ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, September 5, 2017

የጎንደርን ሕዝብ እርስ በርስ ለማፋጀት መቀሌ ላይ ልዩ ቢሮ ተከፍቷል።በህወሓት መስከረም 7/2010 ዓም ቅማንት እና ዐማራ እንዲለያይ የሚያስገድድ አስገዳጅ የሕዝብ ድምፅ እንዲሰጥ ቀጠሮ ተይዟል።

ቅማንት እና ዐማራ በሚል እንዲለያዩ  ህወሓት የፈረደበት አዲስ  ትውልድ በጎንደር ተራሮች ላይ 

ጉዳያችን/ Gudayachn
ነሐሴ 30/2009 ዓም (ሴፕቴምበር 5/2017)
  • መቀሌ ላይ ለቅማንት ቢሮ ከፍቶ (እንደ ጠላት ሀገር የነፃነት ቢሮ መሰል አደረጃጀት አደራጅቶ) ዐማራ ጠላታችሁ ነው የሚል ስብከት እያደረገ መሆኑ ተሰምቷል።
  • መስከረም 7/2010 ዓም የቅማንት ሕዝብን ለመለየት በምርጫ ቦርድ አስተባባሪነት ይፈፀማል የተባለው እና መቀሌ ላይ የተቀናበረው የድምፅ መስጠት ጉዳይ በኢትዮጵያ አዲስ የበቀል ምዕራፍ እንደሚከፍት ማወቅ ይገባል።
  • በተለይ ከወደ መቀሌ ሰፈር ያላችሁ ሽማግሌዎች እና ታዋቂ ግለሰቦች እንዲሁም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ  ይህንን በሕዝብ  መካከል የፋሺሽታዊ ሥራ የሚሰሩትን ቢያንስ በዝምታ በማበረታታችሁ ወቅቱን ጠብቆ የመከራው ፅዋ በእራሳችሁ እና በልጆቻችሁ በኩል እንደሚደርሳችሁ ልታውቁት የገባል።
  • መቀመጫውን መቀሌ አድርጎ የዐማራ እና የቅማንት ህዝብን ለመለያየት ከተነደፈው መርሃ ግብር ውስጥ ከመስከረም 7 በኃላ የዐማራ ተወላጅ ያሏቸውን ንብረት ገፎ  ከመሬታቸው መንቀል ይገባል የሚል እቅድ ተይዟል።


ኢትዮጵያ በረጅሙ የመንግስት ስሪት ታሪክ እንደ ህወሓት ሙሉ ጊዜውን፣ሃብቱን እና የሰው ኃይሉን ሕዝቧን ለመከፋፈል እና እርስ በርስ ለማጫረስ እጅግ አረመኔያዊ ተግባር የሰራ መንግስት የለም።የቀደሙት ነገስታት በስልጣን ዘመናቸውም ሆነ ስልጣን ለመያዝ በሚያደርጉት የእርስ በርስ ጦርነት በሕዝብ መካከል ጠብ ለመዝራት እና በውጤቱ ለመጠቀም ከመጣር ይልቅ በኃይል እና በጉልበት ማስገበር ላይ ያተኮረ የስልጣን ትግል ሲያደርጉ ብቻ ይታወቃሉ።ህወሓት ግን ኢትዮጵያን ጣልያን በአምስቱ ዓመታት እንደከፋፈለው የጎሳ ክልል ኢትዮጵያውያንን በጎሳ መልከዓ ምድር እና የመታወቂያ ወረቀታቸው ላይ ሳይቀር የጎሳ ስም እየፃፉ እጅግ አደገኛ የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ  ሲያራምዱ ሃያ ስድስተኛ አመታቸውን ይዘዋል።ይህም ሆኖ ግን የኢትዮጵያውያን ጠንካራ ማኅበራዊ እና ሃይማኖታዊ ትስስር አሁን እስካለንበት ሰዓት ድረስ እንደ ሀገር እንድንቀጥል አድርጎናል። ይህ ማለት ግን ማኅበራዊም ሆነ ሃይማኖታዊ እሴታችን በህወሓት መርዘኛ የጎሳ ፖለቲካ እጅጉን አልተጎሳቆለም ማለት አይደለም።

በአሁኑ ወቅት ህወሓት በሱማሌ እና በኦሮሞ መካከል፣ በቤንሻንጉል እና በዐማራ መካከል፣  በአፋር እና በዐማራ መካከል፣በሲዳማ እና በኦሮሞ መካከል እና በሌሎች በእዚህ ፅሁፍ ውስጥ ባልተካተቱ ኢትዮጵያውያን መካከል ሆን ተብሎ የተጠና ግጭት በመፍጠር የስልጣን ዘመኑን ለማራዘም ሲሞክር ተስተውሏል።የእዚህ ፅሁፍ አቅራቢም በቦረና ጉጂ እና ኦሮሞ መካከል ህወሓት እንዴት ግጭት እንደፈጠረ በወቅቱ የተግባሩ ፈፃሚ የነበረ ግለሰብ አንደበት የሰማውን ታሪክ ያስታውሳል እና ሕዝብ የማጋጨት ለህወሓት የተካነበት የሙሉ ጊዜ ስራው እንደሆነ የሚነገረው አንዳች ስህተት እንደሌለበት ለመግለፅ በእማኝነት ለመግለጥ ይወዳል።

