ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Monday, November 28, 2016

የኢትዮጵያ የውጭ ዕዳ ፣ ባለ እብነ በረዱ ህንፃ እና ኢትዮጵያን አጥፍቶ መጥፋት (የጉዳያችን አጭር ማስታወሻ)


ጉዳያችን/Gudayachn 
ህዳር 19፣2009 ዓም (ኖቬምበር 26፣2016)
==============================

የኢትዮጵያ የውጭ ዕዳ ጉዳይ 
====================
በ2016 እኤአ  ሰኔ ወር ላይ በተዘጋጀ ሪፖርት ኢትዮጵያ ከጠቅላላ ምርት  52% ለብድር ክፍያ እና ዋስትና የሚውል ሲሆን ከእዚህ ውስጥ 30% ለውጭ ብድር ዕዳ የሚከፈል ነው (ካፒታል ጋዜጣ፣ጥቅምት 17፣2016) የአሁኑ የኢትዮጵያ የውጭ ዕዳ በ2014 =16.59 ቢልዮን ዶላር ሲሆን በአንድ ዓመት ውስጥ በ2015=19.04 ቢልዮን ዶላር (ከ400 ቢልዮን ብር በላይ) ደርሷል (CIA world fact book report)  

እኤአ 2016 ሲጠናቀቅ ደግሞ ከ21 ቢልዮን ዶላር በላይ እንደሚሆን በእዚህ ዓመት የሰማናቸውን የብድር ስምምነቶች  ደምረን ማወቅ እንችላለን።በአንፃሩ የኢትዮጵያ ገንዘብ ንፁህ ወርቅ ሳይቀር (ባለፈው ሳምንት ህንድ ኒው ዴሊ የተያዘውን ወርቅ ጨምሮ) በባለስልጣናት እና ዘመዶቻቸው እየተመዘበረ ነው።

ባለ እብነ በረዱ ህንፃ
=============== 
ከእዚህ በታች የምታዩት ህንፃ አዲስ አበባ ከንግድ ሥራ ኮሌጅ ዝቅ ብሎ የሚገኘው የፀረ ሙስና ኮሚሽን ህንፃ ነው።አሁን መስርያ ቤቱ ጥርሱ ወልቆ ስለ ሙስና ማስተማር እንጂ መክሰስ አትችልም ተብሎ ተቀምጧል።አቶ ኃይለ ማርያም አንድ ሰሞን ስለ ሙስና ፉከራ ነገር ሲያሰሙ ነበር።ዛሬ አቶ ደብረ ፅዮን ባልተስተካከለ አማርኛ ስለ ጥልቅ ተሃድሶ እያሉ ኢትዮጵያ በአራቱም አቅጣጫ ስትዘረፍ ዜማ እያወጡላት ነው። የኢትዮጵያ የውጭ ዕዳ በታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ ጨምሮ ብዙዎች ባለስልጣናት በውጭ ሃገራት በሚልዮን ዶላር እያጋበሱ ነው።የባለስልጣናት ልጆች ከኢትዮጵያ በሚላክ የውጭ ምንዛሪ በሚል ቅለድ ውጭ ሀገር ይኖራሉ፣ይነግዳሉ።ኢትዮጵያ ግን በዕዳ ተዘፍቃ፣ተቆጣጣሪ የሌለባቸው የዘመኑ ባለስልጣናት ይንደላቀቃሉ ሲፈልጉ ከመኪና መኪና ያማርጣሉ።
















ኢትዮጵያን አጥፍቶ መጥፋት 
===================
የኢትዮጵያ ውጭ ዕዳ ለትውልድ በሚተርፍ መልኩ እየጨመረ ነው።አሁን ዝርፍያው በኮማንድ ፖስቱ ደረጃ ተደራጅቶ ወደ እያንዳንዱ ሰው ቤት እየወረደ ነው።የኢትዮጵያውያን ቤት ልክ ደርግ በ1960ዎቹ መጨረሻ እንደሚያደረገው ቤት በማንኛውም ጊዜ ይበረበራል። ፈታሹ ያገኘውን ዕቃ የመውሰድ መብት አለው።ብዙዎች ጥሬ ገንዘብ ሳይቀር ከቤታቸው በኮማንድ ፖስቱ ተዘርፎባቸዋል። የሚጠፋው የሰው ሕይወት እና የታሰረው ወጣት ቁጥር የትዬለሌ ነው።ይህ ሁሉ ሆኖ የኢትዮጵያ ንግድ ሚዛን ተዛብቶ ቀውስ ተባብሷል።ኩባንያዎች ሰራተኞች እያባረሩ ነው። ለስርዓቱ ቅርብ የሆኑት እንደ ተክለ ብርሃን አምባዬ ኮንስትራክሽን ሳይቀሩ 400 ሰራተኛ የቀነሱት በቅርቡ ነው። ቱሪዝም በአስደንጋጭ ደረጃ ቀንሷል።

የቡና አቅርቦት ለአንድ ዓመት ያህል በኦሮምያ በተነሳ ሕዝባዊ ማዕበል ቀንሷል።በርካታ ኩባንያዎች ኢትዮጵያን እየለቀቁ እየሄዱ ነው።በሰሜናዊ የኢትዮጵያ ክፍል ጦርነት መከፈቱ ከተነገረ ሰነበተ።ይህ ማለት ሕወሓት የመከላከያ እና ደህንነት በጀት የበለጠ ያወጣል ማለት ነው።ይህ በደከመው የኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት ላይ ድህነቱ እና የዋጋ ንረቱን ያብሰዋል።ለእዚህ ሁሉ ቀውስ መነሻው የሕወሓት የስልጣን ጥማት አለመርካት ነው።ኢትዮጵያን አጥፍቶ መጥፋት የሚለው የሕወሓት መንገድ አደገኛ ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ በጎሳ እና መንደር መከፋፈል ትቶ ለኢትዮጵያ በአንድ ልብ መነሳት ያለበት ጊዜ አሁን ነው።ኢትዮጵያን እንደ ሀገር ለማስቀጠል እና ከአጥፍቶ ጠፊ ለመታደግ የእያንዳንዱ ሰው ኃላፊነት ነው።

ጉዳያችን GUDAYACHN

 www.gudayachn.com

Friday, November 25, 2016

Thursday, November 24, 2016

Breaking News: A heavy fight broke out between Ethiopian government and Patriotic Ginbot 7 forces.

Commander Mesafint Tigabu 


Abbay Media News

By Surafel Aerate

A heavy fight between Ethiopian government troops and Patriotic Ginbot 7 forces broke out in the outskirts of  Gonder. Abbay Media sources from the war zone confirmed that there have been very heavy fight going on between the two foes since yesterday. This is the first time that the Ethiopian army used its military Tanks and sophisticated machine guns against Patriotic Ginbot 7 forces.

Our sources who are participated in this fight told us that there are casualties from both sides. From Patriotic Ginbot 7 side, three of its division (Ganta) leaders have been killed and three other fighters surrendered on the battlefield. In the other hand, from the government side, more than Thirty government troops killed by patriotic forces. In addition, unknown numbers of government troops have surrendered to Patriotic Ginbot 7 forces.

During the fight, Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracy ranking official, commander Mesafent Tegabu nicknamed Gebrye refused to surrender and killed himself on the battlefield. When he was asked to surrender, commander Tegabu claimed that he is the son of King Tewodros and he would rather kill himself instead of giving himself up to the fascist regime. After fierce fight with heavily armed with Tanks and machine guns government troops, commander Tegabu refused to give himself up and shot and killed himself.   

