Monday, April 15, 2013

''አቤት በሉን''...''ለምን ልጣት ለምን ትዘን፣ ሆናኝ ጎኔ ለኔ በዚች አለም።''

ከእዚህ በታች የምታገኙት ግጥም እና ዘፈን ከያንያኑ ለሴት ልጅ መብት የደረሱት እና ያቀነቀኑት ነው። ነገር ግን ሀገር በሴት(እናት)  ትመሰላለች እና ለእናት ሀገር ብለው ቢሰሙት የማይሆንበት ምን ምክንያት አለ? 

አቤት !አቤት በሉን አቤት ስሙን ፣
መልክት አለን እዚህ ቤት ፣
አቤት በሉኝ አቤት መልክት አለኝ እዚህ ቤት። 
አቤት በሉን አቤት መልክት አለን እኛ ስለኛ።
----------እንዳንለያይ እንዳንለያይ አደራ።

እንውጣ ነቃ ብለን፣

እናስብ እንችላለን።

የናቁት አንድቀን ያደርጋል እራቁት፣

ንገሩት ለእዛ ሰው ምከሩና አንቁት።

ያክብረኝ ላክብረው መናናቁም ይቅር፣

መቸም የትም ቢሆን ያሸንፋል ፍቅር።

ለምን ልጣት ለምን ትዘን፣

ሆናኝ ጎኔ ለኔ በዚች አለም፣

የኛ ፡ የሁላችንም ድምጽ (ኢትዮ ገርልስ ግሩፕ እና ሃይሌ ሩት)

አጥታ ሰው ከጎኗ አቅሟም አንሷት፣

ላያት አልፈልግም ከፍቷት ብሷት፣

እንግዲህ ቻልኝ እሷን ልደግፋት፣

እንዳላየሁ ሆኘ ስንቴ አለፍኳት፣

ግን አሁን ይብቃኝ ልቁም ጎኗ፣

አለም ካለርሷ ሙሉ አትሆንምና።

ለምን ልጣት ለምን ትዘን፣

ሆናኝ ጎኔ ለኔ በዚች አለም።

ተነስተናል ቆርጠናል፣

ይሄው መጥተናል ።

ይበቃናል የድሮ፣ 

ተነስተናል ዘንድሮ። 
ተነስተናል ድሮ ተንቀናል፣

ባሳለፍነው ሰዎች ከፍቶናል 

ተነስተናል ዛሬ ቆርጠናል፣

ፍቅር ጥበብ ተስፋን ይዘናል፣

ተደፍረናል ድሮ ተንቀናል፣

ባሳለፍነው ሰዎች ከፍቶናል


1 comment:

Anonymous said...

Gitum girum etsub etsub new wendimschin.

የክፍለዘመናችን የኢትዮጵያ የስልጣኔ ማማ መለኪያ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ጉባዔ ነገ በአዲስ አበባ ይከፈታል። ህልውናችን፣መጪው ስልጣኔያችን፣ሰላማችን እና ዕድገታችን በእዚህ ጉባዔ ውጤትና ሒደት ይወሰናል።

Foto : Fana digital  የቻልን በሀሳብ እና በጸሎት፣ ያልገባን እና የተምታታብን ደግሞ እኪገባን በዝምታ በመቆየት ኢትዮጵያን እናግዛት። ========= ጉዳያችን ልዩ ========= ኢትዮጵያ ሐምሌ 8፣2018 ዓም...