ደረጃ የሚጠላው የትግራይን ህዝብ ነው።በስሙ ነግዶበት፣ሃብት አካብቶበት እና ከኢትዮጵያ እና ከኤርትራ ጋር አጋጭቶት እና ላለፉት ወራት ደግሞ ወደ ህዝቡ የተላከውን የእርዳታ እህል እንዳያልፍ አፋር ላይ ተኩስ ከፍቶ አቋርጦበት  የካቲት 11 ደደቢት የገባሁበትን አክብር እያለ ህዝቡን እያስገደደው ነው።የሚገርመው አሁን ላይ ሆኖም ህዝቡን የተረፈ ሰው ከቤት ፈልጉ ወደ ጦርነት ልማግደው እያለ እየቀሰቀሰ ነው።ይህንን የሚቀሰቅሱት እነ ጻድቃን ኝ ልጆቻቸውን በአሜሪካ ውድ ዩንቨርስቲዎች እየተማሩ ነው።የጻድቃን ገብረትንሣይ ልጅ በቅርቡ ከታወቀ የአሜሪካ ዩንቨርስቲ መመረቋን በማኅበራዊ ድረ ገጿ ላይ ለቃ ታይታለች። የትግራይ ወጣት ግን የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ለመፈተን የነበረውን ዕድል ሳይቀር ዘግቶበት ዝመት እያለ አስፈጅቶታል።የድንቁርናው ግዝፈት ደግሞ ፊደል ቆጠርን የሚሉት በውጭ የሚኖሩት የሽብርተኛው ህወሓት ደጋፊዎች እና በሃገር ውስጥ ያለው ጀሌውም ሳይቀር የትግራይን ህዝብ ወደየመጨረሻው ገደል ሲከተው እያዩ የቅስቀሳ ዘፈን ከመኝታቤታቸው ሳይወጡ እየለቀቁ ሲቀማጠሉ ማየት ምን ዓይነት የቅዠት ዓለም ውስጥ እንዳሉ መረዳት ይቻላል።አስከሬን ከቦ በመዝፈን፣ሃይማኖት ከፍሎ በመፈንጠዝ እና አጼ ዮሃንስ የሞቱለትን ሰንደቅ ዓላማ አውርዶ እንደጣኦት አምልኩኝ ማለት ወግ ያለው ሞትም ላለመሞት ህወሓት መወሰኗን በግልጥ ያሳያል።

ህወሓት ቀድሞ በህዝብ ህልውና ላይ መጥቷል።ቀጥሎ በሃይማኖት ላይ ዘምቷል።በሰሞኑ ህወሓታዊ የትግራይ ቤተክህነት እና የእስልምና ጉዳዮች ኮሚቴ ከኢትዮጵያ ለይቻለሁ ብሎ አውጇል።ይህ ከቅዱስ ሲኖዶስ እና ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች የበላይ አካል ትግራይ እንድትለይ በህወሓት መገድዷ፣ በትግራይ በህዝቡ ውስጥ ከፍተኛ ፍርሃት ፈጥሯል።ፍርሃቱ የተፈጠረው የትግራይ በህወሓት በግድ መለየት አዲስ ቅስፈት ይዞ ይመጣል የሚል ወሬ በሰፊው በትግራይ እየተዛመተ መምጣቱ መሆኑን  አስተማማኝ መረጃ ያላቸው እየተናገሩ ነው።እዚህ ላይ እነ ቢቢሲ አማርኛ ጨምሮ ''የትግራይ ክልል ካህናት እና  የእስልምና ጉዳዮች የበላይ አካል ከኢትዮጵያ ተለዩ ''እያለ ዘገባ ሰርቷል።

የቢቢሲ ዘገባ ሁለት ስህተቶች አሉበት።የመጀመርያው የትግራይ ካሕናት የት ተሰብስበው? ተፈራረሙ? ስንት የደብር እና የገዳማት አለቆች ተሰብስበው ወሰኑ? እንደ ቢቢሲ ያሉ የዜና አውታሮች የዜናውን ትክክለኛ ምንጭ ሳያገኙ ጥቂት ጳጳሳት የተሰበሰቡበት ፎቶ እና ቪድዮ ይዞ ማውጣት ነገ ማጣፍያው ያጥራል። በሁለተኛ ደረጃ ዘገባው የተወሰኑ ካሕናት የታዩበት ስብሰባ የተመራው በደብረጽዮን እና አለቃ ጸጋዬ ነው። ይህ ማለት ስብሰባው በካሕናቱ የተጠራ ሳይሆን የፖለቲካ አካሉ የሃይማኖት አባቶችን ጠርቶ መመርያ ነው የሰጣቸው።ቢቢሲ ይህንኑ ስብሰባ ሲዘግብ የደብረ ጽዮንን እና የአለቃ ጸጋዬን ፎቶ ቆርጦታል።ይህ በስህተት የተደረገ አይደለም።ጉዳያችን ላይም ሆነ በራሱ በህወሓት ሚድያዎችም ሁለቱም ጥቂት አባቶችን በመኖርያ ቤት ሰብስበው ሲያወያዩ ለቀዋል።ይህ ታሪክ ወደፊት የሚጠይቀው ነው።በመሆኑም የትግራይ አባቶች፣የደብር አለቆች፣የገዳማት አስተዳዳሪዎች እና ሊቃውንቱ ከቅዱስ ሲኖዶስ ለመለየት የወሰኑበት ስብሰባ ይዘት የለም።በእስልምናም የሆነው ይሄው ነው።ለህወሃት የተወዳደሩ የእስልምና አባት ጨምሮ ሰብሰብ ብለው ቪድዮ ተነስተው ከኢትዮጵያ የሃይማኖት ማዕከል ተለየን የሚል የሜዳ ላይ መግለጫ ነው የተሰጠው።ባጭሩ ህወሃት መቃብር አፋፍ ላይ ሆና ሃይማኖት ለማገት ሞክራለች።ሃይማኖት በመኖርያ ቤት በሚደረግ ስብሰባ አትታገትም።በእያንዳንዱ ልብ ውስጥ ጠልቃ የገባች ስለሆነ ደብረጽዮን እና አለቃ ጸጋዬ በስብሰባ አይሸብቧትም።

