ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Thursday, March 23, 2017

ሰበር ዜና - Breaking News Ethiopia - የተባበሩት አረብ ኢምሬት አምባሳደር ትናንት መከላከያ ሚኒስቴር መስርያ ቤት ታይተዋል ድርጊቱ ያልተለመደ ነው።UAE Ambassador makes extraordinary meeting with chief of staff of Ethiopian Army



ጉዳያችን/ Gudayachn 
መጋቢት 14፣2009 ዓም (March 23,2017)
(የአማርኛ ፅሁፍ ከእንግሊዝኛው ስር ያንብቡ )

On March 22, 2017, United Arab Emirates - UAE Ambassador to Ethiopia, Gazi Abdullah Al Mahri,  makes extraordinary meeting  with chief of staff of Ethiopian Army General Samora Yenus with in Ethiopian ministry of defence premises. Even if the meeting was given a cover of " discussion on terrorism", Gudayachn can learn as many questions are arising around the meeting. First of all, the UAE Ambassador did not keep his diplomatic protocol to meet the chief of staff. Because the concerned office to arrange such meeting in Ethiopia was ministry of Foreign Affairs. Secondly, the meeting was not disclosed to other high officials in the country. Non confirmed news from Addis are reporting as there is power straggle among high military officials. In the past few days, top urgently needed corrupt officials were leaving the country legally with the assistance of corrupt immigration officials exit visa from Ethiopia. 

It is over six months, since the state of emergency was declared in Ethiopia. The declaration could not improve the security condition and uprising of the mass against the brutal TPLF government. On the other hand, It is known as TPLF army is under pressure of fighting with Patriotic Ginbot 7 and KEFAGN rebel forces in Amhara region. This week the rebel groups announced as they got significant victory over TPLF army in the North west part of the country. 
==================================
የተባበሩት አረብ ኢምሬት አምባሳደር ትናንት መከላከያ ሚኒስቴር መስርያ ቤት ታይተዋል ድርጊቱ ያልተለመደ ነው። 
===================================
ጀነራል  ሳሞራ የኑስ አዲስ አበባ የሚገኙትን የተባበሩት አረብ ኢምሬት አምባሳደርን ትናንት ፅህፈት ቤታቸው ጠርተው ማነጋገራቸውን አንድ የመካከለኛ ምስራቅ ድረ-ገፅ ገልጧል። አምባሳደር ጋዚ አብዱላህ አል ማሃሪ (Gazi Abdullah Al Mahri) ከሳሞራ የኑስ ጋር የተናጋገሩት ስለ ሽብርተኝነት የምትል ከሶስት መስመር ያልበለጠ ዜና የዘገበው ዜና ለምን አምባሳደሩ ፕሮቶኮሉን ጠብቀው በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በኩል እንዳልተነጋገሩ ያለው ነገር የለም።አምባሳደሩ ከጀነራል ሳሞራ የኑስ ጋር የተነጋገሩት መከላከያ ሚኒስቴር መስርያ ቤት ድረስ በመሄድ ነው።

አምባሳደሩ መከላከያ ሚኒስቴር መስርያ ቤት ድረስ ሄደው ከሳሞራ የኑስ ጋር መነጋገራቸው በሚስጥር እንደነበር እና መከላከያ ውስጥ ያሉ ሰዎችም አለመስማታቸው እየተሰማ ነው።ድርጊቱ ያልተለመደ ነው።ጉዳዩ በኢትዮጵያ የጦር ሰራዊቱ አመራር እና ባለስልጣናት መካከል የስልጣን ፍትግያ መጀመሩን የሚያመላክት መሆኑ እየተሰማ ነው።በሌላ በኩል ጀነራል ሳሞራ የኑስ የጠቅላይ ሚኒስትሩንም ሆነ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን ስልጣን በዘለለ መንገድ የእራሳቸውን ግንኙነት ከአምባሳደሮች ጋር እያደረጉ ነው የሚሉ ወገኖችም አሉ።

ሰሞኑን እንደሚታወቀው የሕወሓት መንግስት ከአርበኞች ግንቦት 7 እና ከፋኝ ጦር ጋር በተለያዩ ቦታዎች ውግያ እንዳደረገ እየተነገረ ነው።የአርበኞች ግንቦት 7 እና ከፋኝም የበላይነት እንደተቀዳጁ በእዚህ ሳምንት መጀመርያ ላይ አሳውቀዋል።አርበኞች ግንቦት 7 ባልተለመደ መልኩ " ኢትዮጵያውያን ሚናቸውን የሚለዩበት ጊዜ ላይ ደርሰናል" የሚል ሃሳብ ያለው ጠንከር ያለ መግለጫ አውጥቷል።




ጉዳያችን GUDAYACHN 

 www.gudayachn.com