ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Wednesday, March 21, 2018

ማኅበረ ቅዱሳን በዋልድባ ጉዳይ ዝም ብሎ አያውቅም።ለመጀመርያ ጊዜ በጥናት በተደገፈ ማስረጃ መንግስት እጁን እንዲያነሳ የጠየቀም ማኅበረ ቅዱሳን ነው።

የማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማዕከል ጽህፈት ቤት 

ከእዚህ በታች ያለው ፅሁፍ በአብርሃም ሲሳይ የቀረበ ፅሁፍ ነው።
+++++++++++++++
ማኅበረ ቅዱሳን በዋልድባ አባቶች ጉዳይ የት ነው ያለው? የሚል ነገር ፤ እዚህም እዛም እየተነሳ አየሁ። በርግጥ ማኅበሩ በዋልድባ ጉዳይ ዝም ብሏል?ለጉዳዩ ቀረብ ያላችሁ የገዳሙ ጉዳይ መዘዝ ምን እንዳመጣ ታቁታላችሁ። ለሌሎቻችሁ በአጭሩ ለመግለጽ ያክል 

ዋልድባ፤ በምሥራቅ ጎንደር እና በምዕራብ ትግራይ መካከል የሚገኝ ታላቅ ገዳም ነው። ምሥረታው በ485 ዓ. ም. ገደማ እንደሆነ የሚነገርለት ይህ ገዳም ጥንታዊ እና ታሪካዊ ሀገራዊ ቅርሶችን እንዲሁም ከ3000 በላይ መናንያንን የያዘ ገዳም እንደሆነ ይነገርለታል። ከምስራቅ ወደ ምዕራብ ከ፴ እስከ ፵ ኪሎሜትር ርቀት ስኖረው ከሰሜን ወደ ደቡብ ከ፹—፺ ኪሎ ሜትር ስፋት ነበረው፡፡ ገዳሙ ዙሪያውን በአራት አፍላጋት(ወንዞች) በምስራቅ የእንስያ፣በምእራብ የዛሬማ፣በደቡብ የማይወባ፣በሰሜን የተከዜ ወንዞች አጥር ቅጥር ሆነው ገዳሙን ይከልሉት ነበር። አዎ ነበር፡፡
...
ለሺህ ዓመታት ተከብሮ የኖረው ገዳም ዙሪያውን ከብበው አጥር ቅጥር ሆነው የነበሩት ወንዞች ላይ መሰረት ያደረግ ለስኳር ማምረቻ የሚሆን የሸንኮራ ልማት በገዳሙ ክፍል ላይ እንገነባለን ሲባል ነው ጉዳዩ የሚጀምረው። ቀደም ብሎ በዋልድባ ገዳም በማኅበረ ቤተ-ሚናስ እና ቤተ-ጣዕመ መካከል ቅራኔ ነበር ፤ በገዳሙ ታላላቅ አባቶች ቅራኔዎቹ ሊፈቱ ካለመቻላቸውም ባሻገር አገልግሎታቸው እንኳን በየተራ እስኪሆን ድረስ የደረሰ ትልቅ ልዩነት ሆኖ መቆየቱ ይታወሳል፥ ለዓመታት ጉዳዩ ከወረዳ ቤተክህነት አንስቶ ፣ እስከ ቅዱስ ሲኖዶስ የደረሰ ቢሆንም፤ አባቶች ጉዳዩን ከማስታረቅ ከመፍታት ይልቅ ለቤተ መንግሥቱ መንገድ በመክፈት፤ ገዳሙ እንዲደፈር አድርገዋል።
..,
መንግስት በ2004 ዓ.ም በገዳሙ ክልል እና ዙሪያ የፓርክ ይዞታ ለመከለል እና የስኳር ፋብሪካ ለማቋቋም እንቅስቃሴ ሲጀምር በገዳሙ የነበሩ አባቶችተቃውሟቸውን ማሰማት ጀመሩ። በዚህም አባቶት ያን ጊዜ ለነበሩት ፓትሪያሪክ አቡነ ጳውሎስ፣ ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽህፈትቤት፣ ለትግራይ እና ለአማራ ክልል ፣ እንዲሁም ለጠቅላይ ሚንስትሩ ደብዳቤ በተደጋጋሚ አስገብተዋል።