በመጨረሻም ይሄውም የሽብርተኛው ህወሓት በሃይማኖት ጉዳይ ላይ መቅደስ እና መስጊድ ገብቶ መክፈል ቢያንስ በረከት ይዞ አይመጣም ብቻ ሳይሆን ህወሓትን እንደተክለፈለፈ ወደ መጥፍያው መንገድ እየሄደ መሆኑን ትግራይ ውስጥ በግልጥ እየተነገረ ነው።ለመጠገን መራወጡ ግን ቀጥሏል።ይህ ደግሞ በተጨማሪ የትግራይ ወጣት ደም የሚያስፈስስ ነው።ለእዚህ የትግራይ ህዝብ ፍቃደኛ ነው ወይ? ላለፉት 47 ዓመታት የሞቱት ኢትዮጵያውያን አጥንት ዛሬ እንደ አዲስ ለፍርድ የሚቆምበት ጊዜ ነው።ስለሆነም መደናበሩም ምንም ለውጥ አያመጣም።አስከሬን ከቦ በመዝፈን፣ሃይማኖት ከፍሎ በመፈንጠዝ እና አጼ ዮሃንስ የሞቱለትን ሰንደቅ ዓላማ አውርዶ እንደጣኦት አምልኩኝ ማለት ህዝብ እና ክልሉን አብሮ ይዞ ለመጥፋት ካልሆነ በቀር የሚያመጣው ለውጥ የለም።ህወሓት 47 ዓመት ያላመጣው ብልጽግና የመቃብር አፋፍ ላይ ሆኖ ለትግራይ ህዝብ ይቆማል ብለው መቃብሩ አፋፍ ላይ ቆመው የሚያዩት የበለጠ ደንዝዘዋል።

================////===========

Friday, February 11, 2022

ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ ኖርዌይ ናቸው።ቅዳሜ የካቲት 12/2014 ዓም (ፌብርዋሪ 19/2022 ዓም) ከጉዳያችን እና የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ጋር በመተባበር በኦስሎ ልዩ የኪነጥበብ ዝግጅት አላቸው።


የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ መምህር፣ደራሲ፣የኪነጥበብ ሰው እና በአነቃቂ ንግግራቸው የሚታወቁት ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ ኖርዌይ ናቸው።ቅዳሜ የካቲት 12/2014 ዓም (ፌብርዋሪ 19/2022 ዓም) በኦስሎ የኪነጥበብ ዝግጅት ያቀርባሉ።በእዚሁ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በኖርዌይ ከጉዳያችን ጋር በመተባበር የሚቀርበው የኪነጥበብ ዝግጅት ላይ ልዩ መጣጥፎቻቸውን፣ በዝግጅትም በማቅረብም የተሳተፉበት አጭር ፊልም እና ካሳተሟቸው መጻሕፍቶች ውስጥ ጥቂት ኮፒዎች በዕለቱ ለሚገኙ የኦስሎ ነዋሪዎች ያቀርባሉ።የዝግጅት ቦታው ጥቂት ሰው ስለሚይዝ በሰዓቱ አለመድረስ የቦታ ማጣት ችግር እንዳያመጣብዎት፣በሰዓቱ ይገኙ።

ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ በኢትዮጵያ የጋራ ጉዳይ ላይ ንቁ ሃሳብ አመንጪ ናቸው።በቅርቡ በኢትዮጵያ ሃገር አቀፍ እርቅ ኮሚሽን ዕጩ ተመራጭ ናቸው።

ዝርዝር ሰዓቱን እና የቦታውን አድራሻ ከእዚህ በታች ከሚገኘው ፖስተር ላይ ይመልከቱ።



"እውን አንተን ወለደ?" ገጣሚ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ (ኦድዮ)





Monday, February 7, 2022

በትግራይ የኢትዮጵያ ኦ/ ተ/ ቤ/ክርስቲያንን ከቅዱስ ሲኖዶስ ለመለየት ህወሓት የሚሰራውን እኩይ ተግባር ለማምከን መንግስት፣ምዕመናን፣መንፈሳዊ ማኅበራት፣ማኅበራዊ ሚድያዎች፣ እና ከቤተክርስቲያኒቱ ዕምነት ውጪ ያሉ ሊያውቋቸው እና ሊከተሏቸው የሚገቡ ሦስት መሪ ሃሳቦች


ከውቅሮ 20 ኪሜ እርቀት የሚገኘው የአብርሃወአጽብሓ ገዳም
===============
ጉዳያችን / Gudayachn
===============

በትግራይ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ከቅዱስ ሲኖዶስ እንዲለዩ ህወሓት በእብሪት መወሰኗን ለብጹአን አባቶች በዶ/ር ደብረጽዮን መነገሩን ትናንት ጉዳያችን ጽፋ ነበር።የህወሓት ልሳኖችም እንደ መልካም ሥራ ሲዘግቡት ታይተዋል። የህወሓት ልሳኖችም ሆኑ የምዕራብ ሚድያዎች ለምሳሌ ቢቢሲ አማርኛ ''ትግራይ ያሉ ካህናት ወሰኑ'' በሚል ዜናውን ለቀውታል።ይህ መታረም ያለበት እና በህዝቡ ስም እየነገደ ያለው ህወሓት እና አሰርጎ ያስገባቸው መዋቅሩ መሆኑ መታወቅ አለበት።

አሁን የትግራይ ገዳማት ሊቃውንት ጉዳዩን አስመልክተው በቀጣይ ህዝቡን የሚነግሩትም ሆነ የሚጸልዩበት ጉዳይ ስለሚሆን እርሱን በሂደት የሚታይ ነው። በእዚህ ጽሁፍ ግን ለማቅረብ የምሞክረው የችግሩ መሰረታዊ ጭብጥ ፖለቲካ እና ፖለቲካ ስለሆነ ከውጭ ያለው ምዕመን፣መንግስት፣መንፈሳዊ ማኅበራት፣ማኅበራዊ ሚድያዎች እና ከቤተክርስቲያኒቱ ዕምነት ውጭ ያሉት ሊያውቁት እና ሊከተሉት የሚገባቸው ሦስት መሪ ሃሳቦችን ነው። እነኝህ ሃሳቦች ሁሉም ከተግባባቸው ችግሮቹ ተለይተው የፈጠረው ህወሓት ላይ እና እርሱን ተከትለው በእየዕምነቱ ውስጥ ተሰግስገው የህወሓትን ዓላማ ለማስፈጸም የሚጥሩትን ለመነጠል እና ምዕመኑን እና ቤተክርስቲያኒቱን ለማዳን ይረዳል።ሦስቱ መሪ ሃሳቦች -

