ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, December 11, 2015

የኦሮሞን ሕዝብ ከፅንፈኛ የእስልምና አቀንቃኞች እንታደግ! በኢትዮጵያዊነታቸው የፀኑ የክልሉ ተወላጅ ምሁራን ሕዝቡን ለመምራት መነሳት አለባቸው።


  •  የኦሮሞን ብሔር ከኢትዮጵያዊነቱ የማይለያይ ከፅንፈኛ የእስልምና እንቅስቃሴ የፀዳ መሪ ያስፈልገዋል።

እናትና አባቱ ጥረው ግረው አስተምረውት ደሙ በመንገድ ላይ እንደዋዛ የሚፈሰው ኢትዮጵያዊ የኦሮሞ ብሔር እንዴት ያሳዝናል? መብቱን በሰላማዊ መንገድ የጠየቀን ሕዝብ እንዴት የጥይት አረር ይሰጠዋል? ይህንን የፈፀሙ በሙሉ ይዋል ይደር እንጂ ሕዝብ ለፍርድ ማቅረቡ አይቀርም።

በኢትዮጵያ አርሲ፣ወለጋ ምዕራብ ሸዋ እና ሐረር ለሞቱት ኢትዮጵያውያን በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከዋሽንግተን እስከ ጀርመን ተቃውመው እየወጡ ነው።አሁን በስልጣን ላይ ያለው ስርዓት ችግሩን የመፍታት ስነ-ልቦናዊ፣ርዕዮተ አለማዊና ተቋማዊ ብቃት አንሶታል።በእዚህ ሁሉ መካከል ተቃውሞው የሚመራው በፌስ ቡክ እና ትዊተር ፎቶ ግራፍ እና ቁርጥራጭ ፊልሞችን በሚለጥፉ መሆኑ በእራሱ አደገኛ ነው።እንደ ጅማ ዞን ወጣ ባሉ፣አርሲ እና ባሌ አካባቢዎች በፅንፈኛ የእስልምና አመለካከት  የኦሮምኛ ተናጋሪውን ኢትዮጵያዊ የቁጣ ስሜት ተጠቅመው አካባቢውን ወዳልተፈለገ የፅንፍ ጫፍ ለመውሰድ የሚፈልጉ እንዳሉ ማንም የሚያውቀው ነው።ይህንን ጉዳይ እንዳላዩ ማለፍ ወይንም አሁን ትግሉን ለማደብዘዝ የሚነሳ ሃሳብ ነው ማለት በእራሱ አደገኛ ነው።ይህንን ሁኔታ እንዲያውም በውጭ የሚገኙ ነፃ ሚድያዎች ለሕዝብ መረጃውን በትክክል ማድረስ አለባቸው።እውነታው ሶስት ነው።
አንድ፣ኢህአዴግ ወያኔ ሕዝቡን በዘር ፖለትካ ከፍሎታል።
ሁለት፣ፅንፈኛ የእስልምና አቀንቃኞች በኦሮሞ ሕዝብ ተንጠላጥለው ኢትዮጵያን ከታሪካዊ ጠላቶቿ ጋር ለማጥፋት ይፈልጋሉ።
ሶስት፣አብዛኛው የኦሮሞ ተወላጅ ይህንን ፈፅሞ አይቀበልም።እነኝህን እውነታዎች ፈፅሞ ለስልት ሲባል መካድ አይቻልም።

ከአምስት እና ስድስት አመታት በፊት በእነኝህ አካባቢዎች በእምነታችን ለማይመስል ሰው ግብር መክፈል የለብንም የሚል እና በእምነታቸው መለየት ብቻ ለእረጅም ጊዜ እና ለትውልዶች በቡና ይዞታ ይኖሩ የነበሩ ከእድር እየተለዩ ሲባረሩ የነበሩ መሆኑን ለስራ ጅማን ባየሁበት ጊዜ ከአካባቢው የመጡ የኦሮሞ ብሔር ተወላጆች በሃዘን ሲናገሩ አስታውሳለሁ።ግብር መክፈልን ከእምነት ጋር ማያያዝ እንደ ኢትዮጵያ ባለች አገር ላይ ማንሳት የነማን ሃሳብ እንደሆነ ማሰብ ይችላል።

የኦሮሞን ሕዝብ ከፅንፈኛ የእስልምና አቀንቃኞች እንታደግ! የክልሉ ተወላጆች የማስተማር እና የመምራት ኃላፊነቱን የመውሰድ  ግዴታ አለባችሁ።

የኦሮምኛ ተናጋሪ ሕብረተስባችን በደረሰበት በደል ምክንያት እያሳየ ያለው የእንቅስቃሴ አቅጣጫ በፅንፈኞች እንዳይመራ መጠበቅ ያስፈልጋል። ፅንፈኞች ሁል ጊዜ ግባቸውን ለመምታት የሚያደርጉት አንድ  ነገር ነው።ይሄውም ሕዝቡን ከኢትዮጵያዊነት ስሜት መለየት ነው።ይህንን ተግባር ኢህአዴግ/ወያኔ በብዙ መንገድ ሲፈፅመው ላለፉት 24 አመታት ኖሯል።ይሄውም  የኢትዮጵያዊ ስሜቱን ቋንቋን መሰረት ባደረገ ፌድራል ስርዓት ይብሱን ቤንዚን ስያርከፈክፍበት እንደነበረ ይታወቃል።ትናንት ህዳር 30/2008 ዓም ለኢሳት ራድዮ ከወለጋ ሆሮ ጉድሩ ቃላቸውን የሰጡ የአካባቢው አዛንትም ይህንኑ እንዲህ በማለት አረጋግጠዋል:
 ''ስርዓቱ አንተ አማራ፣አንተ ኦሮሞ አንተ ትግሬ እያለ እየከፋፈለ እርሱ እንደዳኛ ሆኖ መቀመጥ እና መምራት ነው የሚፈልገው'' ነበር ያሉት።