ህወሓት በኢትዮጵያውያን መካከል የሚፈጥራቸው የግጭት አይነቶች በመልክዐ ምድር እና ቋንቋ የሚለያዩትን ብቻ ሳይሆን ተመሳሳይ ቋንቋ፣ባህል እና ሃይማኖት ያላቸው እንደ ቅማንት እና ዐማራ ያሉ ለዘመናት አብረው የኖሩ እና ልዩነታቸውን እራሳቸውም የማያውቁትን ሕዝብ ሁሉ ለመለያየት  እና የእልቂት ደም ለማፍሰስ ተዘጋጅቷል።ለእዚህም በመጪው መስከረም 7/2010 ዓም ቅማንት ከዐማራ የተለየ ዞን እንዲከለል እና በውጤቱም የመሬት ግጭት እንዲፈጠር መቀሌ ላይ ለቅማንት ቢሮ ከፍቶ (እንደ ጠላት ሀገር የነፃነት ቢሮ መሰል አደረጃጀት አደራጅቶ) ዐማራ ጠላታችሁ ነው የሚል ስብከት እያደረገ መሆኑ ተሰምቷል።በመሰረቱ የዐማራ እና የቅማንት ሕዝብ እርስ በርስ ተለያይቶ የማያውቅ እና ኢትዮጵያ በዘመናት በገጠማት የውጭ ወራሪ ሁሉ አብሮ የሞተ እርስ በርስ ልዩነት ብሎ ነገር የማያውቅ ሕዝብ ነው።በቅማንትም ሆነ በዐማራ መካከል የሚታወቀው አባባል ቅማንት ዐማራ ነው።ዐማራም ቅማንት ነው የሚል ሲሆን የዐማራ ሕዝብ በመልክዓ ምድር ጎጃሜ፣ ጎንደሬ፣ ሸዌ፣ ወሎዬ በሚል የተለምዶ አጠራር ከመታወቁም በላይ  ባደገበት አካባቢ ቅማንት፣ አገው፣ አርጎባ፤ ወይጦ፤ ቤተ እስራኤል ወዘተ በመባል ይታወቃል። ይህ ማለት ግን የተለያየ ሕዝብ አድርጎ ህወሓት ለመሳል እንደሚሞክረው አይደለም።

መስከረም 7/2010 ዓም የቅማንት ሕዝብን ለመለየት በምርጫ ቦርድ አስተባባሪነት ይፈፀማል የተባለው እና መቀሌ ላይ የተቀናበረው የድምፅ መስጠት ጉዳይ በኢትዮጵያ አዲስ የበቀል ምዕራፍ እንደሚከፍት ማወቅ ይገባል።የህወሓት አድናቂዎች አርቆ የማየት አቅም ባጠረው አዕምሮ  ይህንን የቅማንት እና ዐማራን የመለያየት ተንኮል የሚያደንቁት ህወሓት የተንኮል ምጡቅነት እያሉ ሊያደንቁት ሲዳዱ ተሰምተዋል።ይህ ነገ የምፀፀቱበት የአስተሳሰብ ድህነት መገለጫ ነው።ቅማንት እና ዐማራ በርካታ በማኅበራዊ እና ሃይማኖታዊ ትስስር ብቻ ሳይሆን በእዚህ ፅሁፍ የማይገለጡ በርካታ ውስጣዊ ትስስሮች አሏቸው።እነኝህ ትስስሮች በመካከላቸው ልዩነት ፈጥረው ለመለያየት የሚሞክሩትን ሁሉ መልሰው በሕብረት የሚነሱ ቀን እንደነበልባል እሳት የሚፋጁበት ቀኖች እሩቅ አይደለም።ህወሓት በርካታ ጊዜ ስህተት ሲሰራ ኖሯል።የወልቃይት ጉዳይ ሲነሳ እናቶችን ሳይቀር ክላሽ እያስያዘ ሰልፍ እየወጣ ሲፎክር በእዚህ ፅሁፍ ፀሐፊም ሳይቀር ይህ ጉዳይ 'ጎረቤቴን ለመግደል ተዘጋጀሁ' የሚል መልዕክት ነው።ነገ እንደ እሳት የሚፋጅ ኃይል ይነሳል መዘዙን አትችሉትም የሚል ማሳሰቢያ ሲሰጥ የሰማ የህወሓት ሰው አልነበረም።አሁንም እንላለን የቅማንት እና ዐማራ ሕዝብ በመካከሉ የሚደረገውን የመለያየት ሥራ ዝም ብሎ የሚቀበል አይደለም።ለጊዜው ለኑሮ ብለው ውር ውር የሚሉ የተንኮል አስፈፃሚ የተገኙ መስለው ይሆናል።የህዝቡ መሰረት ግን ጥልቅ ነው።እንደ አሕዛብ እርስ በርሱ አይጋደልም።ለጊዜው አነስተኛ ግጭቶች ታዩ ብላችሁ ጮቤ ብትረግጡም ችግሩን ፈትቶ በጋራ ጠላቱ ላይ ይነሳል።ለዚያን ጊዜ የሚሆን በጎ ሥራ መስራት ዛሬ ነበር።ሰዓቱ ካለፈ በኃላ አልቃሽም አስለቃሽም አይገኝም። አሁንም ይህንን ጉዳይ ትክክል አይደለም የምትሉ የሀገር ሽማግሌዎች በተለይ ከወደ መቀሌ በኩል  ጉዳዩን ለመውቀስ ድፍረት ቢኖራችሁ ለእራሳችሁም ለልጆቻችሁም ውለታ እንደዋላችሁ ይቆጠራል።በቸልታ ብትተዉት እና ከእዚህ ባለፈ የሽሩድ ስራውን እያደነቃችሁ የደሙ ተካፋይ ከሆናችሁ የመከራው እሳት እጥፍ ሆኖ እንደሚመጣ ለማወቅ ሊቅ መሆን አይጠበቅም።በተለይ ከወደ መቀሌ ሰፈር ያላችሁ ሽማግሌዎች እና ታዋቂ ግለሰቦች እንዲሁም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ  ይህንን በሕዝብ  መካከል የፋሺሽታዊ ሥራ የሚሰሩትን ቢያንስ በዝምታ በማበረታታችሁ ወቅቱን ጠብቆ የመከራው ፅዋ በእራሳችሁ እና በልጆቻችሁ በኩል እንደሚደርሳችሁ ልታውቁት የገባል።


