ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Sunday, January 13, 2019

የጥምቀት በዓል በእዚህ ሳምንት መጨረሻ በመላዋ ኢትዮጵያ እና በባሕር ማዶ ይከበራል።በዓሉ የብሔራዊ አንድነታችን እና መተሳሰባችን አንዱ መገለጫ ነው።

  • ኦስሎ፣ኖርዌይም የበዓሉ ታዳሚ ነች። 
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን  በአደባባይ ከሚከበሩት በዓላት ውስጥ ጥምቀት አንዱ እና ዋናው ነው። ዘንድሮ የሚከበረው የጥምቀት በዓል በያዝነው ሳምንት ከዓርብ ጥር 10/2011 ዓም (ጃንዋሪ 18/2019 ዓም) ከቀትር በኃላ ጀምሮ ታቦታት ወደ ጥምቀተ ባሕሩ ወጥተው  በመላዋ ኢትዮጵያ እና በባሕር ማዶ በሚገኙ ኢትዮጵያን ዘንድ ይከበራል።በዓሉ የብሔራዊ አንድነታችን እና መተሳሰባችን አንዱ መገለጫ ነው።

በዓሉ በኦስሎ፣ኖርዌይ የኢትዮጵያ ኦ/ተ/መካነ ቅዱሳን ቅዱስ ገብርኤል ወአቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያንም በድምቀት ይከበራል።በበዓሉ ላይም የደቡብ አውሮፓ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የሚገኙ ሲሆን መምህር ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ ከኢትዮጵያ  በስብከተ ወንጌል ያገለግላሉ።

ጥምቀት አዲስ አበባ ቪድዮ (ከዩቱብ ፋይል)

ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...