ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Wednesday, February 7, 2018

የዘመነ አክሱም ስልጣኔ ቅርሶች የማን ናቸው?


በቀሲስ መንግሥቱ ጐበዜ
ሉንድ ዩንቨርሲቲ ፣ ስዊድን
(ቀሲስ መንግስቱ ጎበዜ በአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ አርኪኦሎጂ እና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር እና በሉንድ ዩንቨርስቲ የዶክትሬት የመጨረሻ ዓመት ትምህርታቸውን በታሪክ ዘመን አርክዮሎጂ በማጥናት ላይ ይገኛሉ)
የአክሱም ሐውልት
አክሱም የጥንታዊ ኢትዮጵያ ስልጣኔ እምብርት፣ የጠንካራ መንግሥታዊ አስተዳደር ማዕከል እና የድንቅ ባህል መድረክ እንደነበረች ይታወቃል የታቦተ ጽዮን መገኛ የቅዱስ ያሬድ መፍለቂያ የመጀመሪያው ጳጳስ አባ ሰላማ (ፍሬምናጦስ) መንበር የዘጠኙ ቅዱሳን በዓት የነበረችው አክሱም በኢትዮጵያ የክርስትና ሐይማኖት ታሪክ ልዩ ክብርና ስፍራ አላት አክሱም የመጀመሪያዎቹ ሙሃመድ ተከታዮች ከሃገራቸው በተሰደዱ ጊዜ በእንግድነት ተቀብላ መጠጊያ ስለሆነች በሙስሊሙ ዓለምም ውለታዋ የሚዘነጋ አይደለም

የአክሱም መንግሥት በትንሹ ከመጀመርያው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ መኖሩ ሲታወቅጠንካራ መሪዎችና የራሱ የሆነ የመገባበያ ገንዘብ እንደነበረውም ይታወሳልበዚሁ በመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን ዞስካለስ በመባል የሚታወቀው ንጉሥ የግሪክኛ ቋንቋን በደንብ የሚያውቅና የአዶሊስ ወደብን በዋና የንግድ ማዕከልነት ይጠቀም እንደነበር ተመዝግቧል። የአክሱም መንግሥት ያልነት 2ኛው እስከ 3ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በነበረው የአዶሊስ ሐውልት ጽሑፍ (Adulis Inscription) ላይ ተጠቅሷልበ3ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረ ማኒ የተባለ ፐርሺያዊ ጸሐፊ አክሱምን ከሮምከፐርሺያና ከቻይና ጋር በመደ በዘመኑ ከነበሩት የዓለም ሃያላን መንግሥታት ተርታ አስቀምጧታል4ኛው እስከ 6ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ለነበረው ከፍተኛ የሆነ የአክሱም መንግሥት እድገትና ብልጽግና ከበቂ በላይ የታሪክ ምስክሮች ይገኛሉየ4ኛው መቶ ክፍለ ዘመኑ ንጉ ኢዛና እና የ6ኛው መቶ ክፍለ ዘመኑ ንጉ ካሌብ በቤተመንግሥትም ሆነ በቤተክህነቱ ታሪክ ጉልህ ስፍራ ያላቸው ናቸው