የገዳሙ አባቶች ከደብዳቤ ባለፈ ፓትሪያሪኩንና ፤ ጠቅላይ ምንስቲሩን በአካል ሄደው የሚያናግሩ አባቶችን በመምረጥ ወደ አዲስ አበባ እንዲሄዱ አደረገ። ያን ጊዜ ከገዳሙተወክለው ጠቅላይ ምንስትር መለስ ዜናዊን ሊያናግሩ የመጡት አባቶች ናቸው ዛሬ በማሰቃያ ወህኒቤት ያሉት።
...
ማኀበረ ቅዱሳን በገዳሙ ክልል ውስጥ በጊዜው ሊሰራ የታሰበውን ፕሮጀክት በቦታው ተገኝቶ ግድቡ ገዳሙ ላይ ሊያደርስ የሚችለውን አደጋ ለመጀመሪያ ጊዜ በጥናት አስደግፎ ለህዝብ አቅርቦ እንደነበር ይታወሳል። ማኀበሩ ጥናታዊ ጽሁፍ ከማቅረብ ባሻገር በይፋ መንግስት እጁን ከደሙ ላይ እንዲያነሳ በተደጋጋሚ ጠይቋል፡ ጉዳዩ በቤተ ክህነት ሰዎ ችና በምንግስቱ ባለስልጣናት የዘር መልክ እንዲይዝ ተደረገ እንጂ።
ሪፖርቱ በአጭሩ
ሀ. ግድቡ 16.6 ሔክታር ከገዳሙ ቅዱስ ቦታ ገብቶ እንደሚያርፍ፤
ለ. አጽመ ቅዱሳን መነሳቱን አረጋግጦልናል
ሐ. 500 ሜትር ስፋት ያህል ያለው መንገድ በገዳሙ ውስጥመቀደዱን
መ. አብያተክርስትያናት እንደሚፈርሱ
ሠ.ገዳሙ የእርሻ መሬቱን እንደሚያጣ
እና ሌሎች ጉዳዮችን በመጀመሪያ ጥናቱ ለህዝብም ለመንግስትም ያቀረበ ሲሆን፡። ያንን ተከትሎ በገዳሙ ሆናችሁ መረጃ ታቀብላላችሁ በማለት መነኮሳቱ በሱባዔ ላይ እያሉ ተደበደቡ ከገዳሙ ተሰደዱ። ለአቤቱታና ጠቅላይ ምንስትሩን ለማናገር አዲስ አበባ የመጡት መነኮሳት ከዛንጊዜ አንስቶ ሲሳደዱ ቆዩ።ማኅበሩንም ቀደም ብሎ ከተጀመረው ከአልቃይዳና ከአልሰለፊያ ጋር የማመሳሰሉንና የመምታቱን አላማ የዋልድባ ጥናት ሪፖርት ለመንግስት እንደምክንያት በመጠቀም ማህበሩን ለማፈራረስ እንደ አቅማቸው ሞከራ ጀመሩ። ላይጨርሱ ጀመሩ እንጂ። በዋልድባ አባቶች ሃዘንና ለቅሶ ሁለቱም ተከታትለው ተወሰዱ።
...
ሳጠቃልል፡ ማኅበረ ቅዱሳን ላለፉት ስድስት ዓመታት በዋልድባ ጉዳይ ዝም አላለም!ምን አልባት ለብዙዎ ቻችን አባቶቹ በወህኒ ቤት ምን እየደረሰባቸው እንዳለ በዚህ ወር ይሆናል ያወቅነው ፡ ድምጽ አሰማን ብለን የምናስበውም የFacebook Profile ሰለቀየርን ይሆናል፡ ማህበሩ እንደ ማህበርም ይሁን እንደ አባላት(በግል)አባቶቻችን ለአቤቱታ ከመጡበት እለት አንስቶ(ምን አልባትም ስለጉዳዩ በማንቃትና፡ መንገድ በማሳየት በኋላም ጉዳያቸውን በመከታተል) የሚያውቃቸውም ሆነ የሚገባውን ሲያደርገ የነበረ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል።











ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

No comments:

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።