Thursday, February 6, 2014

እባክህ ክፈለኝ ያስተማርኩበትን (አጭር ግጥም የኢትዮጵያን ገበሬ ለተሳደቡት የኢህአዲግ ከፍተኛ ባለስልጣን)



አንጀቴን አስሬ ፣
ከእኔ ይቅር ብዬ አንተን አስተምሬ፣

ዛሬ ያወቀ መስሎት…. ''ባዶ እግር'' ነህ አለኝ፣
  ትስቅብኝ ጀመር ጫማ ስለሌለኝ፣

ባለጫማ መሆን  መቼ ጠፋኝ እኔ፣
መልበስ መሽቀርቀሩ አንተን አደንቁሬ።

ላስተምርህ ብዬ እንጂ ነገ እንድትሻገር፣
መስሎኝ----እኔ መራቆቴ ላንተ ልሆን ማገር።

ግና ምን ያደርጋል አንተም አልተማርክም፣
    ማስተዋል ነስቶሃል ከእኔ አልተሻልክም።

እናም ---እኔ ባዶ ሆኘ ያለበስኩበትን፣
            እባክህ  ክፈለኝ ያስተማርኩበትን።

ጉዳያችን
ጥር 30/2006
ምሽት ኦስሎ፣ኖርዌይ

No comments:

በጠ/ሚ/ዐቢይና ሙ/ጥ/ዲ/ዳንኤል ላይ በውሸት ወሬ የዘመቱት ''አፈ-ጊንጦች'' በቴዲ አፍሮ ዘፈን ሊሸሸጉ ሲሞክሩ የኢትዮጵያ ሕዝብ እየሳቀባቸው ነው።

ጠ/ሚ/ዐቢይ አሕመድ እና ሙ/ጥ/ዲ/ዳንኤል ክብረት በታላቁ የዓባይ ግድብ ምርቃት ቀን። ======== ጉዳያችን ምጥን ======== አፈ ጊንጥነቱ እና የውርደት ካባው ''አፈ ጊንጥነት'' የሚለውን ...