የአክሱም ስልጣኔ አንድአንዶች እንደሚመስላቸው አንድን ህብረተሰብ ብቻ የሚወክል ሳይሆን የብዙ ኢትዮጵያውያን አሻራ ያረፈበት የድምር እንቅስቃሲያቸው ውጤት ነው። ለምሳሌ ያህል አክሱም የሚለውን መሰረተ ሥርወ ቃል (etymology) መመልከት ተገቢ ይሆናል አክሱም ለው ቃል አኽ ከሚለው የአገውኛ ቃል (ትርጉሙ ውሃ ማለት ነው) እና ስዩም ከሚለው የግዕዝ ቃል (የተሾመ ሹም እንደ ማለት ነው) የተገኘ ሆን እንደሚችል ከፍተኛ ግምት አለ በአንድ ላይ ተጠቃሎ ሲነበብም የው ሹም የሚለውን ትርጉም ይሰጣል እስከ ዛሬ ድረስ በአክሱም ማይ ሹም (የውሃ ሹም) ተብሎ የሚታወቅ ቦታ መኖሩ የስያሜውን እውነትነት ያጠናክረዋል ለረጅም ዘመን የዋግ (ሰቆጣ) መሪ ዋግ ሹም በሚል ማዕረግ ስም ይጠሩ እንደነበርም ይታወቃል ከላስታ ነገሥታት መካከልም ሁለቱ ግርማ ስዩም (የንጉሥ ይምርሃነ ክርስቶስ አባት) እና ዛን ስዩም (የንጉስ ላሊበላ አባት) ተብለው ይጠሩ እንደነበር ልብ ይሏል አክሱም የሚለው ቃል ስያሜ መሰረቱ የኩሽ (አገውኛ) እና የሴም (ግዕዝ) ቋንቋዎች ጥምረት ከሆነ የአክሱም መንግሥት ሥልጣኔ እና ቅርሶቹ የኩሽና የሴም ሕዝቦች መስተጋብር ውጤት መሆናቸውን ከዚህ በላይ ማሳያ የለም

ሆኖም ግን የታሪክና የአርኪኦሎጂ ማስረጃዎች እንደሚመሰክሩት የአገው ሕዝቦች በአክሱም ዘመነ መንግሥት አስተዳደርና እና የስልጣኔ ፈርጦቹ የነበራቸውን ከሁሉም የላቀ አስተዋጽኦ መካድ አይቻልምከጅምሩ አገዎች በቁጥር ብዙና መልካዓ ምድራዊ አሰፋፈራቸውም ቀላል የማይባለውን የአክሱም መንግሥት ወሰነ ግዛት ያካተተ ነበርአገዎች የመካከለኛውና የሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ቀደምት ነዋሪዎችና አገር አቅኝዎች መሆናቸው ይታወቃል እነዚህ ሕዝቦች የአባይ ወንዝ መነሻ ከሆነው ከጣና ጀምሮ የጎጃም፣የጎንደር፣ የላስታ፣የዋግ (ሰአቆጣ) እና የትግራይ በርካታ አካባቢዎችን በማካተት የመረብን ወንዝ ተሻግረው እስከ ኤርትራ ግዛት ከረን ድረስ ሰፍረው ይኖሩ ነበር ይህ ትልቅ የሕዝብ ቁጥርና ሰፊ የቦታ ይዞታ በራሱ አገዎች በዘመነ አክሱም ተጽእኖ የመፍጠር አቅም እንደነበራቸው አመላካች ነው።

አገዎች ዓይነተኛ በሆኑ ጥንታዊ የታሪክ መዛግብት (primary sources) ከተጠቀሱት ጥቂት ሕዝቦች መካከል አንዱ ናቸውከላይ በተጠቀሰው የአዶሊስ የሃውልት ላይ ጽሑፍ (Adulis Inscription)የ4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የንጉሥ ኢዛና የድንጋይ ላይ ጽሑፍ (Ezana Inscription)እንዲሁም በ6ኛውመቶ ክፍለ ዘመን የኮስሞስ ጽሑፍ (Christian Topography of Cosmas Indicopleustes) የአገዎችን እንጅ በዘመናችን የሚታወቁ የሌሎች ሕዝቦችን ስም አናገኝምከአገው ሌላ አጋዚ የሚለው ስም በጥንቱ መዛግብት የተገለጸ ሲሆን ይኸውም የግዕዝ ቋንቋ ተናጋሪ ሕዝቦችን (አጋዝያን) የሚመለከት እንደሆነ ብዙዎች ይስማሙበታልበአዶሊስ ሐውልት ጽሑፍ (Adulis Inscription) ላይ የአክሱም ንጉስ ከአጋዚ ነገ ጋር እንደተዋጋ ተጥቅሷልበሌላ በኩል ከአክሱም መንግሥት ሥልጣኔ ጋር የቅርብ ዝምድና ሊኖራቸው ይችላል ተብለው የሚታሰቡት ሕዝቦች ስማቸው በጥንቱ የአክሱም ዘመን የታሪክ ሰነዶች አልተካተተምለምሳሌ የትግራይ ሕዝብ ለመጀመሪያ ጊዜ በጽሑፍ ተጠቅሶ የሚገኘው በ10ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከአክሱም መንግሥት ማክተም በኋላ ነው።

