ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Wednesday, October 16, 2013

ኢቲቪ የደበቀኝ ልማት

የኢትዮጵያ ሕዝብ የመስራት ባህሉ ጠንካራ ነው።ያጣው ሃብት የማፍራት ዘዴ እና የዘመናዊ እውቀት ክህሎት ነው።በእዚህ ፊልም ላይ የምንመለከተው ''ኮምዩኒት ብሪጅ'' የተሰኘ ድርጅት በጎጃም እና በጎንደር መካከል የሚያገናኘውን ድልድይ የዛሬ ሶስት ዓመት በ 2003 ዓም ግንባታውን ሲያጠናቅቅ ነው።

የህዝቡን ጥንካሬ እና የመስራት ፍላጎት የምንመለከትበት አንዱ መንገድ ድልድይ ባይኖርም ወንዶችም ሆኑ ሴቶች በገመድ ተንጠላጥለው የማለፍ ልምዳቸውን ነው።የእዚህ አይነቱን የማለፍ ድፍረት ያለው ሕዝብ የሚያሰራው እና ለትምህርትም ሆነ ለእውቀት በር የሚከፍትለት ቢያገኝ ትልቅ እድገት ላይ የመድረስ አቅም እና ድፍረት እንዳለው መገንዘብ ይቻላል።

የኢህአዲግ ተቀፅላ የሆነው ''የአማራ ልማት ማኅበር'' በሚልዮን የሚቆጠር ብር እያወጣ የቢራ ፋብሪካ ለሕዝቡ ከሚገነባ እንደዚህ የተረሱ አካባቢዎችን ቢመለከት እና ገንዘቡን እውቀት እና ክህሎት ማዳበርያ ላይ ቢያውለው እንዴት ጥሩ ነበር? ኢቲቪ የደበቀኝ ልማት።




ጉዳያችን GUDAYACHNgetachewb221@gmail.com

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...