ህወሓት ሕዝብ ለሕዝብ ለማጋጨት የቅማንት እና ዐማራ ሕዝብ የተለያየ ነው የሚል ትርክት ብቻ ሳይሆን ያመጣው በቅርቡ ሊተገብረው ያሰበው የሰሜን ጎንደርን ለሶስት መክፈል የሚል ሌላ የመከፋፈል ሃሳብ ነው።ይህንን ጉዳይ የሰሜን ጎንደር ሕዝብ በእጅጉ የተቃወመው ብቻ ሳይሆን ለትውልድ የሚቆይ በደል እንደተፈፀመበት እና ምላሹም አስከፊ እንደሚሆን ነው። የህወሓት ልሳን ተደርጎ የሚወሰደው ' አይጋ ፎረም' ነሐሴ 29/2009 ዓም የሰሜን ጎንደርን ለሶስት መከፈል በገለጠበት የሰሜን ጎንደር አስተዳደር ለሶስት የመከፈሉ ጉዳይ ለምን ይህን ያህል ትኩረት ሳበ? በሚል ርዕስ በፃፈው ፅሁፉ ላይ እንዲህ የሚል አረፍተ ነገር ይነበባል - 'የክልሉ አመራር በእጅጉ ተገፍቶና ተላልጦም ጭምር በሒደት የቅማንትን ማንነት እውቅና ከመስጠት አልፎ ራሳቸውን በራሳቸው እንዲያስተዳድሩ የሚያደርግ አዋጅ እንዲያጸድቅ መገደዱ አልቀረም፣'' ይላል። ይህ ማለት ጉዳዩ በህወሓት የተቀመመ አስገዳጅ ተግባር እንጂ የህዝብ ፈቃድ አለመሆኑን የሚያሳይ ነው። ቂም፣ በቀል እና ጥላቻ ከመቶ ሚልዮን የኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር መግባት ትርፍ እና ኪሳራውን ማስላት ያልቻለው ህወሓት እና ግብረ አበሮቹ መጪውን ጊዜ በሚገባ መመልከት እንዳልቻሉ እና ተስፋ በቆረጠ ስሜት እየተንቀሳቀሱ እንደሆነ ለሁሉም ግልጥ ነው።

ባጠቃላይ በየትኛውም የዓለም ክፍል የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ይህንን ከላይ የተጠቀሱትን ሕዝብ ከሕዝብ ለማጋጨት የሚድረግ የህወሓት እኩይ ተግባሮችን  ለዓለም ለማጋለጥ እና አስገዳጅ እርምጃ በስርዓቱ ላይ በመውሰድ ከደሙ በዝምታ ላለመተባበራቸው በግልጥ ማሳየት አለባቸው። 

ከእዚህ በታች የምትመለከቱት መርሃ ግብር መቀመጫውን መቀሌ አድርጎ የዐማራ እና የቅማንት ህዝብን ለመለያየት ከተነደፈው መርሃ ግብር ውስጥ ከመስከረም 7 በኃላ የዐማራ ተወላጅ ያሏቸውን ንብረት ገፎ  ከመሬታቸው መንቀል ይገባል የሚል እቅድ ተይዟል።ይህ ማለት የጎንደር ሕዝብ ከመሬቱ እንዲነቀል ይደረጋል ማለት ነው። 'የማን ቤት ፈርሶ የማን ሊበጅ' የምትለው አባባል በትክክል ቦታዋ በእዚህ አይነቱ የፋሺሽቶች አስተሳሰብ ወቅት መሆኑ አያጠራጥርም። 



ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...