ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, October 21, 2016

ህዝቡ ዲሽ ሊነቅሉ የሚመጡ የሕወሓት ወታደሮችን የመምታት ሙሉ መብት አለው።ንብረትን መከላከል የሞራል ግዴታ ነው!መረጃ የማግኘት መብት ዓለም አቀፍ ድንጋጌ ነው።

ጉዳያችን
ጥቅምት 12፣2009 ዓም
====================================
ዲሽ (የሳተላይት መቀበያ ሳህን)  የዓለም አቀፍ ዜናዎችን ከዓለም አቀፍ የዜና አውታሮች የምንከታተልበት የመገናኛ መሳርያ ነው።ሰሞኑን የሕወሓት ቅልብ የአጋዚ ሰራዊት እና ሚሊሻ በእየቤቱ እየገባ ዲሽ መንቀል እና መስበር መጀመሩ ተሰምቷል።የቴሌቭዥን ቻናል መቀበያ ዲሽ አንድ ኢትዮጵያዊ ለፍቶ ካገኘው ንብረት ውስጥ ዋጋ አውጥቶ የገዛው የግል ንብረቱ ነው።ዲሽ መስቀል እና ዓለም አቀፍ ዜናዎችን መከታተል ወንጀል አይደለም።

ዲሽ ሊነቅል የሚመጣ ማናቸውም ፖሊስ ሆነ ወታደር፣ካድሬ  መመታት አለበት።ሕዝብ ንብረቱን የመከላከል ሙሉ መብት አለው።በእዚህ ጉዳይ ላይ መወላወል አይገባም።ኢትዮጵያዊ ሁሉ ቤቱ መጥቶ ንብረቱን ሊሰብር የመጣን ማንኛውንም ሰው በግልም ሆነ በቡድን ማጥቃት  የሞራል ልዕልና ነው።ሃገርን መከላከል የግል ንብረትን ከመጠበቅ ይጀምራል።መረጃ የማግኘት ሙሉ መብት እንዳለህ/ እንዳለሽ ማወቅ አለብህ።መረጃ የማግኘት መብት  በዓለም አቀፍ ደረጃ የተደነገገ መብትም ነው። በእዚህ ጉዳይ አክትቪስቶች ህዝብን ማንቃት አለባቸው።የእዚህ አይነቱን ተግባር ሕዝብ አምርሮ እንዲታገል አለማድረግ ባርነትን እንዲለምድ ማበረታታት ነው።ስለሆነም በእዚህ ጉዳይ ላይ ሕዝብ አምርሮ ንብረቱን እንዲከላከል ማንቃት ከመገናኛ ብዙሃንም ብዙ ይጠበቃል።


ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...