Source : Abbay Media News 
             

Monday, November 21, 2016

¨የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ግብረ ሀይል ኮማንድ ፖስትን ይመሩ ከነበሩ መካከል 5 አዛዦች በአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት ተገደሉ።¨ የአግ7 ራድዮ Five state of emergency command post commanders are killed

ፎቶ አርበኞች ግንቦት 7 ድረ-ገፅ 


ካለፈው ሳምንት መጨረሻ ጀምሮ የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊቱን ወደ ኢትዮጵያ ማስገባቱን እና ገዢ መሬቶችን መቆጣጠሩን እየገለፀ ነው።የድርጅቱ ራድዮ ይህንኑ አስመልክቶ በፎቶ ግራፍ የተደገፈ ዘገባ አቅርቧል። የራድዮው ሙሉ ዘገባ ከእዚህ በታች እንዳለ ቀርቧል።
==================================
November 20, 2016
(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ)
===========================
የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ሰራዊት ህዳር 7 ቀን 2009 ዓ.ም በቃፍቲያ ሁመራ ልዩ ስሙ ማይነብሪ በተባለው ቦታ ከመቀሌ የተላከ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ኮማንድ ፖስት ግብረ ሀይል ጋር ባደረገው ውጊያ ከፍተኛ ድል ተጐናፅፏል።

ይህ ከመቀሌ የተንቀሳቀሰው የወያኔ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ኮማንድ ፖስት ግብረ ሃይል ዋና ተልዕኮ የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊትን እንቅስቃሴ ለመግታት ታስቦ ሲሆን እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰራዊት በ56 መኪኖች አጓጉዞ በቃፍቲያ ሁመራ ልዩ ስሙ ማይነብሪ በተባለ ቦታ ቢያሰፍርም ለሀገራቸውና ህዝባቸው ሲሉ ውድ ህይወታቸውን ለመክፈል የማይሰስቱት የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት በከፈቱት ድንገተኛ ማጥቃት 92 በመግደልና 65 በማቁሰል አንፀባራቂ ድል ማስመዝገባቸውን ከስፍራው የሚገኘው አርበኛ ታጋይ ሪፖርተራችን ባደረሰን ዘገባ ለማወቅ ተችሏል።
ፎቶ አርበኞች ግንቦት 7 ድረ-ገፅ 

ይህ በእንዲህ እንዳለም የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት እንቅስቃሴን ለመግታት የተንቀሳቀሰውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ግብረ ሀይል ኮማንድ ፖስትን ይመሩ ከነበሩ መካከል 5 አዛዦች የተገደሉ ሲሆን ከእነዚህም መካከል መቶ አለቃ ጣዕመ የሚባል እንደሚገኝበትም ታውቋል።

በተያያዘ ዜና የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ሰራዊት ህዳር 8 ቀን 2009 ዓ.ም በቃፍቲያ ሁመራ ሩዋሳ አካባቢ ማይጐነጥ ልዩ ስሙ ማይቆማ በተባለው ቦታ ሰፍሮ ከሚገኘው የ24ኛ ክፍለ ጦር ጋር ባደረገው ውጊያ አንድ ብርጌድ ካምፕ ሙሉ ለሙሉ ከማውደሙም በተጨማሪ በወያኔ መከላከያ ሰራዊት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ማድረሱን ከስፍራው የደረሰን የአርበኛ ታጋይ ሪፖርተራችን መረጃ ያመለክታል።

በዚሁ አካባቢ በተደረገው ውጊያ የወያኔው የ24ኛ ክፍለ ጦር ሰራዊት ከአርበኞች ግንቦት 7 ጀግኖች የሚሰነዘርበትን ጥቃት መቋቋም ተስኖት እንደነበረ ለማወቅ ተችሏል።

በእለቱ በተደረገው ውጊያ 120 የወያኔ መከላከያ ሰራዊትን በመግደልና 80 በማቁሰል በጠላት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን በርካታ ቁጥር ያላቸው ከባድና ቀላል ተተኳሽ መሳሪያዎችን ከነመሰል ጥይቶቻቸው ጋር መማረካቸውንም ሪፖርተራችን ገልጿል።

በውጊያው እለት የቆሰሉ የወያኔ መከላከያ ሰራዊት ብዛት ቁጥር ስፍር የሌለው ከመሆኑ የተነሳ ሁመራ የሚገኘው ሆስፒታል በቁስለኞች መጥለቅለቁንና ከፍተኛ የመቁሰል አደጋ የደረሰባቸውን ደግሞ ወደ ጐንደር ሆስፒታል በመላክ ላይ መሆናቸውም ተገልጿል።

የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ሰራዊት ባደረገው ተከታታይ የማጥቃት ርምጃ የአካባቢው ነዋሪ ህብረተሰብ እጅጉን ከመደሰቱም በተጨማሪ ከትግሉ ጐን ለመሰለፍ ያላቸውን ቁርጠኝነት እየገለፁ እንደሚገኙም ታውቋል።

የወያኔ አገዛዝ ባለስልጣናትም በእነዚህ አካባቢዎች የሚገኙ ነዋሪዎችን አገዛዙን ለመፋለም ከአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት ጋር እንዳይገናኙ አካባቢውን በመውረር ህብረተሰቡ ከቤቱ ወጥቶ እንዳይንቀሳቀስ በማድረግ ስራ ላይ ተጠምደው የሚገኙ ሲሆን፤የሞቱ የሰራዊቱ አባሎቻቸውንም ህዝቡ እንዳያይባቸው የራሳቸውን ሰዎች በመመልመል እንዲቀበሩ እያደረጉ መሆናቸውን ሪፖርተራችን አክሎ ገልጿል።

በደረሰባቸው የሰው ህይወትና የንብረት ኪሳራ እጅጉን የተደናገጡት የህወሀት አገዛዝ ባለስልጣናትም በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ኮማንድ ፖስት ግብረ ሀይልና በ24ኛ ክፍለ ጦር ላይ ከአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት የሚሰነዘረው ጥቃት ተጠናክሮ በመቀጠሉና ፋታ ሊሰጣቸው ባለመቻሉ በአካባቢው የጦር ሄሊኮፕተሮችን በማሰማራት አሰሳና ቅኝት ሲያደርጉ እንደነበረ ተገልጿል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት እስከአሁን ባደረጋቸው ውጊያዎችና ባስመዘገባቸው ድሎች በመደሰት በአካባቢው የሚገኙ የሚሊሸያ ታጣቂ ሀይሎች ከወንድሞቻችን ጋር ውጊያ አናደርግም በማለት በአገዛዙ ላይ እንዳመጹና ብዛት ያላቸው የሚሊሸያ አባላትም ከአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት ጋር መሰለፋቸውን ከስፍራው የደረሰን የአርበኛ ታጋይ ሪፖርተራችን መረጃ ያስረዳል።

ምንጭ - http://www.patriotg7.org/?p=1157 

ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Friday, November 18, 2016

ጎዳናው ይገርማል (ግጥም ቪድዮ)

ጀግና ልጅ አትወልድም አያቶቿን ገድላ የምትሸልል ሀገር
በበረከት በላይነህ



ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Thursday, November 17, 2016

በኦስሎ በወቅታዊ የሀገራችን ተያያዥ ጉዳዮች ዙርያ ልዩ ውይይት በኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ ኖርዌይ ተዘጋጀ

ካልተወያዩ ኢትዮጵያን በምኞት አይገነቧትም።ሃሳባችንን እናካፍል!
የሌሎችንም ሃሳብ እንስማ !

