Thursday, January 30, 2014

አሜሪካ በኢትዮጵያ ጉዳይ ተነቃቃች …ወይንስ ?(አጭር ማስታወሻ)



አሜሪካ ዘግይታም ቢሆን በኢህአዲግ ላይ የምታደርገውን ድጋፍ ቀስ በቀስ ለመሳብ እያሰበች ይመስላል።በሳምንቱ ውስጥ አሜሪካ ለኢትዮጵያ የምትሰጠው እርዳታም ሆነ ድጋፍ የዜጎችን ከመሬታቸው መፈናቀል የሚያስከትል እንዳይሆን ቅድመ ሁኔታ እንዲኖረው መወሰኑ በተነገረ በቀናት ውስጥ የኢትዮጵያ መንግስት የሰብአዊ መብት ካላከበረ በቀር  ለፖሊስ እና ለጦር ኃይል ከአሜሪካ የሚሰጠው ድጋፍ በቅድመ ሁኔታ ስር እንዲሆን ወስኗል።

አሜሪካ  ይህንን ለማድረግ 23 አመታት ብትዘገይም ለዛሬው እርምጃ መጀመር ግን ምክንያቶቹ ከእዚህ በታች ከተዘረዘሩት የትኞቹ ይሆኑ?

1/ በድንገት ለኢትዮጵያ ሕዝብ ማሰብ ጀምራ?

2/ የቻይና በኢትዮጵያ መንሰራፋት ለአፍሪካም የተረፈ መሆኑ አስግቷት?

3/ ኢትዮጵያውያን በዋይት ሃውስ ደጃፍ ለአመታት ያደረጉት ሰልፍ በድንገት ትዝ ብሏት?

4/ የኢትዮጵያ ሕዝብ በኢህአዲግ አሰራር መማረሩን እና መቁረጡን ስላወቀች?

5/ የኢትዮጵያ ሁኔታ ወደባሰ መስመር የመሄዱ አዝማምያ ለአካባቢው አለመረጋጋት መዘዝ ስላለው የአካባቢ አረጋጊ ኃይል ላለማጣት?

6/ የድል አጥብያ አርበኛ ለመሆን?

መልሱ በሂደት የሚታይ ነው።

ላለፉት 23 አመታት ኢህአዲግ ሲታሰብ አሜሪካም አብራ ነበረች።ይህ ሀቅ ነው።ኢትዮጵያ የጎሳ ፖለቲካ ሲታወጅባት ጉዳዩ አደገኛ መሆኑን በትንሹ ለጎሳ ፖለቲከኛ መንግስት ስትናገር ብንሰማት ጥሩ ነበር። የሆነው ሆኖ የዛሬ የአሜሪካ መነቃቃት ደስ የሚል ነው።አሜሪካ ግን ተነቃቃች ማለት የሚቻለው ለኢትዮጵያ አንድነት፣የግዛት ሉአላዊነት እና የባህር በር ባለቤትነት የማያወላውል አቋም ስታሳይ ነው። ኢትዮጵያ ከፊቷ የሚጠብቁ ብዙ ጉዳዮች አሏት እና ዛሬ ማለት የሚቻለው አሜሪካ በርታ በይ ቀጥይ ገና ነሽ ይመስለኛል።

No comments:

የክፍለዘመናችን የኢትዮጵያ የስልጣኔ ማማ መለኪያ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ጉባዔ ነገ በአዲስ አበባ ይከፈታል። ህልውናችን፣መጪው ስልጣኔያችን፣ሰላማችን እና ዕድገታችን በእዚህ ጉባዔ ውጤትና ሒደት ይወሰናል።

Foto : Fana digital  የቻልን በሀሳብ እና በጸሎት፣ ያልገባን እና የተምታታብን ደግሞ እኪገባን በዝምታ በመቆየት ኢትዮጵያን እናግዛት። ========= ጉዳያችን ልዩ ========= ኢትዮጵያ ሐምሌ 8፣2018 ዓም...