1) በትግራይ ያሉ አባቶች በጊዜያዊ ሁኔታዎች እና በተጽዕኖ ውስጥ መሆናቸውን መረዳት እና ከበዛ ነቀፋ እና ክብርን የሚነኩ መልዕክቶች እንዳይተላለፉ ሁሉም ጥንቃቄ ማድረግ 

ይህ ማለት 
  • ጉዳዩ ፖለቲካ እንጂ ሃይማኖታዊ አለመሆኑን በሚገባ መረዳት፣
  • በትግራይ ያሉ ብጹዓን አባቶች አባቶቻችን መሆናቸውን ጉዳዩ ፖለቲካዊ መሆኑን ሁሉም እንዲያውቅ ማድረግ፣
  • ፖለቲካዊ ጉዳይ ከሃይማኖታዊው ጉዳይ እንዲለዩ አባቶችን በትህትና ደጋግሞ ማስረዳት
  • ከቤተ ክርስቲያኒቱ ቀኖና እና ዶግማ አንጻር የሚኬዱ አካሄዶች አግባብ ባለው በቤተክርስቲያኒቱ ቅዱስ ሲኖዶስ የሚሰጡ መግለጫዎች መጠበቅ።
2) ምዕመናን ሃይማኖት እና ፖለቲካ እንዳይቀላቀልባቸው ህወሓት በሃገር ውስጥም ሆነ በውጭ በስውር መዋቅሮቹ በቤተክርስቲያን ውስጥ የሚፈጥራቸውን ቀጣይ የልዩነት አጀንዳዎች ነቅቶ መጠበቅ እና በመንፈሳዊ አግባብ መከላከል።

ይህ ማለት 

  • ህወሓት አብያተ ክርስቲያናትን በቀጥታ በመዋቅሩ ስር አድርጎ የጦርነት ማካሄጅያ እና የሃብት ማጋበሻ ለማድረግ እንደሚፈልጋቸው ማወቅ እና ምዕመኑን ከእዚህ አደጋ መጠበቅ
  • ሁሉም ትግራይ የተወለደ ወይንም ትግርኛ ተናጋሪ ሁሉ ከህወሓት የቤተክርስቲያን መክፈል ጉዳይ ጋር አብሮ ይቆማል የሚል የተሳሳተ ሃሳብ መውጣት። በተለይ ይህ አለመሆኑን የሚያውቁት መንፈሳውያኑ እና ቤተክርስቲያኒቱ ውስጥ ያደጉት ብቻ እንጂ ከውጭ ያለው አይረዳውም።
  • ስለሆነም ከውጭ የተሳሳተ ሃሳብ ይዘው ትግራይ በመወለዳቸው ወይንም ትግርኛ በመናገራቸው ብቻ ለመግፋት ከሚሞክሩት መከላከል።
  • በማናቸው የማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ሁሉ ከአንደበት የሚወጡ ዘርን መሰረት ያደረጉ ንግግሮች ወዘተ መጠንቀቅ 

3) ከእዚህ በፊት በዘመነ ህወሓት ቅዱስ ሲኖዶስ ተከፍሎ በነበረበት ጊዜ የነበሩ ችግሮችን አሁን በልምድ መውሰድ 

ይህ ማለት 

  • አባቶች ጉዳዮችን ወደ መሃል የጋራ ነጥብ እስኪያመጡ ጊዜ መፈለጉን እና በትዕግስት፣ በጸሎት እና በጊዜው የሚፈታ መሆኑን ከባለፈው መማር፣
  • ሁል ጊዜ ጉዳዮችን ከማክረር ይልቅ ማለዘብ እና ችግሩ ህወሓት የጠነሰሰው ነገር ግን የህዝብ ጉዳይ ለማድረግ እንደሚሞክር አውቆ ይህንን በተግባር ማክሸፍ፣
  • በእዚህ ችግር ሂደት ጋር የባዕዳን እጅ እንዳለበት ማወቅ የእነርሱን አጀንዳ የሚያስፈጽሙትን መለየት እና ዓላማቸውን ማክሸፍ
  • ለምዕመናን መዳረስ ያለባቸው አገልግሎቶች ባለው መንገድ ሁሉ የበለጠ ተግቶ በመስራት ማድረስ መቻል።በእዚህ የቴክኖሎጂ ዘመን መንፈሳዊ አገልግሎት ከመቀሌ እስከ ሞያሌ ለማድረስ ቀላል ስለሆነ ይህንን ዕድል ተጠቅሞ ትክክለኛ የመንፈሳዊውን እና የነፍስ ጉዳይ ላይ ያተኮሩ ትምሕርቶች መስጠት፣
  • በትግርኛ የሚያስተምሩ መምሕራን ከመቼውም ጊዜ በላይ የህወሓት የመለያየት ፖለቲካ ቢያንስ መንፈሳዊነት አለመሆኑን ሕዝቡን ማስተማር እና
  • ክፉ የሚያደርግ እና ዛሬ ለመለያየት ከህወሓት ጎን ቆሞ ቤተክርስቲያንን ለማድማት የሚሞክር ነገ በሥጋውም ሆነ በነፍሱ የሚጎዳበት በመሆኑ እና ከሁሉም በላይ ደግሞ ችግሩ ከእዚህ በፊት እንደነበረው የቅዱስ ሲኖዶስ መለያየት በአንድ ቀን ሲፈታ አባቶች ሁሉን በይቅርታ አልፈው በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ስለሚፈታ ከአሁኑ በጥበብ መራመድን ማወቅ ጠቃሚ መሆኑን ማወቅ ተገቢ ነው።
በመጨረሻም ህወሓት ይህንን የትግራይ ቤተክርስቲያንን ከቅዱስ ሲኖዶስ የመለየት ምክር ባዕዳን እንደምክረ ሃሳብ ያቀረቡለት እና ኢትዮጵያውያንን ለመከፋፈል ሊጠቀሙበት ያሰቡት መሆኑን ሁሉም ወገን ሊረዳው ይገባል።ስለሆነም ከህወሓት የዘር ፖለቲካ ጋር አብሮ የሚሄዱ አስተሳሰቦችን ከራሱ ከትግራይ ህዝብ መንፈሳዊ ህይወት ጋር የተለየ መሆኑን አንጥሮ ማሳየት እና ማጉላት የህወሓትን ተንኮል ሜዳ ላይ ያሰጣዋል።ስለሆነም መንግስት፣ምዕመናን፣መንፈሳዊ ማኅበራት፣ማኅበራዊ ሚድያዎች፣ እና ከቤተክርስቲያኒቱ ዕምነት ውጪ ያሉ ሁሉ ጉዳዩን በስሜታዊነት ከማቀጣጠል ከላይ ከተነሱት ሦስት ነጥቦች አንጻር መቃኘት ጠቃሚ መሆኑን ሊረዱት ይገባል።

