Thursday, February 6, 2014

እባክህ ክፈለኝ ያስተማርኩበትን (አጭር ግጥም የኢትዮጵያን ገበሬ ለተሳደቡት የኢህአዲግ ከፍተኛ ባለስልጣን)



አንጀቴን አስሬ ፣
ከእኔ ይቅር ብዬ አንተን አስተምሬ፣

ዛሬ ያወቀ መስሎት…. ''ባዶ እግር'' ነህ አለኝ፣
  ትስቅብኝ ጀመር ጫማ ስለሌለኝ፣

ባለጫማ መሆን  መቼ ጠፋኝ እኔ፣
መልበስ መሽቀርቀሩ አንተን አደንቁሬ።

ላስተምርህ ብዬ እንጂ ነገ እንድትሻገር፣
መስሎኝ----እኔ መራቆቴ ላንተ ልሆን ማገር።

ግና ምን ያደርጋል አንተም አልተማርክም፣
    ማስተዋል ነስቶሃል ከእኔ አልተሻልክም።

እናም ---እኔ ባዶ ሆኘ ያለበስኩበትን፣
            እባክህ  ክፈለኝ ያስተማርኩበትን።

ጉዳያችን
ጥር 30/2006
ምሽት ኦስሎ፣ኖርዌይ

No comments:

Urgent Justice to the Ethiopian Orthodox Tewahido Church in Greece. Attention: The Hellenic Ministry of Education, Religious Affairs department, and the Athens Police

Under this special report, you will find the following subtitles:  The Ethiopian Orthodox Church foundation in Greece. The Ten years Controv...