ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, January 30, 2018

የትግራይ ሕዝብ ይህ አጋጣሚ ባያልፈው ይመረጣል።የአድዋዎችን የመገንጠል እና ትግራይን ከቀረው ሕዝብ የማጋጨት ሥራ በመቃወም የሚነሳበት ጊዜ አሁን ነው (የጉዳያችን ማስታወሻ)


  • ህወሓት አሁን ለእርድ ያቀረበው የትግራይን ሕዝብ ነው
  • ህወሓት በእጁ የቀረው የትግራይ ሕዝብ ስለሆነ ከእጁ እንዳያፈተልክበት ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ገብቷል።
ህወሓት ሙሉ የስልጣን ዘመኑን ያሳለፈው ሕዝብ ከህዝብ ሲያጋጭ ነው።የምናውቀውን ኦሮምኛ ተናጋሪውን ኦነግ፣አማርኛ ተናጋሪውን ግንቦት 7፣ሱማልኛ ተናጋሪውን የኦጋዴን ገንጣይ እና የአልሸባብ ተላላኪ እያለ በጅምላ ሕዝብ እየፈረጀ እርስ በርስ ስንፈራራ እንድንኖር አድርጎናል።ለስልጣኑ ሲል ለእርድ የማያቀርበው ሕዝብ በህወሓት ዘንድ የለም።ህወሓት አሁን ለእርድ ያቀረበው የትግራይን ሕዝብ ነው።
አንዳንዶች ህወሓት ከትግራይ ስለተነሳ ለትግራይ ሕዝብ የሚጨነቅ አድርገው የሚያስቡ አሉ።ህወሓት የትግራይን ሕዝብ የምፈልገው ለስልጣን መንጠላጠያ ብቻ ነው።

የተቀሩትን የኢትዮጵያ ክፍሎች ለማናከስ በተለይ በኦሮሞ እና አማራ መካከል ያለው ግጭት አልፈጠር ሲል ህወሓት በእጁ የቀረው የትግራይ ሕዝብ ስለሆነ እርሱ እንዳያፈተልክበት ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ገብቷል። ይህንንም ስላወቀ ሕዝቡን በስጋት ውስጥ ከትቶ የፋሺሽታዊ ስራው ሙሉ በሙሉ ተባባሪ እንዲሆን እና እንዳያፈነግጥ ወጥሮ ይዞታል። ለእዚህ ማስረጃው ህወሓት በመጀመርያ የትግራይን ሕዝብ ከጎንደር ሕዝብ ጋር አጣላው በመቀጠል ከወሎ ሕዝብ ጋር ግጭት እንዲፈጠር አደረገ። አንዳንዶች ይህ ተግባር ለትግራይ ታስቦ የተደረገ ቢመስላቸው መጃጃላቸውን ከመግለፅ ሌላ ምንም ማለት አይቻልም። ሕዝቡን የሚወድ ድርጅት በተቻለ መጠን የሚወደው ሕዝብ ከሌሎች ጋር እንዳይጣላ የቻለውን ሁሉ ያደርጋል እንጂ እንዴት ለወልቃይት ችግር ክላሽ እናቶች አሮጊቶችን እያስያዘ ያስዝታል? ሕዝቡን የሚወድ ድርጅት እንዴት በወልዲያ ጫወታ ላይ ቀድሞ ካረዎቹን ልኮ በአደባባይ እየተፉ የሚዝቱ ጠብ ጫሪዎች  እንደ መንገድ ጠራጊ ነቢይ ቀድሞ ልኮ እሳት ይለኩሳል? ሕዝቡን የሚወድ ድርጅት እንዴት ሕዝቡን እንደ ግል እቃው ቆጥሮ ስለመገንጠል ያዜምለታል።
ሎሚ ፅባ በሶፍያ አፅብሃ (በኢትዮጵያ አንድነት የሚያምነው የኢትዮጵያ ጦር ሰራዊትን ግንባር ድረስ ሄደው በ1970ዎቹ እና 80ዎቹ ላይ ያነቃቃ የነበረው የሙዚቃ ሉዑክ )
አሁን የትግራይ ሕዝብ በአድዋ ስብስብ አማካይነት የደረሰበትን ፍጥጫ እና ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር የገባውን መቃቃር የሚያደበዝዝ መልካም አጋጣሚ ህወሃቶችን የመገንጠል አጀንዳ በማንሳታቸው ምክንያት አትወክሉንም ብሎ መነሳት ካለበት ወቅቱ አሁን ነው።ሕዝብ ለዘላለም ይኖራል ድርጅቶች ግን በእየዘመኑ ተለዋዋጭ ናቸው።የትግራይ ህዝብም መመልከት ያለበት ይህንን የው።አሁን ምንም አይነት ቅሌን ጨርቄን የሚያስብለው ጉዳይ የትግራይ ሕዝብ በህወሓት ላይ መነሳት እና ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር መስመሩን ማስተካከል የቀረበለት መልካም ዕድል ነው። እድሉን መጠቀም ብልህነት ነው።ህወሓት እኛን አይወክልም።መገንጠል የሚል አጀንዳ የትግራይ ሕዝብ አይደለም! የጥቂት ህወሃቶች እብደት ነው! ብሎ ድምፅን ማሰማት የብዙ በሽታ መፈወሻ ነው።


ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

No comments:

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።