======================////==================


ህወሓት፣በቅዱስ ሲኖዶስ ስር ሆነው ትግራይ ለሚገኙ ጳጳሳት ከቅዱስ ሲኖዶስ እንዲለዩ ትዕዛዝ ሰጥቷቸዋል።ዓላማው የትግራይ ገዳማትን ለግብጽ ለማስረከብም ያለመም ነው።

 
ህወሃት ጳጳሳትን ሰብስቦ ትዕዛዝ ሲያስተላልፍ። ጳጳሳት ከፖለቲካ መሪዎች መመርያ ሲቀበሉ (ትግራይ)

👉የትግራይ ካህናት ሃይማኖት ወይንስ ህወሃት? ወሳኝ የነፍስ ጥያቄ ቀርቦላቸዋል።
👉የትግራይ ገዳማት እና አድባራት ሃይማኖታቸውን እንደሚመርጡ የኢትዮጵያ ህዝብ ያምናል።
👉ሃይማኖት በፖለቲካ ሸቀጥ ውስጥ እንደማትውል የትግራይ ካህናት የተማሩት ከህወሃት አይደለም።ከጥንታዊቷ ሃይማኖታቸው ነው። አሁን ህወሃት በነፍስ ጉዳይ ላይ መጥቷል።
👉የትግራይ ካህናት ህወሃትን ፖለቲካህን ወደ ሃይማኖታችን አታስገባ ሊሉት ይገባል።

===================
ጉዳያችን/Gudayachn
===================

የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ከቤተክርስቲያን ላይ እንዲያወርዱ ያዘዘው ህወሃት፣በቅዱስ ሲኖዶስ ስር ሆኖ ትግራይ ለሚገኘው ቤተ ክህነት ከኢትዮጵያ እንዲገነጠል ትዕዛዝ ሰጥቷል።ሽብርተኛው ህወሃት ቀድሞም በጠላትነት የፈረጃትን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ለ27 ዓመታት ያህል ቅዱስ ሲኖዶስን ለሁለት ከፍሎ፣በጎሳ ፖለቲካ በርዞ እና በሙስና አምሶ ወደ መቀሌ ከሄደ በኋላ አሁን የመጨረሻ ካርዱን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ላይ መዟል። ይሄውም ትግራይ የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ከቅዱስ ሲኖዶስ እንዲለይ ትግራይ የሚገኙ ጳጳሳት እና ጥቂት ካህናትን ጠርቶ ዶ/ር ደብረጽዮን እና አለቃ ጸጋዬ በተገኙበት ባሳለፍነው ሳምንት ውስጥ የህወሃትን ውሳኔ ገልጠውላቸዋል።

ይህ ብዙ ትንተና የሚፈልግ አይደለም።ድርጊቱ በራሱ ገላጭ ነው። የስብሰባው ጠሪ ህወሃት ነው።በስመ ምክክር ተደርጎ ተወሰነ ይባል እንጂ ውሳኔውን ነው ያሳወቃቸው።በውሳኔው ላይ አብረው የሰሩ ካህናት የሉም ማለት አይቻል ይሆናል።የትግራይ አድባራት እና ገዳማት በነጻነት የወሰኑት ውሳኔ ነው ወይ? ብሎ ለመደምደም እንደማይቻል ግን ግልጥ ነው።የእዚህ ዓይነቱን የትግራይ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የመመስረት ሃሳብ አመንጪው ህወሃት እና በስሩ ያሉ በውጭ ያለው መዋቅሩ ነው። በእዚህ ስራ ላይ ውስጥ ውስጡን ሲሰሩ እና በአውሮፓ እና አሜሪካም ተመሳሳይ የመገንጠል ስራ ሲያሴሩ ነበር። ሆኖም ግን አብዛኛው የትግራይ ህዝብ እንደጠበቁት ከተንኮላቸው ጋር አብሮ አልሄደላቸውም። ጉዳዩ በሙስና፣በዘረኝነት እና በወንጀል ውስጥ ያሉት የሚያመላልሱት የውስጥ ጉዳይ ሆኖ ሰንብቷል።

ህወሃት በቀጥታ ለባዕዳን ያደረ እና ኢትዮጵያን ለማፍረስ ዕቅድ ያለው፣የማፍረስ ስራውንም ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ለመጀመር ሲሰራ መኖሩ የአደባባይ ምስጢር ነው። ይህንን የትግራይ ካህናት ጠንቅቀው ያውቃሉ።ሃይማኖት በፖለቲካ ሸቀጥ ውስጥ እንደማትውል የትግራይ ካህናት የተማሩት ከህወሃት አይደለም። አሁን ህወሃት በነፍስ ጉዳይ ላይ መጥቷል።የትግራይ ካህናት ህወሃትን ፖለቲካህን ወደ ሃይማኖታችን አታስገባ ሊሉት ይገባል።

ኢትዮጵያ ከ3 ሺህ ዓመታት በላይ ስትኖር የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ እያለፈች ነው።ክርስትና ወደ ኢትዮጵያ በ34 ዓም ከገባ በኋላ እስከ ዘመነ መሳፍንት የእርስ በርስ ጦርነቶች ጊዜ ሁሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እንደ ተቋም እና አገልጋይ ካህናቶቿ እንዴት የዘመኑን ፈተና እንዳለፉት ያውቃሉ።መኳንንቱ ሲዋጉ የአብነት ተማሪዎች (በተለምዶ የቆሎ ተማሪ የሚባሉት) ከትግራይ ሸዋ፣ከሽዋ ጎንደር እና ሌሎች ቦታዎች ሁሉ እየሄዱ ካለምንም የዘር ልዩነት አንድነታቸውን ጠብቀው በኋላም የኢትዮጵያን አንድነት አስጠብቀው ኖረዋል።በእዚህ ዓይነት የተማሩት ናቸው በኋላ የቤተክርስቲያኒቱ ጳጳሳት፣ኢጲስቆጶሳት፣ቀሳውስት እና ዲያቆናት ሆነው ህዝቡን በእምነቱ አጽንተው ለምድራዊ የእርስ በርስ ጦርነት ሳይሆን ለነፍስ የጽድቅ እና ኩነኔ ጉዳይ ትኩረት ሰጥተው ያሻገሩት። ዛሬም ከስር ያሉት ካህናት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ጥለው በመሄድ ጽድቅ እንደሌለ ማንም ነጋሪ አይፈልጉም።ሃይማኖቱ በራሱ አስተማሪ ነው።ሆኖም ግን ህወሃት ከ30 ዓመታት በላይ በቤተክርስቲያኒቱ ላይ የሾማቸው የፖለቲካ ሹመኞች በክህነት ስም ህዝቡን ለመለያየት ሊያስገድዱት ይሞክራሉ። በሙከራቸው ሁሉ ግን ከእግዚአብሄር ተጣልተው እራሳቸውን መጋጨት ከሌለባቸው የማዕዘን ራስ ከተባለ ከክርስቶስ ጋር ይጋጫሉ እንጂ አንዳች አያተርፉበትም። 

ህወሃት ተስፋ ቆርጧል።ተስፋ በመቁረጡም ነው የመጨረሻ ያለውን የሃይማኖት ካርድ የመዘዘው።በእዚህም እመራዋለሁ የሚለውን የትግራይን ህዝብ እንደማያውቀው በድጋሚ ተጋልጧል።የትግራይ ጠቅላይ ቤተክህነት ይመስረት የሚለው የህወሃት ትዕዛዝ ህወሃት ለግብጽ የትግራይን ገዳማት ለመሽጥ ከገባው ፕሮጀክት ውስጥ የሚካተት ነው።የትግራይ ህዝብ በቶሎ ነቅቶ ሁኔታዎች እንዲስተካከሉ ካላደረገ ህወሃት የአክሱም ጽዮን ላይ የያዛቸው ድብቅ ፕሮጀክቶች ለባዕዳን አሰጥቶ በምትኩ ዓለም አቀፍ ድጋፍ የማግኘት ዕቅድ ሁሉ ያካተተ መሆኑ እየተነገረ ነው።ይህንን ደግሞ እምነት የለሹ ህወሃት ከእዚህ የበለጠ እንጂ ያነሰ እንደማያቅድ ግልጥ ነው።ጠቅላይ ቤተክህነት ብሎ ጥቂት ከሄደ በኋላ፣ ጳጳስ በግብጽ ለማሾም እና ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ድርጎ ሊቀበል ያለመ ነው። ይህንን የህወሃት ካድሬ ካህናትን ትተን የትግራይ ገዳማት እና አድባራት ይቀበሉታል ወይ? ተገደው አስፈጻሚ የሚሆኑ እና አልፈጽምም የሚሉ የሚደርስባቸው ቅጣት እንደሚኖር ይታወቃል።ሆኖም ቅዱስ መጽሃፍ የሚያስተምረን  ''ሥጋን የሚገድሉትን አትፍሩ።ይልቁንም ሥጋንም ነፍስንም በገሃነም የማጥፋት ስልጣን ያለውን ፍሩ'' ነው እና ህወሃትን በእዚህ ጊዜ የማይቃወም እና በሃይማኖት ጉዳይ አትግባ! የማይል ሃይማኖተኛ ነኝ ለማለት አይችልም።
==============////===========
  

Saturday, February 5, 2022

The Prime Minister of the Federal Democratic Republic of Ethiopia, H.E. Abiy Ahmed (Ph.D.) Historical Speech on the Opening of the 35th Ordinary Session of the African Union Assembly. ( watch his 15 minutes speech in English)

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአፍሪካ ሕብረት 35ኛ የመሪዎች ስብሰባ ላይ ያደረጉት ሙሉ ንግግር።
  • ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለጉባኤው አህጉር አቀፍ የአፍሪካ ህብረት የመገናኛ ብዙሃን ማዕከል እንዲመሰረት ጠይቀዋል።
  • የተባበሩት መንግስታት ከተመሰረተ ከ70 ዓመታት በኋላ አፍሪካ እንደ ጀማሪ አጋር መታየቷ ትክክል አለመሆኑን ለጉባኤው ገልጠዋል።
  • The PM Proposed the Establishment of an Africa Union Continental Media House.
  • He challenged the meeting on how Africa, even after 70 years since the UN was established, could be a junior partner.



Friday, February 4, 2022

Western Lies and False Narratives About Ethiopia



 
Source = CounterPunch.org 

Feb.4,2022
===============

War is big, loud, significant and attracts an audience; media likes it. Foreign wars (commonly Middle Eastern or African) distract from domestic chaos and reinforce a long-held prejudice of savagery and race, and the opposite, equally false notion of western superiority.

In all conflicts mainstream media plays a crucial role, often inflammatory, feeding the discord through a particular narrative. Western media claims it is independent, but this is fallacious; corporate owned or State sponsored, it is conditioned by a particular world-view, ideologically/politically, nationalistically, historically.

After war erupted in Ethiopia in November 2020 western media have played a major role in spreading mis-/disinformation and, occasionally, outright lies. Together with foreign powers led by the United States, international human rights groups and elements within United Nations Agencies, they attacked and undermined the Ethiopian government.

Statements are issued and regurgitated in various outlets: BBC, CNN, France24, Al Jazeera, etc., seemingly without verification; the more often something is repeated, the louder the drumbeat of insistence on its truth, no matter how incredible it may be. In November 2021 e.g., media carried the totally untrue story that TPLF forces were “200 km, or 400 km away from the capital Addis Ababa and could take the city in weeks”. Was this story spread in all innocence by the media; why would a responsible editor publish such information without checking it?

Such stories sensationalize events, build tension and attract public attention. In Ethiopia they falsely portrayed the terrorist Tigray Peoples Liberation Front (TPLF) as an ascendant force, the Ethiopian government as cruel and desperate, their forces deflated and inadequate.

The war was triggered by the TPLF’s preemptive attack on Federal Army bases on 4 November 2020; uncounted soldiers were killed, arms stolen. This fact (and the terrorist nature of the TPLF), is routinely disregarded by international media, and western governments, despite various TPLF spokespeople admitting it.

Imagine the outrage if such an assault took place against a western military base: there would be widespread fury, a sharp retaliatory response – or a protracted “war on terror” – unanimous support from allies, and wall-to-wall anger across the media. But, instead of condemning the terrorists, the US attacked the Ethiopian government, legitimized the TPLF, demanded PM Abiy Ahmed enter into negotiations with it. Again, would any western government be expected to negotiate with a terrorist gang that had carried out an act of treason? The hypocrisy, condescension and, yes, racism of the “international community” (the US and her bedmates), former or decaying imperialists, knows no limits.

Manufacturing Consent

An influential voice in the build-up to the conflict and a regular voice of media dis-/misinformation once fighting started, was the International Crisis Group (ICG). In a report published May 2021, Disinformation in Tigray – Manufacturing Consent for a Secessionist War, New Africa Institute (NAI) detail that, ICG played a critical role in driving the world to believe that TPLF had the upper hand in any ensuing conflict”.

A week before the TPLF attacked the Northern Command ICG publishedSteering Ethiopia’s Tigray Crisis Away from Conflict, stating, Tigray’s “well-armed regional paramilitary force is led by former national army generals. It also boasts a large militia full of war veterans. TPLF leaders say that many officers in the units of the Northern Command…would not be likely to support any federal intervention, and some could even break and join Tigray’s forces.” Such material, it is believed, emboldened the TPLF to launch their deadly attack, plunging Ethiopia into chaos.

NAI detail the extraordinary level of falsehoods, distortions and errors perpetrated by media; the dis-/misinformation campaign, they make clear, was an attempt “to manufacture consent for an unpopular irredentist, ethnic secessionist war that could not be justified in the eyes of the international public through honest reporting.” For Ethiopians it has been devastating, but within the halls of western power – Washington, mainly, but also London and, though less so, Brussels, it appears it was welcomed. A chance to destabilize not just Ethiopia under PM Abiy Ahmed, seen as too independent and potentially influential, but the Horn of Africa more broadly. The US and co. supported the TPLF politically, diplomatically and, many believe, militarily from the outset; mainstream news outlets obediently followed suit.

Media may refute the assertion of a conscious campaign of support for the TPLF; however, given the breadth of material published that either attacks the government, misleads the public or supports the terrorists, it is hard to deny.

Initially, a common excuse for the appalling coverage was the “communications blackout”. The Washington Post went as far as to blame the government for the dis-/misinformation, saying, “by blocking communications and access to Tigray, the [Ethiopian] government helped create conditions where disinformation and misinformation can thrive.” They only “thrive” if journalists/editors don’t do their jobs and check their material.

The menu of mis-/disinformation varies from the seemingly innocuous, e.g. describing the forced retreat of the TPLF to Tigray in December 2021, as a “withdrawal” (similar to reporting of the 2021 Gaza assault by Israel, in which BBC said X number of Palestinians had died and Y number of Israelis had been killed), to false accusations of “massacres, mass rape and sexual violence, looting, extrajudicial killings, genocide, ethnic cleansing and war crimes.” Savage portrayals of Ethiopian and Eritrean forces – drawn into the conflict after the TPLF bombed the capital Asmara – that NAI make clear “draw on old colonial tropes of Africans.”

The oft-repeated media claims of rape and gang rape by Ethiopian Federal Forces and Eritrean soldiers feed into this perverse notion of primitive Africans. Sexual and gender based violence was highlighted in the United Nations High Commissioner for Human Rights (OHCHR) and the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC), joint report, 3 November 2021. Premature and partial, it is full of generalized accusations of criminality.

Whilst admitting it is not an “exhaustive record of all relevant incidents”, its authors asserted that violations were committed by all parties to the conflict, including rape/gang rape. Assertions disputed by the Ethiopian government (which has said it will investigate) and refuted in Eritrea, where there is no culture of rape/gang rape, among society or the military. Within the TPLF however, rape/gang rape is part of its modus operandi.

TPLF military/para-military committed rape in the Ogaden region e.g., over a 25 year period of suppression of the ethnic Somali population. The same abuse took place against Oromo women for decades, and long before the conflict started in Tigray rape was a serious problem throughout the region; in 2019 a leading activist, Meaza Gidey tweeted: “rape culture is ubiquitous in Tigray oftentimes stigmatizing & shaming female rape survivors into marrying their rapist.”

While Tigray was in total chaos, on 11 February, 10 prisons in the region were emptied of all inmates. EHRC report that paperwork on the prisoners was destroyed, making, “Tracking major offenders nearly impossible and that it is one of the causes for the substantial increase of … major crimes.” The increase was so pronounced that the TPLF-mouthpiece Tigrai Media House (TMH) admitted that, “TPLF itself was responsible for the rise in crimes.” NAI report the TMH statement: “When news broke out that the Ethiopian army was making its way to Mekelle, the Tigray regional police forces and the prison forces disbanded abandoning their posts. As a result of this, the prison doors were left open and all the hardcore criminals escaped into the community.”

None of this information was reported by western media; misrepresentation through omissions, like this, has been widespread throughout.

Another example is the absence of coverage or condemnation of the Mai Kadra Massacre, one of many such TPLF atrocities. In November 2020 the village of Mai Kadra was the scene of a brutal attack by TPLF militia, the Samri and Tigrayan special police forces. The EHRC found that, “Samri, …local police and militia….killed hundreds of people beating them with batons/sticks, stabbing them with knives, machetes and hatchets and strangling them with ropes.” This atrocious, ethnically motivated attack, EHRC states, “May amount to crimes against humanity and war crimes.” The massacre was largely overlooked by mainstream media and ignored by foreign governments; after all, those slaughtered were savages – poor (black) Africans, murdered by other poor (black) Africans.

Mai Kadre is included in the OHCHR/EHRC report, though estimating the deaths at 200, in contradiction to the 600+ Amnesty International say were murdered. To “balance” this appalling atrocity the report refers to a highly disputed incident by the Ethiopian Defense Force (EDF) in Axum, where it is claimed more than 100 people were killed. Despite the fact that there is no evidence of such an attack and no bodies have ever been discovered the story was all over mainstream media.

Then there is the oft-repeated claim that the Abiy government blocked humanitarian aid to Tigray. In January 2021 The Economist announced that food was being used as a weapon by the government, and quoted that the US run Famine Early Warning Systems Network, saying that, “parts of central and eastern Tigray are probably one step from famine.” There was no famine (terrible hardship as in all war zones, yes), and according to Ethiopia’s National Disaster Risk Management Commission, by May 2021 all 4.5 million Tigrayans in need of food had received assistance, 70% of it subsidized by the government.

The whole area of UN humanitarian work was polluted by TPLF moles, including within the World Food Programme (WFP). In October 2021 whistleblowers from UN Ethiopia revealed that the “TPLF……. have networks within UN system.” In an attempt to purge the organisation of TPLF infiltrators on 27 September the Ethiopian government expelled seven UN officials for, “Dissemination of misinformation and politicization of humanitarian assistance;” the “diversion of humanitarian assistance to the TPLF; Transferring communication equipment to be used by the TPLF;” and, unbelievably, “reticence in demanding the return of more than 400 trucks commandeered by the TPLF for military mobilization and for the transportation of its forces since July 2021.” None of this was reported by international media or commented upon by the US administration, or any other western government.

The spirit of unity

The examples of betrayal and western media dis-/misinformation over the course of the conflict are endless. The sources of material and the way stories evolve and become disseminated is often convoluted, facts ignored, evidence found wanting, or manufactured entirely, as with the so-called “Axum massacre”, examined in detail by NAI. Various players, including Europe External Programme with Africa (EEPA), where it apparently originated, and discredited ex-BBC Africa journalist Martin Plaut, contributed to a concocted narrative, accepted by Amnesty International and forming the basis for a human rights report.

A positive consequence of the west’s betrayal has been the heartening community spirit engendered among Ethiopians. Divided for decades by manipulative TPLF ethno-policies, Ethiopians, at home and abroad, have united against this group of self-supporting interconnected adversaries: The terrorist TPLF, “The West”, specifically the United States and the international mainstream media.

And now, as the fighting subsides and the country collectively draws breath the work of reconciliation and healing must begin.

To this end, in the hope of facilitating “national reconciliation”, PM Abiy announced the extraordinary step, which angered many Ethiopians, of granting an amnesty for some of the country’s most high-profile political prisoners and parliament has established a “Commission for National Dialogue”, “to pave the way for national consensus and keep the integrity of the country.” Despite the TPLF and their partners in crime, the Oromo Liberation Front (OLF), refusing so far to participate, this is encouraging.

Ethiopia has suffered terribly over the last year or so, and it will take time to recover. But, if the sense of national unity that has been created over the past year or so is maintained, healing will come more readily and this wonderful country will emerge stronger than ever.

=================

Graham Peebles is a British freelance writer and charity worker. He set up The Create Trust in 2005 and has run education projects in Sri Lanka, Ethiopia and India.  E: grahampeebles@icloud.com  W: www.grahampeebles.org

Source of Article = https://www.counterpunch.org/2022/02/04/western-lies-and-false-narratives-about-ethiopia/ 

Wednesday, February 2, 2022

ጠልነት ወቅታዊ የሃገራችን ችግር ነው።ከዘረኝነት እኩል አደገኛ ነው።መገናኛ ብዙሃን ሊዘምቱበት ይገባል።

===============

ጉዳያችን / Gudayachn

==============

በሽታ ህመሙ የሚሰማ እና ህመሙ በቀላሉ የማይሰማ በሚል መክፈል እንችላለን።በአካላችን ላይ የሚደርስ በሽታ ውስጣዊ በሽታችንንም ሆነ ላይኛውን አካላችንን ቢያመን የቱ ጋር ህመሙ እንዳለ ስለምናውቀው ወደ ሃኪም ዘንድ ሄደን በመታከም እንድናለን። ህመማቸው በአካላችን ላይ የማይታዩ ውስጣዊ የስሜት ችግሮች ግን አደገኛ የሚያደርጋቸው ታማሚው በራሱ እንደታመመ አለማወቁ ነው።

በሃገራችን አሁን የሚታየው አንዱ ችግር የጠልነት ችግር ነው።የጠልነት ችግር ምክንያታዊነት የሌለው በአብዛኛው የጠልነት ችግር ያለበት ሰው በራሱ የታመመ የማይመስለው ወይንም ለጠልነቱ የራሱን ምክንያት ያለውን ሰጥቶ በጥላቻ ላይ ሌላ ጥላቻ እየደረበ በእራሱ አዕምሮ ላይ በጠልነት የተለወሰ መርዝ እያኖረ እራሱን የሚጎዳ እና ሌሎችም እንደርሱ ጠል እንዲሆኑ እያወቀ ወይንም ሳያውቅ የሚያዛምት ሰው ነው።በተለይ በአሁኑ ጊዜ ዘረኝነት ምክንያታዊ አለመሆኑ እየታወቀበት ሲመጣ ጠልነት በሰፊው እየተንሰራፋ ነው።

ጠልነት ከእኛ ጎሳ ውጭ የሆነ ሰው ወይንም የተለየ እምነት ያለው አልያም ከእኛ አስተሳሰብ ውጭ ነው የምንለውን ሰው፣ማንነቱን ሳናውቅ፣ደግ ይሁን ክፉ፣የተማረ ይሁን ያልተማረ ገጠር ይሁን ከተማ ማንነቱን ሳናውቅ በአዕምሯችን ውስጥ በፈጠርነው ምናባዊ ፍረጃ ብቻ ያንን ሰው የመጥላት ክፉ በሽታ ነው። ባብዛኛው ጠልነቱን የሚፈጥሩ ሰዎች በራሳቸው የሚዛናዊነት ዕይታ ችግር ያለባቸው ሲሆኑ በአስተዳደጋቸውም ነገሮችን የመመርመር፣የማድመጥ እና የትዕግስት ክህሎትን ከአደጉበት ውጭያዊ አካባቢ ለማግኘት ያልታደሉ ወይንም በህይወት ልምዳቸውም ይህንኑ ማዳበር ያልቻሉ ናቸው። እገሌን ለምን ጠላህ/ሽ? ተብለው ሲጠየቁ የሚመልሱት የተሟላ መልስ እንደሌለ የሚያውቁት በራሱ ሲጠየቁ እንጂ ቀድሞም ምክንያት የላቸውም። ለእራስ ማታለያ ግን የሚሰጥ ምክንያት አላቸውም።እነኝህ ምክኛቶች ግን መልሰው ሲመለከቱት ለራሳቸው አስደንጋጭ መሆናቸውን በእርጋታ ቢመለከቱት ጥሩ ነበር።

አንድ ሰው በራሱ መርጦ ባልተወለደበት ቦታ ምክንያት መጥላት፣ አንድ ሰው በሚያምነው ዕምነት ምክንያት መጥላት፣ አንድን ሰው በሚወደው ነገር ወይንም በግል የኑሮ ዘይቤው ምክንያት ከእኛ ጋር ስላልተመሳሰለ ብቻ መጥላት እና የመሳሰሉት ሁሉ አደገኛ የጥላቻ ምክንያት ሆነው ሲቀርቡ መመልከት አሳዛኝ ነው።ጠልነት በተለይ ከሚዛናዊነት እና ሁሉን ለማገልገል ወይንም ለመርዳት ካለ ፍላጎት ጋር ስለሚጋጭ በራሱ አድሏዊነትን ይፈጥራል።ስለሆነም ጠልነት የሚያራምድ ሰው ለጊዜው ለራሱ ጥሩ እና ፍትሃዊ ነገር እየሰራ ያለ ይምሰለው እንጂ ውሎ አድሮ ትክክል አለመሆኑን ይረዳዋል። የጠልነት በሽታ አለብኝ? ወይንስ የለብኝም? ብሎ መመርመር ያስፈልጋል። ህመሙም መድሃኒቱም ያለው እራሳችን ውስጣችን ነው። ለሃገር ትልቅ አስተዋጽኦ ያደረጉ ምሁራን በተደረገባቸው የጠልነት ዘመቻ እነርሱ የተናገሩት ሁሉ ጥፋት መስሎን እራሳችንን የምናታልል፣በራሳችን የእምነት አባቶች ላይ የጠልነት ስሜት የምናስተናግድ፣በማኅበራዊ ሚድያ የጠልነት ዘመቻ የተደረገበት ሰው ምን አንዳለ ሳናውቅ በውስጣችን የጠል ስሜት አብቅለን በአዚያው ደምድመን የምንኖር አንጠፋም። 

ጠልነት የትኛውም እምነት አይቀበለውም።ነገር ግን በእምነት ድርጅቶች ውስጥ ሳይቀር ሰርጾ የሚገኝ አደገኛ ስሜት ነው።ሰውን ያህል ቡር ፍጥረት ጠልቶ ጽድቅ የለም።መርዛማ ጠልነትን ይዞ ውስጣዊ መረጋጋት አይኖርም።ሰዎች ሊጠሉን ይችላሉ።ይህ በእኛ የሚወሰን አይደለም።የመውደድም ሆነ የመጥላት መብታቸው ይከበራል።ነገር ግን የጥላቻ ስሜት በጠል አራማጁ ግለሰብ ውስጥ የሚገኝ መርዝ በመሆኑ ለጠል አራማጁ ቀሪ እና አደገኛ ውስጣዊ ቅሪት ሆኖ ይጎዳዋል እንጂ የሚያተርፈው ነገር የለም።ስለሆነም ሌሎች የጥላቻ ባህር ውስጥ ሲገቡ እራስን ከእዚህ የጥፋት ባህር አትርፎ የራስን ጤንነት መጠበቅ አስፈላጊ ነው። 

ባጠቃላይ ጠልነት አደገኛ ወቅታዊ የሃገራችን ችግር ነው።ልጆች ቤት ውስጥ ከወላጆቻቸው በሚሰሙት እና በመልክ በማያውቁት ዕምነት፣የመንግስት ባለስልጣን ወይንም ታዋቂ ሰው ላይ በሚሰነዘር የጠልነት ወሬ የተነሳ የማያውቁትን ሰው ጠልተው ይኖራሉ።ይህም እንደ ባህል ሆኖ ጠልነትን ከልጅነታቸው ይለማመዳሉ።ጠልነት ሃገር ያፈርሳል። ጠልነት ጦርነት ያስነሳል።ጠልነት በሽታ መሆኑን በግልጥ የመገናኛ ብዙሃን አስፍተው ሊናገሩበት፣የስነ ልቦና ጠበብት ህዝቡን ሊያስተምሩበት ይገባል።ይህ ካልሆነ የሰዎችን መልካም ሃሳብ ከመቀበል በፊት በጭፍን የመጥላት ውጤት መልካሙንም ሃሳብ የማንቀበል ብኩን እንዳንሆን መጠንቀቅ ያስፈልጋል።ሁሉም ከእራሱ ጋር መወያየት አለበት። 

==============////==============

በጠ/ሚ/ዐቢይና ሙ/ጥ/ዲ/ዳንኤል ላይ በውሸት ወሬ የዘመቱት ''አፈ-ጊንጦች'' በቴዲ አፍሮ ዘፈን ሊሸሸጉ ሲሞክሩ የኢትዮጵያ ሕዝብ እየሳቀባቸው ነው።

ጠ/ሚ/ዐቢይ አሕመድ እና ሙ/ጥ/ዲ/ዳንኤል ክብረት በታላቁ የዓባይ ግድብ ምርቃት ቀን። ======== ጉዳያችን ምጥን ======== አፈ ጊንጥነቱ እና የውርደት ካባው ''አፈ ጊንጥነት'' የሚለውን ...