ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, December 29, 2017

ኢትዮጵያ ከሥርዓት ለውጥ በኃላም ከእራሷ ጋር የታረቀች፣ ከሕዝቡ ባህል እና ስነ ልቦና ጋር የሚሄድ የችግር አፈታት መከተል እንዳለባት የሚያሳይ ልዩ ጥናታዊ ዝግጅት - ሽምግልና እና እርቅ በኢትዮጵያ (ኦድዮ)

  • ከእዚህ በፊት ፈፅሞ ሰምተዋቸው የማያውቋቸው በርካታ የሀገራችን ታሪኮች የተካተቱበት ልዩ  የድምፅ ዝግጅት 
የልዩ ጥናታዊ ዝግጅቱ አቅራቢ = ሸገር ኤፍ ኤም ስንክሳር ፕሮግራም 

ኢትዮጵያ በመንግስት ስርዓት ስትኖር የሃያ ስድስት አመታት እድሜ ያስቆጠረች አይደለችም።ከሶስት ሺህ አመታት በላይ በመንግስት ስርዓት ታቅፋ በየዘመኑ የሚገጥሟትን ፈተናዎች እያለፈች የሄደችበት ምስጢር ከባዕድ ምድር የተፈበረከ ርዕዮት ዓለም በመጠቀም አይደለም።ይልቁንም በሕዝቧ ባህል፣ስነ ልቦና፣መልካም ግንኙነት እና እምነት ሁሉ ጋር በተናበበ መልክ መሪዎቿ ከእያንዳንዱ ግለሰብ እስከ ሹማምንቶቿ ድረስ ያሉትን ችግሮች የሚፈቱባቸው ሃገራዊ የሆኑ ዘዴዎችን በመጠቀማቸው ነበር። የሸገር ራድዮ በያዝነው ታህሳስ/2010 ዓም ስንክሳር በተሰኘ ሳምንታዊ መርሃ ግብሩ 'ሽምግልና እና እርቅ በኢትዮጵያ'' በሚል ርዕስ ተከታታይ መርሃ ግብሮችን አስደምጧል።ኢትዮጵያ እንዴት እንደኖረች እና እንዴት መኖር እንዳለባት ይህ መርሃ ግብር ያመላክታል። ዝግጅቶቹን እስከመጨረሻ ቢያዳምጡ ይጠቀማሉ።

ሽምግልና እና እርቅ በኢትዮጵያ ክፍል አንድ 

ሽምግልና እና እርቅ በኢትዮጵያ ክፍል ሁለት 

ሽምግልና እና እርቅ በኢትዮጵያ ክፍል ሶስት 

ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

No comments: