ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, February 3, 2017

ሰበር ዜና - ግብፅ የደቡብ ሱዳን ተቃዋሚ ይዞታዎችን በጦር ጀት ደበደበች።ጉዳዩ አዲስ አካባቢያዊ ውጥረት ይፈጥራል።Egyptian Air Force bombs South Sudanese rebels




ጉዳያችን / Gudayachn 
ጥር 27/2009 ዓም  (ፈብርዋሪ 4፣2017)
========================
የሱዳን ህዝቦች ነፃነት ጦር የተሰኘው የደቡብ ሱዳን ተቃዋሚ ይዞታ ላይ የግብፅ የጦር አይሮፕላኖች ቢያንስ ዘጠኝ ቦንቦች መጣላቸውን የተቃዋሚ ጦሩ ቃል አቀባይ ኮ/ል ዊልያም ጋትጅአዝ ደንግ አስታውቀዋል።ቃል አቀባዩ አክለው እንደተናገሩት የግብፅ ድርጊት አካባቢያዊ ጦርነት ሊጭር ይችላል ማለታቸውን የደቡብ ሱዳን ዜና አገልግሎት ዘግቧል።ግብፅ የአየር ጥቃት ትናንት ሐሙስ እለት መፈፀሟን የገለፀው የሱዳን ህዝቦች ነፃነት ጦር የተሰኘው የደቡብ ሱዳን ተቃዋሚ ኃይል በጥር ወር ላይ ግብፅ እና የጁባ መንግስት የፈፀሙትን ውል ¨ቆሻሻ ውል¨በማለት ከጠራው በኃላ በስምምነቱ መሰረት ደቡብ ሱዳን ጠቀም ያለ የጦር መሳርያ ከግብፅ እንደምታገኝ ቃል እንደተገባላት በመጥቀስ መክሰሱ ይታወሳል።ከእዚህ በተጨማሪም የሁለቱ ሀገሮች ውል ኢትዮጵያ ላይ ያለመ መሆኑን ይሄው ተቃዋሚ ኃይል ባወጣው መግለጫ መጥቀሱ ይታወቃል።

በሌላ በኩል ዩጋንዳ ሰራዊቷን ከደቡብ ሱዳን ማውጣት ማሰቧን እና ይህም ለሱዳን ሰላም ወሳኝ መሆኑን ደግማ ያስተጋባችው በእዚህ ሳምንት ነበር።በተለይ የዩጋንዳ የእዚህ ሳምንት ሰራዊቷ እንደሚወጣ መግለጧ ከግብፅ ጉዳይ ጋር ለማያይዝ ግርታ ፈጥሮ ነበር።ይህ የግብፅ የአየር ጥቃት ጋር ጉዳዩ ሲያያዝ ግን ምናልባት የአየር ጥቃቱን ዩጋንዳም ከግብፅ ጋር ካደረገችው ንግግር ጋር የሚገናኝ ነጥብ ሊኖረው ይችላል የሚል ጥርጣሬ ያጭራል።የዛሬውን የግብፅ የአየር ጥቃት አስመልክተው መግለጫ የሰጡት ኮ/ል ዊልያም ጋትጅአዝ ደንግ (Colonel William Gatjiath Deng) የግብፅን ድርጊት የአፍሪካ ሕብረት፣ የተባበሩት መንግሥታት እና ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ምርመራ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

የሕወሓት መንግስት በእዚህ ሳምንት ለአፍሪካ ህብረት ስብሰባ አዲስ አበባ የገቡትን የግብፅ እና የደቡብ ሱዳን መሪዎች ጋር ያደረገውን የእግረ መንገድ ስብሰባ እያስታከከ ኢትዮጵያ ከደቡብ ሱዳንም ሆነ ከግብፅ ጋር ጥሩ ግንኙነት እንዳላት ከመግለፅ አልፎ የመንግስት ቃል አቀባይ በኢትዮጵያ እና በደቡብ ሱዳን መሃል ችግር እንዳለ የሚያወሩ ፀረ ሰላም እንደሆኑ መግለፃቸው እና ፋና ብሮድካስቲንግም ይህንኑ ከፍ አድርጎ ለማስተጋባት ሲሞክር ሰንብቷል።ብዙዎች የስርዓቱ ደጋፊዎችም ጭምር አቶ ኃይለማርያም ፈፅሞ የዲፕሎማሲው ደንብም ሆነ ፕሮቶኮሉ በማይፈቅደው ደረጃ ከመጠን ያለፈ ¨ተለማማጭ¨ የመሰለ ፈገግታ ለግብፁም ሆነ ለደቡብ ሱዳን መሪዎች በማሳየት በመታየታቸው ሕወሓት ኢትዮጵያን ምን ያህል ደረጃ እያወረዳት እንደሆነ በቁጭት የሚገልፁ ብዙዎች ናቸው።

ከእዚህ በታች የደቡብ ሱዳን ዜና አገልግሎት ከሰዓታት በፊት ግብፅ የደቡብ ሱዳን ተቃዋሚዎች ይዞታን በጦር ጀት መደብደቧን የገለፀበትን ሙሉ ዜና ይመልከቱ።

Egyptian Air Force bombs South Sudanese rebels in Upper Nile

February 3, 2017Breaking News, News, South Sudan

 The military command of the Sudan People’s Liberation Army-In Opposition (SPLA-IO) has accused Egyptian air force of carrying out air attacks on its bases in Kaka town, saying Cairo dropped at least nine bombs and explosions.

Rebel military spokesperson Colonel William Gatjiath Deng, who declined to offer more details, warned that the involvement of JEM, the SPLM-North, and Egypt in the ongoing civil war could provoke a regional war.

“The continuous involvement of the Sudanese rebels and the escalation of the Egyptian participation in the ongoing war in South Sudan are clear indications to the people of South Sudan, the African Union (AU), the United Nations (UN) and the international community that the Juba regime is provoking the region and tilting South Sudan for a regional war,” he said.

Col. Deng also claimed two Sudanese rebel groups: Justice and Equality Movement (JEM) and the SPLM-North sneaked into South Sudan Thursday from their northern base called Angathna in the Blue Nile and that their intention is to attack and retake Mustakbal, Wadekona, and Detang from the armed opposition.

He further asserted in a statement that combined forces of government and Sudanese rebels launched a coordinated attack on SPLA-IO positions in Detang today, which he said resulted in a shocking defeat to Lelo, adding rebel forces inflicted heavy losses on the enemies forcing them to flee to areas in Renk, Malakal, and Paloch.

He added the SPLA-IO captured 43 PKMs and 300 AK-47s in good condition.

The rebel spokesman further explained that Juba-backed forces were also repulsed in Booth and Mayom of Unity State. He claimed SPLA-IO Special Division captured nine government soldiers and that they are being treated as Prisoners of War.

South Sudanese rebels have increasingly become suspicious of recent bilateral agreements Cairo strucked with Juba.

In January, the SPLM/A-IO accused South Sudan and Egypt of striking a “dirty deal,” saying the agreement would allow Kiir to receive lethal weapons and ammunition from Egypt to wage a full-scale war against the armed opposition.

“There is a dirty deal going between Kiir and El-Sisi. the issue of Grand Ethiopian Renaissance Dam is one of the main deals being finalized in Cairo. Our intelligence sources in Kampala and Juba confirmed that Egypt wants South Sudan and Uganda to be her regional allies so that she can advance its covert sabotage campaign against the Ethiopian Dam. The man [Kiir] is a double agent; he will cause many problems for the entire East Africa region,” a senior rebel official told the South Sudan News Agency last month.

The official added that Egyptian military experts and engineers have been in Juba for months and that the entire secret military deal between Juba and Cairo was orchestrated by Kampala last year.

Col. Deng calls on the AU, UN, and the international community to investigate Egypt’s involvement in South Sudan civil war.

 Source: - ደቡብ ሱዳን ዜና አገልግሎት / South Sudan News Agency 

ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...