Tuesday, July 9, 2013

አምባሳደር ብርሃኑ ዲንቃ አረፉ

አምባሳደር ብርሃኑ ዲንቃ 


  • በዲፕሎማሲው አለም ከእሩብ ክፍለዘመን በላይ አገልግለዋል።  
  • በካይሮ፣በዋሽግተን፣ነውዮርክ፣ጅቡቲ የሀገራቸው አምባሳደር ሆነው ሰርተዋል፣
  • በካምቦድያ፣ደቡብ አፍሪካ፣ሱማልያ በተባበሩት መንግሥታት ወኪልነት ሰርተዋል፣
  • በደቡብ ሱዳን የዳርፉር ግጭት በአፍሪካ አንድነት ድርጅት  ስር የነበረውን ''የስልጣን መጋራት ኮሚሽንን'' እስከ ስምምነቱ ፊርማ ድረስ በሊቀመንበርነት መርተዋል፣
  • የ ቀድሞው የተ.መ.ድ. ዋና ፀሐፊ ልዩ አማካሪም ሆነው ሰርተዋል፣
  • አሁን በቅርቡ ሕይወታቸው እስካለፈበት ድረስ በኬንያ በቀድሞው የምርጫ ወቅት ተነስቶ በነበረው ግጭት ''የእውነት አፈላላጊ ኮሚሽን'' ውስጥ በቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኪባኪ ተሾመው  በአለምአቀፍ ኤክስፐርትነት እና የኮሚሽኑ የሪፖርት ኮሚቴ ሊቀመንበር ሆነው እያገለገሉ ነበር።

አምባሳደር ብርሃኑ ዲንቃ በኒውዮርክ በነበረባቸው የካንሰር ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ትናንት ሰኞ ሰኔ 1፣2005 ዓም ሕይወታቸው ማለፉን የኬንያ ጋዜጦች ዘግበዋል።እረፍተ ነፍስ ይስጥልን።
source- Daily Nation,July 9,2013
            - The standard Digital news, July 8,2013

1 comment:

Anonymous said...

NEFS YIMAR

የክፍለዘመናችን የኢትዮጵያ የስልጣኔ ማማ መለኪያ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ጉባዔ ነገ በአዲስ አበባ ይከፈታል። ህልውናችን፣መጪው ስልጣኔያችን፣ሰላማችን እና ዕድገታችን በእዚህ ጉባዔ ውጤትና ሒደት ይወሰናል።

Foto : Fana digital  የቻልን በሀሳብ እና በጸሎት፣ ያልገባን እና የተምታታብን ደግሞ እኪገባን በዝምታ በመቆየት ኢትዮጵያን እናግዛት። ========= ጉዳያችን ልዩ ========= ኢትዮጵያ ሐምሌ 8፣2018 ዓም...