ተወያዩ! ዝም አትበሉ።የሀገራችን ጉዳይ ያገባናል።ሁላችንም ሃሳቦች አሉን።ሃሳቦቻችንን ለሌሎች ማካፈል ካልቻልን ወይንም የሌሎች ሃሳቦችን መስማት ካልቻልን ነገ ምን አይነት ኢትዮጵያ እንድትኖረን እንፈልጋለን? ኢትዮጵያን በምኞት መገንባት አይቻልም ሃሳቦችን በማንሸራሸር የጋራ ግንዛቤ በመያዝ ግን አንድ እርምጃ ወደፊት መሄድ ይቻላል።

 የትግራይ ነፃ ኣውጭ ግንባር (ሕወሓት) ወደ ኋላ በመጓዝ በዘመነ ደደቢት ላይ ይገኛል::ኢትዮጵያ ሙሉ በሙሉ በህዋሃት መኮንኖች ስር ወድቃለች::ማሰር መግደል እያንዳንዱ መኮነን መብት ብቻ ሳይሆን የኣንድ ተራ ወታደርና ፖሊስ መብት ሆኗል:: በአንድ ወር ብቻ እስከ መቶ ሺህ የሚገመቱ ኢትዮጵያዊያን ወደ ስር ተግዘዋል::በዘመነ ደደቢት ጊዜ እስር ቤቶች የተፈጥሮ ዋሻዎችና ሰው ሰራሽ ጉድጓዶች በነበሩበት ወቅት የእስር ቤቶች ኣዛዦች የነበሩት ኣሁንም መርማሪዎች የእስር ቤቶች ኣለቆች ናቸው:: በኢትዮጵያ ታሪክ ያልታየ እስር ቤቶችን በ እስርኞች እንደተሞሉ ማቃጠል ኢትዮጵያ ውስጥ የተለመደ ሆኗል::

ታዲያ በደረስንበት በዘመነ የተቋሚዎች ኣሰላለፍ ምን ይመስላል?
በተለይ በነፃ የመደራጀት እድል ያላቸው በውጭ ኣገር የሚገኙ ተቃዋሚዎች ኣሰላለፍ ምን ይመስላል?
በጣም ሊበረታታ የሚገበው በብሔራዊ ደረጃ ወይም በኣገር ኣቀፍ የተደራጁ ኣሉ
በርካታ ድርጅቶች በብሄራቸው ተደረጅተው የሚታገሉ ኣሉ::  የኦሮሞ ህዝብ በብሔር ተደራጅቷል::  ኣማራም  በብሔር መደራጀት ጀምሯል::

በኣደረጃጀት ዙሪያ በርካታ ጠንክር ጠንከር ያሉ መተቻቸቶች ይታያሉ::ትችቶች ገንቢ ናቸው?
የተቀዋሚው ኣደረጃጀት በቂ ነው?
ራሳቸውንና ህዝቡን ለመከላከል በጎበዝ ኣለቃ ተደራጅተው እየታገሉ እንዳሉ እየተሰማ ነው።በቂ ትኩረትና ድጋፍ ኣግኝተዋል?  ካላገኙ ለምን? ሕዝብ በውጭ እና በአገር ቤት ያለው ምን እያደረገ ነው?

እነኝህን እና ተያያዥ ወቅታዊ የሀገራችን ጉዳዮች ዙርያ የኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ በኖርዌይ በመጪው ቅዳሜ የጠረንጴዛ ዙርያ ውይይት አዘጋጅቷል።ውይይቱ በቪድዮ የሚዘጋጅ ሲሆን በውይይቱ ላይ ለመሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውም የኢትዮጵያ ጉዳይ ይመለከተኛል የሚል በሙሉ መገኘት ይችላል።

የጠረንጴዛ ዙርያ ውይይት 

ኣዘጋጅ  =     የኢትዮጵያውያውያን የጋር መድረክ በኖርዌይ
                     አራት ተወያዮች ተዘጋጅተዋል::
                     ውይይቱ ለሁሉም ከፍት ነው:: ለተወያዮች ጥያቄ
                     ማቅረብ ኣስተያየት መስጠት ይቻላል::
ቀን =           በመጪው ቅዳሜ ህዳር 10፣2009 ዓም
                     (ኖቬምበር 19፣2016)  

ቦታ=            ባትሬት 
አድራሻ       Fredsbogveien 24 A, Oslo, Norway

ሰዓት =         እኩለ ቀን (12 am) ይጀመራል። 


ፀጋዬ እሸቱ እውነት 



ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Tuesday, November 15, 2016

በእስራኤል የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ባለፈው ወር ያደረጉት ዝግጅት (ቪድዮ) Ethiopians in Israel discussing on home politics


ቪድዮውን ተመልክተው ሲጨርሱ በእስራኤል ያሉ ኢትዮጵያውያን  በመጪዋ ኢትዮጵያ ላይ ስለሚኖራቸው ሚና እንዲያሰላስሉ ያደርጋል።



ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Sunday, November 13, 2016

Tension between TPLF led, Ethiopia and Egypt is increasing; A couple of Egyptian citizens residing in Addis Ababa are arrested.

Taha Mansour 

According to sources from Addis Ababa a number of Egyptians were arrested by Tigray Peoples Libration Front (TPLF) led-government security personnel.  Ethiopian Weekly news paper, Capital on Nov.7,2016  issue, confirmed as a number of Egyptians are under Ethiopian security forces since October 31. 

The well known hotel, Addis Ababa Radisson Blue Hotel Executive Assistant Manager Taha Mansour was one of the arrested Egyptian citizen on Monday, October 31,2016.Taha has been working at the Radisson Blu since November 2012. That is after he moved from Radisson Blu Resort El Quseir, in Egypt. On the same day another Egyptian from his office was captured.The organisation name and individual´s name is not yet disclosed. 

State television of Ethiopia made a number of documentary films accusing Egypt for assistance Ethiopian opposition forces. While Egyptian officials repeatedly denied for Ethiopian Government accuses. It is known that Ethiopia is under state of emergency to crash protesters against TPLF brutal government.According to articles of state of emergency declared 6 weeks back, main highways from the capital take to southern, northern, western and eastern part of the country are under the title of ´´red line´´ meaning no one is allowed to approach them with out the information of the command post. 
  

ጉዳያችን GUDAYACHN

 www.gudayachn.com

Monday, November 7, 2016

የኢትዮጵያ የወቅቱ የተቃውሞው የፖለቲካ ሜዳ ተስፋ አስቆራጭ አይደለም።ይልቁንም በብዙ ተስፋ የተሞላ ነው። (የጉዳያችን አጭር ማስታወሻ)


  • የሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች እና ስብስቦች ፍላጎት ምንድነው? ብለን ስንጠይቅ የምናገኘው መልስ አንድ ነው። 
  • የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሁኔታ ተስፋ ሰጪ እና ወደፊት ሲሄድ እንጂ ወደ ኃላ እየሄደ አለመሆኑን መገንዘብ ይገባል።
  • በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥም በሁሉም ወገን የሚታዩ ፅንፈኞች ይኖራሉ።
ኢትዮጵያን አንዳንዶች በአንዳንድ መድረኮች ላይ በተነገሩ ንግግሮች ወይንም የተንሸዋረረ የግለሰቦች የፖለቲካ እና ታሪካዊ ትንተና አንፃር እየተመለከቱ ተስፋ አስቆራጭ ደረጃ እንደደረሰች የሚገምቱ አሉ።ይህ ግን የተሳሳተ አስተሳሰብ ነው።ኢትዮጵያ አሁን የምትገኝበት የፖለቲካ ሁኔታ ተስፋ አስቆራጭ አይደለም። ተስፋ አስቆራጭ አድርጎ የሚያቀርበው ስልጣኑን የሙጭኝ ብሎ ሕዝብ እየገደለ እና እያሰረ የሚገኘው ሕወሓት ነው።ይህ ማለት ግን ከሁሉም ወገን ስልጡን አካሄድ መሄድ አይጠበቀም ማለት አይደለም።

ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ ሶስት  ቀናት ውስጥ በባህር ማዶ ኢትዮጵያን የሚመለከቱ ክንውኖችን በአጭሩ በማሳታወስ የወቅቱን የፖለቲካ ሁኔታ የተራራቀ የመሰለን ግን በአንድ መስመር የሚሄዱበት በርካታ እድሎች መኖራቸውን በቀላሉ ማሳየት ይቻላል።እያንዳንዱ ክስተቶች የእራሳቸው ተቃራኒ ሃሳቦች ተነስተውባቸዋል።

የመጀመርያው የኢትዮጵያ ሃገራዊ ንቅናቄ የተሰኘው በአርበኞች ግንቦት 7፣የአፋር ፓርቲ፣ሲዳማ ንቅናቄ እና ኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር የተመሰረተው ንቅናቄ ነው።ንቅናቄው እንደመግለጫው በርካታ ስራዎች የሚቀሩት መሆኑን ቢገልጥም በኢትዮጵያዊነት ስር መንቀሳቀስ ወሳኝ መሆኑን ገልጧል።የእዚህን ንቅናቄ የሚተቹት በአማራውም ሆነ ኦሮሞ ብሔርተኝነት ስም የሚገኙ ናቸው።የአማራው ብሔርተኝነት በተለይ እራሱ በአግባቡ አለመወከሉን ይገልፅና የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር ውስጥ የተወከሉት ግለሰቦች በ1980ዎቹ ውስጥ በአርሲ እና ሐረር ጨምሮ ለተፈፀሙት ግድያዎች ተሳትፎ አላቸው ይላሉ። በአንፃሩ በኦሮሞ ማሕበረሰብ በኩል የእነ አቶ ሌንጮ እና ዶ/ር ዲማ ከአንድነት ኃይል ጋር ንቅናቄ አባል መሆናቸው እንደ ስህተት ይቆትሩባቸዋል።እዚህ ላይ ኦነግ የሚለውን እንቅስቃሴ የጀመሩት ውስጥ እኔ ዶ/ር ዲማ መሆናቸውን ሁሉ ዘንግተው ከማን ጋር መሆን እንዳለባቸው ሊመክሯቸው ይሞክራሉ።ይህ ሁሉ ወቀሳ ግን የተለያዩ አስተሳሰብ ጥጎች ናቸው እንጂ ክፉ ክስተቶች አይደሉም። ዋናው ኢትዮጵያዊ አጀንዳ እስካልተጣለ ድረስ ሊስተካከል የሚችል ቀላል የሂደት ጥያቄ ነው።

ሁለተኛው የእዚህ ሳምንት መጨረሻ ክስተት የኦሮሞ ሚድያ ኔትዎርክ ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ ላይ ከዶ/ር ፀጋዬ አራርሳ እና ኢታና ጋር በተደረገ ውይይት ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር በቅርብ የተመሰረተች መሆኗን ከአንድ ሰዓት በላይ በረዘመ ቃለ መጠይቅ ላይ ሲነገር ተሰምቷል።ሌላው ቀርቶ የሚለበሰው ´´የሀገር ልብስ ሳይቀር የዐማራ ባህል ተፅኖ ነው´´ የሚል አገላለጥ ተሰምቷል።በተለይ ኢትዮጵያ የሚለው ቃል በቅርብ የመጣ ነው የሚለው አነጋገር የሚያጣቅሰው ማስረጃ ሳይኖር በደፈናው አቢሲንያ ትባል ነበር ሲባል ተሰምቷል።ሌላው ቢቀር የኢትዮጵያ ነገስታት ከጥንት ጀምሮ የተፃፃፉት ደብዳቤ፣በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከሁለት ሺህ ዓመታት በፊት የተፃፈው ኢትዮጵያ የሚለውን ቃል ሁሉ ገደል የከተተ ስንኩል አቀራርብ ነበር።

ሶስተኛው ክስተት በትናንትናው ማለትም በጥቅምት 27፣2009 ዓም በሲያትል የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ አዳራሽ የተጠራው እና ምሁራን፣የታሪክ ሰዎች፣የሃይማኖት አባቶች እና አክትቪስቶች የተገኙበት የዐማራ ማኅበረሰብ የጋራ ግብረ ኃይል የተጠራ ስብሰባ ነበር። 

በስብስባው ላይ የምጣኔ ሐብቱ ባለሙያ ዶ/ር አክሎግ እና ድምፃዊ ሻምበል በላይነህን ጨምሮ በርካቶች ታድመውበታል።በስብሰባው መጨረሻ ላይ የጋራ ምክር ቤት በመመስረት ተፈፅሟል።
ከእዚህ በተጨማሪ ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ በአማካሪነት እንዲሰሩ ጥቆማ ቀርቧል።ጉባኤው ከሞላ ጎደል የዐማራው ማኅበረሰብ በሕወሓት ስርዓት ውስጥ ዘርን ያማከለ ጥቃት መድረሱ፣ጥቃቱ ከሌሎች ፅንፈኛ አካላትም መሰንዘሩ፣ ኢትዮጵያን እና እምነቷን ለማጥፋት የዐማራው ማኅበረሰብ ኢላማ መሆኑ እና እነኝህን ችግሮች ለመፍታት የዐማራው መደራጀት አስፈላጊ መሆኑ ተደጋግሞ ተወስቷል።

ከላይ የተመለከትናቸው ክንውኖች በሙሉ እንቅስቃሴን፣መፍትሄ ፍለጋን እና አለመተኛትን የሚያሳዩ እንጂ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ተስፋ አስቆራጭ መሆኑን አያሳይም።አሁን በስልጣን ላይ ላለው ስርዓት ግን በእየዘርፉ እና በአይነት የጠመዱበት የመሳርያ አይነቶችን ያሳያል።ከብሄር ስብስብ እስከ ኢትዮጵያዊነት መገለጫነት በእየመልኩ ያሉ ኢትዮጵያውያን ሁሉ የሚስማሙበት አንዱ እና ዋናው ነጥብ የሕወሓት መንግስት ስልጣኑን ለሕዝብ ማስረከብ እንዳለበት ነው። በሌላ በኩል ከላይ የሚታዩት የፖለቲካ አቀማመጦች መልክ ለመስጠት ከኢትዮጵያ የፖለቲካ ድርጅቶች እና ስብስቦች በሙሉ እውነትኛ ችግሮችን እየነቀሱ እና በእርሱ ላይ ብቻ እያተኮሩ መፍትሄ መስጠት እና ወደ አንድ መድረክ መምጣት እንዳለባቸው አመላካች ጊዜም ነው ወቅቱ።ከሁሉም ግን በተለይ በማኅበራዊ ሚድያ ላይ የሚሰጡ ሃሳቦች ከስድብ እና አጉራ ዘለል ንግግሮች እንዲጠሩ እና በጨዋነት ላይ የተመሰረቱ ቃላትን መጠቀም የግድ ይላል።ማንም የፈለገውን አይነት ሃሳብ ይኑረው ማክበር እና ሃሳብን በጥሩ ቃላት መግለፅ መልመድ ተገቢ ነው።

ከእዚህ በተረፈ ግን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሁኔታ ተስፋ ሰጪ እና ወደፊት ሲሄድ እንጂ ወደ ኃላ እየሄደ አለመሆኑን መገንዘብ ይገባል።ምናልባት ኢትዮጵያ የቅርብ ጊዜ ክስተት ነች ብለው የሚናገሩት ወደ ኃላ እየነዱን እንደሆነ እናስብ ይሆናል። እውነታው ግን በተቃራኒው ነው።ምክንያቱም የእዚህ አይነቱ አባባል በእራሱ  ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ያነቃ እና ፅንፍ የያዙት ኢትዮጵያን የሚያጥላሉበት ደረጃ የት ያህል እንደሆነ ያነቃል፣ያዘጋጃል።

በመጨረሻም የሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች እና ስብስቦች ፍላጎት ምንድነው? ብለን ስንጠይቅ የምናገኘው መልስ አንድ ነው። እርሱም በመጪዋ ኢትዮጵያ ውስጥ ዋስትና ማግኘት የሚል ነው። የኦሮሞ ማኅበረሰብም ሆነ የዐማራ ማኅበረሰብ እንዲሁም ሌላው ሁሉ በነገዋ ኢትዮጵያ ውስጥ አንዱ በዳይ ሌላው ተበዳይ እንዳይሆን ዋስትና ይፈልጋሉ።ይህንን ዋስትና እንዴት አስተማማኝ ማድረግ ይቻላል? ዋናው እና ቁልፉ የፖለቲካ ኃይሎች ሊመልሱት የሚገባ ቁልፍ ጥያቄ ነው።ይህንን ማስተማመኛ ዋስትና ቢኖርም የማይቀረው ግን የፅንፈኞች ጫፍ የያዘ ሃሳብ እስከመቼውም የማይቀር የፖለቲካ እንክርዳድ ነው።እንክርዳድ እንዳይኖር ማድረግ አይቻልም ዋናውን ስንዴ ሳይጎዱ መንቀል ግን ይቻላል።ለመንቀል ግን ትግስት እና ጥበብ ይፈልጋል።በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥም በሁሉም ወገን የሚታዩ ፅንፈኞች ይኖራሉ።ሆኖም ግን ሃሳባቸውን እንደ ሃሳብ እየሰሙ እና ተገቢ ከስድብ የራቀ ምላሽ መስጠት ከእዚህ ባለፈ ግን በኃይል ሃሳባቸውን ለመጫን ሲሞክሩ እንደ እየአመጣጣቸው በሕዝብ ምላሽ እንዲሰጥ ህዝብን ማንቃት ተገቢ ነው።ኢትዮጵያ አሁን የተጫናትን የሕወሓት አገዛዝ ማስወገድ ከቻለች መጪው ብሩህ ተስፋ እንደሆነ ቅንጣት ታህል መጠራጠር አይገባም።
==============================================
አንዳንዴ የጋራ ዕሴቶቻችን ላይ አለማተኮር ለምሳሌ ኪነ ጥበብ ልዩነታችን የበዛ ያስመስለዋል።ኦሮሞው ቢናገር፣ ዐማራው ቢደራጅ፣ሱማሌው ቢቃወም፣ ደቡብ ቢወቅስ  መርሳት የሌለብን ሁሉም ያገር ልጅ መሆኑን ለትውልዱ ደጋግሞ መንገር ተገቢ ነው።የጋራ የሆኑ ዕሴቶችን እያነሳን መኮርኮር የኅብረታችን መገለጫ ነው።ለሕዝብ ተስፋን ማሳየት ለዲሞክራሲ መብቱ የሚያደርገውን ትግል ሁሉ ያጠነክረዋል።

ድምፃዊት ፍሬ ሕይወት ስለሺ
  ´´ዘመድ ያገሬ ልጅ´´
ያገሬ ልጅ  (ሰሜን ያለው፣ደቡብ ያለው፣ ሱማሌ ያለው፣ወለጋ ያለው) 
አብሮ አደጌ እንዴት ነህ ቃናዬ .....


ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Saturday, November 5, 2016

የሕግ ምሁሩ የጎንደር ሕብረት ለኢትዮጵያ አንድነት የቦርድ አባል ፕሮፌሰር ዓለም አንተ ገብረ ስላሴ አማራ፣ኦሮሞ እያሉ ከመደራጀት በመልክዓምድር መደራጀት ለኢትዮጵያ እንዴት እንደሚበጅ በምክንያት ያስረዳሉ።ያዳምጧቸው።

ማሳሰቢያ
======= 
ከጉዳያችን ውጭ የሚመጡ ነገር ግን በጉዳያችን በኩል የሚተላለፉ መልዕክቶች፣ዜናዎች እና ሃሳቦች  የጉዳያችንን ሃሳብ የግድ ያንፀባርቃሉ ማለት አይደለም።ሆኖም ግን የሚነሱ ሃሳቦች ለሕዝብ መድረስ እና ሕዝብ እንዲወያይበት ማድረግ ተገቢ ነው ከሚል እሳቤ መሆኑ መታወቅ አለበት። ሃሳቦችን በቶሎ ወደ ፊት እያመጡ እየተቋጩ ካልመጡ እየተመላለሱ የሕዝብን ሃሳብ ይበትናሉ።ተወደዱም ተጠሉም ሃሳቦቹ ሕዝብ መሃል የምንገዋለሉ ሃሳቦች ናቸው።መልክ አስይዞ ቅርፅ መስጠት እና ወደ በጎው መንገድ መምራት የመገናኛ ብዙሃን እና የምሁራን ሚና መሆን ነበረበት።

ምንጭ= ሕብር ራድዮ 




ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

Friday, November 4, 2016

የዐማራ ሕዝብ አንድነት ግብረ ኃይል እሁድ ጥቅምት 27፣2009 ዓም በሲያትል አሜሪካ ስብሰባ ጠርቷል ስብሰባው ለኢትዮጵያ የወቅቱ ፖለቲካ ምን ይዞ ይመጣል?


ጉዳያችን/ Gudayachn 
ጥቅምት 26፣2009 ዓም 
================
የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሁኔታ ወዴት እየሄደ እንደሆነ ለማወቅ በሚቻልበት ደረጃ አይደለም።በሀገር ቤት በተለይ በዐማራ እና ኦሮሞው ክፍል ለመናገር የሚዘገንን ግድያ፣ስቃይ እና ሰቆቃ በሕወሓት ወታደሮች እየተፈፀመ ነው።ይህ የኢንተርኔት እና ስልክ መስመሮችን በመዝጋት የሚፈፀመው ግድያ እና እስር በተለይ በዐማራ በኩል ከሕዝቡ እየተሰጠ ያለው ምላሽ ወደ በረሃ ወርዶ ከመፋለም እስከ እጅ በእጅ ትንቅንቅ ድረስ ሕዝቡ እየተፋለመ ነው።በእዚሁ ሳምንት መጀመርያ ላይ የባህር ዳር ነዋሪ ወጣቶች በስርዓቱ ባለስልጣናት መኖርያ ሰፈር እና በማዘጋጃ ቤት ቢሮ ላይ የፈፀሙት የቦንብ ጥቃት አንዱ የትንቅንቁ መገለጫ ሆኖአል።በሰሜን ጎንደርም መጠነ ሰፊ ጦርነት እየተካሄደ ነው።የገበሬውን መሳርያ ለመንጠቅ የዘመተው የሕወሓት ሰራዊት በሄደበት የገበሬው የጥይት አረር እያረገፈው መሆኑን የሚገልጡ ዜናዎች እየወጡ ነው። 

ይህ በእንዲህ እያለ ነው በመጪው እሁድ ጥቅምት 27፣2009 ዓም  ´´የዐማራ ሕዝብ አንድነት ግብረ ኃይል´´በሲያትል አሜሪካ ስብሰባ ጠርቷል።ይህ ስብሰባ በተለይ በዐማራ ዙርያ የተሰባሰቡ ድርጅቶች፣ሲቪክ ማኅበራት፣አክትቪስቶች እና ምሁራንን ሁሉ የሚያሳትፍ እንደሚሆን ተገልጧል።በኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ብቻ እንደሚያሸበርቅ የሚጠበቀው ይህ ስብሰባ በዐማራው ማኅበረሰብ ዙርያ የተሰባሰቡ ሁሉ በግልፅ እና በጋራ የሚገናኙበት የመጀመርያ መድረክ ይሆናል።

ስብሰባው የሚደረግበት ዋና ምክንያት እና አጀንዳዎች ምን ምን እንደሆነ እስካሁን አልታወቀም።በተለያየ መልኩ የተደራጁ አደረጃጀቶች ግን አንድ አይነት የኅብረት መድረክ እንደሚፈጥሩ ይታሰባል።በስብሰባው ላይ የጎንደር ኅብረት፣ሞረሽ ወገኔ እና ቤተ ዐማራን እንደሚጨምር የተገለጠው ስብሰባ የብዙዎችን ትኩረት ስቧል።

ባብዛኛው ወጣቶች የሚንቀሳቀሱበት የዐማራ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ሲቪክ ማኅበራት እና አክትቪስቶች በተለያዩ መድረኮች ሲገልጡ እንደሚሰማው የሁሉም መድረሻ ግብ ወያኔን ማስወገድ ብቻ ሳይሆን በዐማራ ማኅበረሰብ ላይ ከእዚህ በፊት በዘር ጥላቻ ላይ ብቻ ተመስርተው ግድያ የፈፀሙ እና ኢትዮጵያን እንደ ሀገር የሚጠሉትን ሁሉ እንደሚፋለሙ ያሳስባሉ።በመጪው የእሁድ ስብሰባ ላይም እነኝህ ስሜቶች እንደሚንፀባረቁ ይጠበቃል።በዐማራ ማኅበረሰብ መደራጀት አለበት? ወይንስ የለበትም? የሚለው ክርክር በማኅበራዊ ሚድያ ላይ ይሰሙ የነበሩት ክርክሮች አሁን አሁን አይሰሙም።ከጥቂት ወራት በፊት በእዚህ ዙርያ የሚነሱት ክርክሮች የእየራሳቸውን ነጥቦች ሲያነሱ ይሰማ ነበር።



የዐማራ ማኅበረሰብ መደራጀት አለበት የሚሉት ወገኖች ሁለት ምክንያቶች ያነሳሉ እነርሱም የማኅበረሰቡ  ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታት በሕወሓት የደረሰበት ዘርን ያማከለ ጥቃት እና በሌሎች የስርዓቱ አጋሮች በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ያደረሱትን ጥቃት በአብነት ይጠቅሳሉ። ከእዚህ በተጨማሪም በመጪው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ስልጣን ላይ ዐማራውን ያገለለ የስልጣን ሽግግር ፈፅሞ የማይታሰብ መሆኑን አሁንም አበክረው ይመክራሉ።

የጥቅምት 27ቱ የሲያትል፣አሜሪካው ስብሰባ ባንድም ሆነ በሌላ መልኩ ከላይ የተነሱትን ነጥቦች ዙርያ የሚንፀባረቁበት መድረክ እንደሚሆን ይታሰባል።የማኅበረሰቡ ትግል እስከምን ድረስ ይሄዳል? በኢትዮጵያ የወደፊት ዕጣ ላይስ የሚኖረው ተፅኖ ምን አይነት ይሆናል? የሚፈጠረው መድረክ እራሱን ወደ ፖለቲካ ኃይል  ይቀይራል? ወይንስ ስብስብ ሆኖ ይቀጥላል? እና ሌሎች ጥያቄዎች ይነሳሉ።ከእዚሁ ጋር በተያያዘ ግን የማኅበረሰቡን የፖለቲካ አስተዋፅኦ በቀላሉ የሚታይ እንዳልሆነ የሚናገሩ ብዙዎች ናቸው። 

በሌላ በኩል ሳይነሳ የማይታለፈው ጉዳይ የማኅበረሰቡ ስብስቦች ላይ የሚነሱ አከራካሪ ጉዳዮች መኖራቸው ነው።ከእነዚህ ውስጥ ፍፁም ጫፍ የያዘ እና ማኅበረሰቡ ´´የእራሱ መንግስት ይኑረው´´ የሚለው ሃሳብ ድረስ ይሄዳል።የእዚህ አይነቶቹ ሃሳቦች እንደ መከራከርያ የሚያነሱት በአሁኑ የኢትዮጵያ ፖለቲካ አክራሪ እና ፅንፍ ካልተያዘ ´´በተቃራኒ´´ በኩል ያለውን ፅንፍ መመከት አይቻልም የሚል እሳቤ ይንፀባርቃል።ሆኖም ግን ይህ አስተሳሰብ በብዙዎች ዘንድ የእራሱ የሆነ ተቃርኖ ገጥሞታል። 

በሌላ በኩል ደግሞ የእዚህ አይነቱ የሃሳብ ክርክር ክስተት የአንድ ተቋም ጤነኛ ባህሪ መሆኑን የሚገልፁ አሉ። መከራከር፣የሃሳብ ፍትግያ እና ግጭቶች አስፈላጊ እና ወደ አንድ  ነጥብ የሚመሩ ተፈጥሯዊ የአንድ ተቋም የመመስረት ወይንም የመለወጥ የምልክት ሂደቶች ናቸው። እነኝህ ሂደቶች በመጪው እሁድ አይነት የፊት ለፊት ስብሰባዎች መፍትሄ እንዲያገኙ ይረዳል። 

በመጨረሻም የሲያትሉ ስብሰባ በቸልታ እንዳይታይ ያሚያደርገው አንዱ እና አይነተኛ ምክንያት በሺህ የሚቆጠር የዐማራው ማኅበረሰብ ብረት አንስቶ ከሕወሓት አምባገነን ስርዓት ጋር እየተፋለመ መሆኑ ነው።ስብሰባው ግን ከወጣት እስከ አዛውንት እና የሃይማኖት መሪዎች ሁሉ የሚገኙበት እና ከማኅበረሰቡ ጉዳይ እስከ ኢትዮጵያዊነት ሃገራዊ ጉዳይ እንደሚወሱበት ይጠበቃል። 


ጉዳያችን GUDAYACHN 

 www.gudayachn.com

Wednesday, November 2, 2016

ጥቅምት 23 የታሪካችን አካል (ቪድዮ)

ዛሬ ጥቅምት 23 ነው።እስካሁን አንድም ሐውልት ያልቆመላቸው ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ስላሴ የነገሱት የዛሬ 86 ዓመት ጥቅምት 23/1923 ዓም በአሁኑ አራዳ (ፒያሳ) የሚገኘው ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ነበር።ሃውልት ብቻ አይደለም በስማቸው የተሰየመውን ከዩንቨርሲቲ እስከ የካቲት 12 ሆስፒታል ስም እየደለዝን የእራሳችንን ታሪክ ለመፃፍ የሞከርን ጉደኞች አሁንም እኛው ነን።
ይህም የታሪካችን አካል ነው።

ንግስት መነን የመጀመርያ የልጃገረዶች ትምህርት ቤት መስራች፣የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል እና በኢየሩሳሌም ያሉ ገዳማት ያደርጉት አስተዋፅኦ ሁሉ የሚጠቀስ ታሪክ ነበራቸው።ከሁሉም የኢትዮጵያ ሴቶችን ንግስት መነን እኩልነትን ለማጠናከር የለፉ ነበሩ።ስለ ዓለም የሴቶች እኩልነት እናወራለን እንጂ የእኛዎቹን ፈላስፋዎች ማድነቅ አልፈጠረብንም።አንድ ቀን ይህንን ሁሉ ምስቅልቅል የሚያስተካክል እና ወደ እራሳችን ሀብት የሚመለከት ትውልድ ይነሳል።እስከዛው ድረስ ግን ለማያውቀው  ጠብታ ተጠራቅሞ ጋን ይሞላል እና እንዲህ የጠብታ ያህል እንነግራለን።



ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

በዐማራ ፖለቲካ ዙርያ የሚታየኝ እውነት እና ስጋት (የጉዳያችን አጭር ማስታወሻ)




ጉዳያችን /Gudayachn 
ጥቅምት 23/2009 ዓም 
====================
አንድን ነገር ፈርተነው ዝም ካልን አላዋቂ እንዲመራን መንገድ መክፈት ነው።ይህንን ጉዳይ የማነሳው አዲስ የውይይት ርዕስ ለመክፈት አይደለም።በፌስ ቡክ ላይ አንድ ግለሰብ ስለፃፈ/ስለፃፈች ወይንም ሶስት እና አራት ሰዎች ሃሳባቸውን ስላሰፈሩ ሃሳቡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ወይንም እንወክለዋለን ያሉት ሕዝብ ሃሳብ ነው ለማለትም አይደለም። ሃሳቦች ግን ከመጀመርያው ካልተነሱ ጊዜ በወሰዱ ቁጥር እየጠጠሩ እና ንግግሮች ሁሉ ሕግ ሆነው ሳይታወቅ ይቀራሉ።

ፖለቲካ መነሻ እና ግብ ከሌለው መውጫው ጭንቅ ነው። ፖለቲካ አስፍቶ የማየት አዕምሮ ላይ ካላረፈ አንድ ሰው ላይ ወጥታ  አጠገቧ ያለውን አንድ ቅንጣት ፀጉር ትልቅ ዛፍ አድርጋ አይታ ደን ውስጥ ነኝ ብላ እንደምታስብ ቅማልም በጠበበ መረጃ ላይ መመስረትን  ያመጣል። ፖለቲካ ልምድ እና ሙያም ይፈልጋል።ፖለቲካ በፍፁም ፍቅር እና የሰውን ልጅ ሁሉ የመውደድ ፀጋ ሳይታደሉ የሚገቡበት አይደለም።የሰውን ልጅ ሁሉ ሳይወዱ የሚገቡበት ፖለቲካ በአለማችን ላይ እንደተመለከትነው መጨረሻ ላይ የእራስን ጎሳ ወደማምለክ ይቀየርና ግቡ ´´ፋሽዝም እና ናዚዝም´´ ይሆናል። ስለዚህ ጥንቃቄ ይፈልጋል።

እውነታው  
=======
የዐማራ  ማኅበረሰብ ለሕወሐት ´እንደጠላት ተቆጥሮ በግልፅ እና በስውር ላለፉት 25 ዓመታት በተለየ መልኩ ተጠቅቷል።በሕወሓት ማኔፌሥቶ ውስጥ እንደተገለፀው በገዢ መደብነት ተጠቅሶ ቁጥር አንድ ጠላት ተብሏል።ላለፉት 25 ዓመታትም በሺህ የሚቆጠሩ በዐማራነታቸው ብቻ እና ብቻ ተጠቅሶ ተገድለዋል፣ከቤታቸው ተባረዋል፣በርካታ ስውር ጥቃቶች ተፈፅመዋል።እነኝህን ትውልድ፣ታሪክ እና እግዚአብሔር በጊዜው የሚፈርዱት ይሆናል።ይህ ማለት በሌላው ብሔር ላይ አልደረሰም ማለት አይደለም።በተለይ በዐማራው ላይ የተደረገው ግን ማኅበረሰቡን የስልጣን ስጋት ነው በሚል ብቻ ሳይሆን ከሰይጣናዊ ፍፁም ጥላቻ የተፈፀመ መሆኑ ነው።በሌላው ላይ የተፈፀመው  አንድ፣የተፈጥሮ ሃብቱን ለመቆጣጠር አልያም ለመብቱ በተነሳበት ወቅት ስልጣንን ለመጠበቅ በሚል ሕወሓት የወሰዳቸው እርምጃዎች ናቸው። በዐማራው ላይ የተወሰደው ግን ከእዚህ በተለየ ስልታዊነት ላይ የተመሰረተ ከፖለቲካ፣ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ዘርፎች ሁሉ የማስወገድ እና በመጨረሻም ወደ ማጥፋት የዞረ ተግባር ነው። ይህ በርካታ ማስረጃዎች ያሉት ያለፉት 25 ዓመታት እውነታ ነው።

ስጋት 
====
ከላይ የተጠቀሰው እውነታ በርካቶች ስለ ማኅበረሰቡ መብት፣ነፃነት (በኢትዮጵያ ውስጥ ያለ ነፃነት) እና እኩልነት ድምፃቸውን እያሰሙ ነው።ይህ ክስተቱ ያመጣው ሂደት ነው።ይህ ማለት ግን ብሶት በእራሱ ፖለቲካ አይሆንም።ብሶት ቁጭት እና የንዴት ማብረጃ ብሎ ያገኘውን ዕቃ ሁሉ የመወርወር ክፉ አባዜ ያስከትላል። ስለሆነም በዐማራ ማኅበረሰብ ዙርያ የሚነሱ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች መልሶ እራሱን ዐማራውን የሚያስከፋ እንዳይሆን ጥንቃቄ ይፈልጋል።የዐማራ ማኅበረሰብን ስነ ልቦና፣ብሔራዊ እና ዓለም አቀፋዊ የሞራል ልዕልናን ከግንዛቤ ያላስገባ ፖለቲካ መጨረሻ ላይ ፈረንጆቹ እንደሚሉት ወደ እራስ መተኮስ (fire back) ያስከትላል።ይህንን ለማለት ያስገደደኝ በማኅበራዊ ሚድያ ላይ አንድ ሰሞን በርካታ ተከታይ ስላገኙ ብቻ እራሳቸው የፖለቲካ ፕሮግራም አውጪ ቀጥለው ወክለነዋል ስለሚሉት ሕዝብ የወደፊት እጣ ለመወሰን የሚዳዱ ደፋሮች ስመለከት ነው።

ስለ ዐማራ ማኅበረሰብ እውነቱን የሚናገሩ በደሉ ስልታዊ መሆኑን በማስረጃ የሚያቀርቡ እና ይህ ለነገዋ ኢትዮጵያ አደጋ መሆኑን የሚያሳስቡ ሁሉ ክብር ይገባቸዋል።ይህንን በደልም አንስተው ቆርጠው ለመታገል የወሰኑም እውነተኞች እና ስለ ፍቅር የሚያደርጉት እንደሆነ የታመነ ነው።ከእዚህ አልፈው ይህንን ስሜት እየኮረኮሩ ስለ ዐማራ ነፃ መንግስት ለመስበክ የሚፈልጉ ግን ´´ሰከን በሉ´´ ማለት ተገቢ ነው። ፖለቲካ የዕቃ ዕቃ ጫወታ አይደለም።ፖለቲካ ሰፊ ልቦና እና አሁንም ልድገመው  በደልን ውጦ ሌላውን በፍፁም ፍቅር መውደድ ይፈልጋል።

የዐማራ ማኅበረሰብ የእረጅም ጊዜ የፖለቲካ ተሞክሮ አለው።ኢትዮጵያን ብሎ የሚኖረው ስለተመቸው እና ስላልተመቸው አይደለም።የዛሬ የሁላችንም ኢትዮጵያውያን መደህየት የነገ እንዳልሆነ ያምናል። ያጣነው መልካም መንግስት ነው።ይህንን ደግሞ በበደላችንን እያሰማን ወደ እኩል ኢትዮጵያ የሚወስደንን መንገድ እንከታለለን እንጂ በማኅበራዊ ሚድያ የሚመራን ሕዝብ አይደለንም።በእርግጠኝነት የእዚህ አይነቱ የዐማራ መንግስት የምትል አጀንዳ ማራገብ አንድ ወያኔ በውጭ ባለው ማኅበረሰብ ዘንድ ሌላ አጀንዳ ለመፍጠር ያሰባት ነች። አልያም አዲስ ነገር የፈጠሩ መስሏቸው ወይንም ጊዚያዊ የፖለቲካ አጀንዳ በማንሳት ጥሩ ስልት የፈጠሩ የመሰላቸው የሚያነሱት ነው።

ባጠቃላይ ግን ያኛውም ተባለ ይሄኛው ቁም ነገሩ የዐማራ ማኅበረሰብን ብሔራዊ እና ዓለም አቀፋዊ የሞራል ልዕልና ከኢትዮጵያዊነት ጋር ያለውን ቁርኝት የዐማራ መንግስት በሚል የፌስ ቡክ አጀንዳ አትጉዱት።በእርግጥ ይህ ሃሳብ በእራሱ ለመውቀስ ገና ነው ሊባል ይችላል።የእኛ ችግር ይህ ነው።ነገሮችን ከወዲሁ በእንጭጩ ሃሳቡ ካልተቀጨ ነገ የሚናገር የለም።እያየን ማለፍ መቼም ባህላችን ሆኗል።ስለዚህ ነው በደሉን አብረን እንጩህ፣ለነገዋ ኢትዮጵያ አብረን እንስራ ነገር ግን አጀንዳውን ወደተለየ መንገድ የሚወስዱትን ´´ሰከን በሉ´´ እንበል የምንለው።



ጉዳያችን GUDAYACHN

 www.gudayachn.com

Tuesday, November 1, 2016

Breaking News Ethiopia - Less than ten hours since PM introduces a new cabinet, there is heavy bomb blast in two places. ሰበር ዜና -ዛሬ ምሽት ባሕርዳር ላይ ሁለት ቦታ ቦንብ ፈንድቷል


(የአማርኛ ፅሁፍ ከስር ያንብቡ) 
It is just hours passed since Prime minister Hailemariam Dessalegn introduced his new cabinet to  parliament, two heavy bombs were blast in the second big city of Ethiopia, Bahirdar.

Ze-Habesha web-site quoting Muluqen Tesfaw, the writer of Amharic book called  ´´YE TIFAT ZEMEN´´ (an investigative journalism work on Amhara massacre for the last 25 years), disclosed the bomb attack was done after the government has failed to release the residents of the city from prison.The residents were sent to prison due to their participation of the recent home strike which could cease all business activities of the city.

According to the news, the warning was sent to concerned government bodies from the young group, demanding to release the prisoners with out any condition in 5 consecutive days. 

The two targeted places attacked by the bombs are: ´Kebele´ 03 residence place of high government officials and the municipal office of Bahrdar city. Even though attacked places were found in different part of the city, both bombs were blast at the same time. The number of casualties is not yet known. But the news confirm as Ambulances are still going and back from Hospitals and local health centres. 

(ከእዚህ በታች ያለው ፅሁፍ ከዘ-ሐበሻ ገፅ ላይ የተወሰደ ነው) 


ሰበር ዜና- የአማራ ወጣቶች በባሕር ዳር እርምጃ ወሰዱ፤

የዕለቱ ዜናዎች | Posted by: Zehabesha
  

ሙሉቀን ተስፋው

የህዝብን ጥያቄ ወደ ጎን በማሸሽ መልስ የማይሰጠው ወያኔና ብአዴን ትምህርት የሚወስዱበት እርምጃ በባህር ዳር ወጣቶች ተወሰደባቸው። ከቀናቶች በፊት የተለያዩ የማህበር ክፍሎችና ነጋዴዎች ከእስር እንዲለቀቁ የጠየቁት ወጣቶች ለ5 ቀን የሰጡት ማስጠንቀቂያ ምላሽ ባለማግኘቱ እርምጃ መወሰዳቸውን አስታወቁ። እርምጃውም ቀበሌ 03 በሚገኘው የባለስልጣኖች መኖሪያ ኪቢአድ ግቢ እና የባህር ዳር መዘጋጃ ቤት( ከተማ አተዳደር)በተመሳሳይ ሰአት ከምሽቱ 2 ሰዓት የቦንብ ፍንዳታ ተፈጽሟል። ይሄንን ተከትሎ አካባቢው ላይ ከፍተኛ የሆነ ውጥረት ከመንገሱም በላይ አምቡላንሶች ሲሯሯጡ ይታያል።

አሁንም ወጣቶቹ ይናገራሉ የታሰሩ ወንድሞቻችንና ነጋዴዎች እስካልተፈቱ ድረስ ይሄ ጥቃት በሰፊው እና በተጠናከረ ሁኔታ እንደሚካሄድ አስጠንቅቀዋል። ከዚህ በዃላ ሊደረግ የሚገባውን እርምጃና ማስጠንቀቂያ ከቀናቶች በዃላ ያስታውቃሉ።

ምንጭ =  ዘሀበሻ ድረ-ገፅ 

 http://www.zehabesha.com/amharic/archives/68307

ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።