የኦሮሞን ሕዝብ ለመምራት የምዳዱት ፅንፈኞቹ ግን በአንድ ደረጃ ኢህአዴግ/ህወሃትን ይበልጡታል።እነርሱ ኢትዮጵያዊነት የሚለውን ከሕዝቡ ስነ-ልቦና ለማውጣት የሚከተሉት መመርያ በቀጥታ ከኢትዮጵያ ጋር ቀጥተኛ ስልታዊ እና ታሪካዊ ጠላትነት ካላቸው ኃይሎች ጋር በገንዘብ፣በማቴርያል እና በሰው ኃይል በመታገዝም  ጭምር ስለሚንቀሳቀሱ ነው።ይህ ''የኢትይጵያ ታሪካዊ ጠላቶች'' የሚለው አባባል የደርግ አባባል የሚመስላቸው ከጅኦ-ፖለቲካ ሳይንስ እራሳቸውን ያገለሉ የዋሆች ይኖሩ ይሆናል።ነገር ግን እውነታ ነው።ምናልባት ኢህአዴግ/ህወሃት ከእነኝህ ኃይሎች ጋር የኢትዮጵያን ጥቅም አሳልፎ እየሰጠ ስለተመሳሰለ ቃሉ በኢትዮጵያ ራድዮ እና ቴሌቭዥን ስለማይሰማ የሉም ካላልን በቀር።ስለዚህ ይህ እንቅስቃሴ ኢትዮጵያዊ መልክ እንዲይዝ እና ከፅንፈኛ የእስልምና ኃይሎች እጅ እንዲወጣ  የክልሉ ተወላጆች ባላችሁ መንገድ ሁሉ ወጥታችሁ የማስተማር እና የመምራት ኃላፊነቱን የመውሰድ  ግዴታ አለባችሁ።


የኦሮምኛ ተናጋሪው ሕዝብ ከማንም በላይ ለኢትዮጵያ ቀድሞ መስዋዕትነት የከፈለ ሕዝብ ነው።አገራችን በአድዋ ጣልያንን ድል ስታደርግ ከወንድሞቹ ጋር የተዋጋ፣ኢትዮጵያ በሱማሌ ስትወረር በሚልሻነት አገር ያዳነ፣ በቀድሞ ሰራዊትም ሆነ በቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ዘመን በበርካታ የጦር አለቆቹ በከፍተኛ የአገር መሪነት የፕረዝዳንትነትን ቦታ ሁሉ ጨምሮ (/ መንግስቱን እና አፄ ምንሊክን መጥቀስ ይቻላል) ኢትዮጵያን ስመ ጥር ያደረገ ኢትዮጵያዊ ነው። ይህንን ሕዝብ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች እንዲመራው ያዘጋጁለት ፅንፈኛ የእስልምና እንቅስቃሴ እንዲሆን ብዙ ጥረቶች ተደርገዋል።አሁንም ሕዝቡን የመምራት ሚና የሚወስድ ከፅንፈኛ እስልምና የፀዳ እና አብሮ በመኖር የሚያምን መሪ በፍጥነት መታየት አለበት።ይህንን አመራር ደግሞ የመደገፍ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ግዴታ ነው።አንዳንዶች በውጭ አገራት ጥገኝነት የመጡ ኢትዮጵያውያን ወጣት የኦሮምኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ አልይዝም ሲሉ ይገረማሉ።ነገር ግን ያላስተዋሉት ነገር ይህ ኢትዮጵያዊነትን የማስጠላት ሥራ በኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች በእጅ አዙር የተደገፈ እና ለእረጅም ጊዜ ሲሰራበት የነበረ መሆኑን ነው።ፍቅር ያሸንፋል! እና ሚልዮኖች የኦሮምኛ ተናጋሪ ወንድሞቻችንን ልብ ከኢትዮጵያዊነት የሚያሸፍት ምንም አይነት ኃይል የለም።ነገር ግን ዛሬ ላይ የክልሉ ተወላጆች በኢትዮጵያዊነታቸው የፀኑቱ የመምራት ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ካልተነሱ አደጋ አለው።ዝምታ ይብቃ! በስህተት ህዝብን ከኢትዮጵያዊነት ለመለየት የሚሞክረውን ለመቸውም ጊዜ ቢሆን ወደ እራሱ ካልተመለሰ የጥፋት እና የባዕዳን ፈረስ ከመሆን ስለማይድን ''አካፋን አካፋ'' የማለት ባህል መዳበር አለበት።


ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com
ታህሳስ 1/2008 ዓም (December 11/2015)

No comments: