ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Wednesday, October 12, 2016

ሰበር ዜና - የሩስያ እና የአሜሪካ ፍጥጫ ከፍተኛ ደረጃ ደርሷል

Photo = independent.co.uk 

ጉዳያችን/ Gudayachn
ጥቅምት 4/ 2009 ዓም 
=======================
የሩስያ እና የአሜሪካ ፍጥጫ ከፍተኛ ደረጃ ደርሷል።መገናኛ ብዙሃን ሶስተኛው የዓለም ጦርነት እና የሁለተኛው ቀዝቃዛ ጦርነት ጅማሮ ብለውታል። በሶርያ ጉዳይ ላይ መስማማት አለመቻላቸው እንደዋና የፍጥጫ መነሻ ይወሰድ እንጂ ጉዳዩ ሩስያ ወደ ምስራቅ የመስፋፋት ዝጋት እና የቻይና በምጣኔ ሀብት መለጠጥ የፈጠራቸው ስጋቶች ናቸው ።ላለፉት ወራት ሶስቱም አገሮች በከፍተኛ የሳይበር ጦርነት ላይ እንደነበሩ ተገልጧል።አሁን ጎንቶ የወጣው ፍጥጫ ግን የሩስያ እና የአሜሪካ ሲሆን የሚታየው ምክንያት የሶርያ ጉዳይ ሆኗል።

የፍጥጫውን ደረጃ ለመረዳት የሩስያው ፕሬዝዳንት ዛሬ ባለሥልጣኖቻቸውን ያዘዙትን ትዕዛዝ መመልከቱ በቂ ነው።በዛሬው እለት ፕሬዝዳንት ፑቲን ባለሥልጣኖቻቸው በውጭ ሀገር የሚገኙ ዘመዶቻቸውን ሁሉ ወደ ሀገር ቤት እንዲጠሩ ማዘዛቸውን ´´ዴይሊ ሜል´´ ´በድረ-ገፁ ገልጧል። ለእዚህ ደግሞ የተሰጠው ምክንያት ሩስያ ወደ ጦርነት የምትገባ መሆኑ ሲሆን ሩስያ በሌላ በኩል የኒኩለር አረሯን ወደ ፖላንድ ድንበር ማስጠጋቷ ተሰምቷል። (www.dailymail.co.uk Russia orders all officials to fly home any relatives living abroad, as tensions mount over the prospect of a global war

በጦርነቱ ወሬ ላይ የአሜሪካም ሆኑ የሩስያ መገናኛ ብዙሃን እያሟሟቁት ነው። ወደ ሀገራችን ጉዳይ እንምጣ እና በተባለው ፍጥነት ፍጥጫው ከመጣ በኢትዮጵያ ያለውን የኃይል አሰላለፍ ላይ ተፅኖ ይኖረዋል? የውጭ ፖሊሲዎች መቀያየር ይታይ ይሆን? ወይንስ እንደተለመደው የአንድ ሰሞን ወሬ ሆኖ ይቀራል።

ከእዚህ በታች ያለው አጭር ቪድዮ የውጥረቶቹ እድገቶች በያዝነው ዓመት ብቻ ያለውን ገፅታ ያሳያል።


ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

No comments:

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።