አገዎች በአክሱም መንግሥት የባህልየምጣኔ ሀብትና የፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ ጉልህ ድርሻ እንደነበራቸው የሚጠቁሙ አያሌ ማሳያዎች አሉ ከነዚህም አንዱ አገዎች በአክሱም መንግሥት በከፍተኛ የአስዳደር ኃላፊነት ያገለግሉ እንደነበር የሚያስረዳው የኮስሞስ ጽሑፍ ነው በዚህ የታሪክ ሰነድ ላይ እንደተገለጸው በንጉሥ ካሌብ ዘመነ መንግሥት ከፍተኛ ኃላፊነትና እምነት የሚጠይቀውን ረጅም የወርቅ ንግድ መተላለፊያ መስመር የሚቆጣጠረው የአገው ሰው ነበር በተለይ ደግሞ ለአክሱም ስልጣኔ መዳበር አገዎች የነበራቸውን ጉልህ ሚና የምንረዳው የራሳቸውን መንግሥት ላስታ ላይ ከመሰረቱ በኋላ የአክሱምን ሥልጣኔ አሻሽለው መድገማቸው ነው። የመንግሥት ማዕከሉ ከአክሱም ወደ ላስታ ከመሸጋገሩ ውጭ በሁለቱ ዘመናት የነበረው የአስተዳደር ዘይቤየባህልየቋንቋየውጭ ግንኙነት ወዘተ የጎላ ልዩነት ነበረው ብሎ ለመናገር አያስደፍርምበአክሱምም በዛጉዬም ዘመናት ግዕዝን በዋና ቋንቋነት ይጠቀሙ ነበርበአክሱምም በዛጉዬም ዘመናት ቤተ መንግሥትና ቤተክህነት እጅግ ጠበቀ ግንኙነት ነበራቸውበርግጥ በዛግዬ ዘመን ነገሥታት ካህናትም ተፈጥረዋል። የአክሱም ነገሥታት በተለይ ከግብፅና ከኢየሩሳሌም ጋር የነበራቸው ግንኙነት በዛጉዬ ዘመንም ተጠናክሮ ቀጥሏል። የአክሱም ዘመን የህንፃ አሰራር ጥበብ በዳበረ መልኩ በዛጉዬ ዘመን ተንፀርቋል

አገዎች የአክሱም መንግሥት አካል ስለነበሩ ድሮም የሚያውቁትን የኪነ ህንፃን ሥራ በረቀቀ መንገድ በላስታ ላይ አሳይተዋል በተለይ ደግሞ የቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ እና የቅዱስ ላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትን ስንመለከት ከአክሱም ዘምን የህንፃ ጥበብ ጋር ያላቸው የቅርብ ዝምድና ሁለቱም ከአንድ ምንጭ የተቀዱ መሆናቸውን መረዳት አያዳግትም ወጥ ለትን በመፈልፈል ለሚፈልጉት ላማ ማዋልን መሰረት ያደረገው ኢትዮጵያዊ ሥልጣኔ በአንድም ይሁን በሌላ መንገድ ከአገው ሕዝቦች ጋር የተዛመደ ስለመሆኑ ዋነኛ አመላካች ነው መርዶክ የተባለው ጸሐፊ ሁሉም ማስረጃዎች የሚጠቁሙት የአገው ሕዝብ በአፍሪካ በባህላዊ የፈጠራ ክህሎቶች የተካ መሆኑን ነው በማለት የገለጸው ከዚህ ተነስቶ ሳይሆን አይቀርም

ሲጠቃለል የአክሱም ዘመን ስልጣኔ ውጤት የሆኑ መንፈሳዊና ባህላዊ ቅርሶችን የራሱ ብቻ እንደሆኑ አድርጎ የሚያስብ የህብረተሰብ ክፍል ቢኖር ታሪካዊ እውነታው አይፈቅድለትም ያም ከሆነ ከአገው ሕዝብ በላይ የቀረበ ማንም እንደሌለ የሚመሰክሩ ከበቂ በላይ ማስረጃዎች አሉ። አገዎችም ቢሆኑ በጊዜ ብዛት በተለይ በአማርኛበትግርኛ እና በኋላም ላይ በኦሮምኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች የተዋ (assimilated) ወይም ከነዚህ ሕዝቦች ጋር የተቀየጡ (mixed) በመሆናቸው ብዙውን የጥንቱን የአገው ማኅበረሰብ የምናገኘው በነዚህ ሕዝቦች ውስጥ ጭምር መሆኑ መዘንጋት የለበትም ደግሞስ አክሱም የሚለው ስያሜ ራሱ ከላይ እንደተመለከትነው በኩሽና በሴም ቋንቋዎች ጥምረት የተፈጠረ ቃል አይደል! ስለሆነም የጥንቱ የአክሱም ዘመን ስልጣኔ ቅርሶች የሁላችንም ቅድመ አያቶች ድንቅ የእምነት የስራና የፈጠራ ቶች መሆናቸው ማስተባበል አይቻልም አክሱማዊ ቅርሶቻችን ሁሉም ኢትዮጵያውያን አባቶቻችንና እናቶቻችን ሰርተውና ጠብቀው ያቆዩልን የጋራ ሀብቶቻችን ናቸው ከዚህም በላይ የአክሱም መካነ ቅርስ በአሁኑ ጊዜ ለም ቅርስነት ተመዝግቦ የሚገኝ የዓለም ሕዝብ ሁሉ ሀብት መሆኑ ማወቁ ተገቢ ነው

ማጣቀሻዎች
McCrindle, John Watson (ed.,tr), 1897. The Christian Topography of Cosmas, an Egyptian monk, London.

Merid Wolde Aregay, 1971. ‘Southern Ethiopia and the Christian Kingdom 1508-1708’. Unpublished PhD thesis, School of Oriental and African Studies, University of London.

Munro-Hay, S. 1991. Aksum. An African Civilisation of Late Antiquity. Edinburgh University Press, Edinburgh.

Munro-Hay, Stuart. 2003. Aksum, Encyclopaedia Aethiopica, I, Siegbert Uhlig, ed., Wiesbaden

Murdock, George P., 1959. Africa: Its people and their culture history, New York

Phillipson, D.W. 2009. Ancient Churches of Ethiopia, Fourth–Fourteenth Centuries. Yale University Press: New Haven/London.

Phillipson, D.W. 2004. The Aksumite roots of medieval Ethiopia. Azania 29: 77-89.

Quirin, James. 2003. Agäw, Encyclopaedia Aethiopica, I, Siegbert Uhlig, ed., Wiesbaden

Sergew Hable Selassie. 1972. Ancient and Medieval Ethiopian History to 1270. United Printers: Addis Ababa.

Sima, Alexander. 2003. Agazi, Encyclopaedia Aethiopica, I, Siegbert Uhlig, ed., Wiesbaden

Smidt, Wolbert. 2010. Tigray, Encyclopaedia Aethiopica, I, Siegbert Uhlig, ed., Wiesbaden

Taddesse Tamrat, 1972, Church and state in Ethiopia, 1270-1527, Oxford.

Taddesse Tamrat, 1988. Process of Ethnic Interaction and Integration in Ethiopian History: the Case of the Agaw (Special Issue in Honour of Roland Oliver), the Journal of African History, 29, 1, 5-18.

No comments: