ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Wednesday, November 11, 2015

የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! እባክህ ከስልጣን አውርደን? (የጉዳያችን ማስታወሻ)




''መሬት ፖሊሲ መሬት ፖሊሲ እያልን ስንት ዓመት አወራን አንዱም ተግባር ላይ አልዋለም'' አቶ ኃይለማርያም በቅርቡ የተናገሩት። ይህ ማለት እኛ አቅም የለንም ብቃታችን ይህ ነው ስንት ዓመት አልነው አልነው አንዳች ፍሬ የለንም  እናም የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ እባክህ በአንድነት ተነስና ከስልጣን አውርደን!!

'' ሙስና ሙስና ትላላችሁ ከእዚህ እንደወጣችሁ ሁላችሁም ወደ ኔት ወርካችሁ ነው የምትሄዱት'' አቶ ሃይለማርያም በቅርቡ የተናገሩት። ይህ ማለት የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ እባክህ በአንድነት ተነስና ከስልጣን አውርደን!!

''ስምንት ሚልዮን ሕዝብ ተራበ ማለት ምንድነች ይህ ማለት ከኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር አንፃር 80 ምናምን ሕዝብ ደህና ነው ማለት ነው'' ዶ/ር ቴዎድሮስ ለቪኦኤ አማርኛው አገልግሎት በቅርቡ የተናገሩት። ይህ ማለት እኛን አይራበን እንጂ ስምንት ሚልዮን ሕዝብ ረሃብ ብዙም ከቁብ አንቆጥረውም ስለሆነም ጥጋባችንን አይተህ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! እባክህ በአንድነት ተነስና ከስልጣን አውርደን!! 

''ድርቅ ካሊፎርንያ አሜሪካንም አለ'' ብለው አቶ ሃይለማርያም ሲናገሩ   እበላ ባይ ጭብጨባ ቹአ!! ቹአ!! ቹአ !!! 

''አውስትራሊያም ድርቅ አለ" ሲጨበጨብ ባሰባቸው አቶ ሃይለማርያም ጭብጨባው ቀለጠ።የአሜሪካ ኤምባሲ ሰራተኞች እኛ ድርቅ መታን ስንባል ከንፈር እንደመምጠጥ ያጨበጭባሉ እንዴ? ማለት ጀመሩ። 

አቶ ሃይለማርያም ቀጠሉ '' እኛ ብንራብም አንድም ሕፃን ወደ 'ፊዲንግ ሴንተር' አላስገባንም'' ጭብጨባው ቀለጠ።ተሰብሳቢ ጀግናው መንግስታችን ሕፃናት ተርበው ቢንከላወሱም እናት የልጇን ገላ አቅፋ ብታለቅስም መንግስታችን ግን በፅናቱ እና ከቀደሙት ታጋዮች በወረሰው ውርስ ወደ ''ፊዲንግ ሴንተር'' አላስገባም ሲሉ ተሰብሳቢዎቹ ደጋግመው አጨበጨቡ። አንደምታው ግን እኛ ጥጋባችን ልኩን አጥቷል።ሕፃናት የመመገቢያ ካምፕ ባለማስገባት በመናገር እና ቢቢሲ በቀን 2 ሕፃናት እየሞቱ ያለበት መንደር ወሎ ውስጥ አገኘሁ ብሎ አለምን ማሳዘኑን ጆሮ ዳባ ልበስ በማለታችን የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ እባክህ በአንድነት ተነስና ከስልጣን አውርደን!!

''ለስድስት ባለስልጣናት ለእያንዳንዳቸው ከአንድ ሚልዮን ዶላር በሚበልጥ ወጪ ወይንም በ25 ሚልዮን ዶላር ቤቶች ሰርተን እያተናቀቅን ነው። ቤቶቹ ሲያልቁ የባለስልጣናቱ የግል ገንዘብ ነው የሚሆነው።ይህ ለመጀመርያ ነው እንጂ ሌሎች ባለስልጣናትም እደላው ይቀጥላል'' ሸገር የግንባታ ባለስልጣን መሰል የሚል ስም ያላቸውን ባለስልጣን ጠይቆ ያሰራጨው ዜና። ትርጉሙ ኢትዮጵያ ብትራብም፣ለአባይ ቦንድ ከጉልት ቸርቻሪ እና ከድሀ ገበሬ እያስለቀስን ብንሰበስብም፣ እኛ ግን በ25 ሚልዮን ብር ቤት እየሰራን ኦባማ የማይኖሩበት ቤት ውስጥ ለመኖር አቅደናል።ለመሆኑ  25 ሚልዮን ብር ማለት ምን ማለት ነው?

25 ሚልዮን በ6ቱ ባለስልጣናት አባዙት 150 ሚልዮን ማለት ነው። እናም ይህ ብር ማለት ለ100 ሺህ መምህራንበነፍስ ወከፍ  የ1500 ብር የደሞዝ ጭማሪ ለእያንዳንዳቸው ይደርሳቸው ነበር ማለት ነው።
150 ሚልዮን ብር ማለት አዲስ አበባ ከ300 በላይ  ዘመናዊ አውቶብሶችን በአንድ ጊዜ ልታገኝ ትችል ነበር።
150 ሚልዮን ብር ማለት 15ሺህ የጎዳና ተዳዳሪዎች በዓመት 10ሺ ብር ለእያንዳንዳቸው በጀት ተይዞ በአንድ ሙያ ማሰልጠንና ከጎዳና ሕይወት ማውጣት ይቻል ነበር ማለት ነው።

በመሆኑም ጥጋባችን ልክ እንደሌለው አየህ? እናም  የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! እባክህ በአንድነት ተነሳ እና ከስልጣን አውርደን!

ለበአዴን በዓል ብለን 300 ሚልዮን ብር ለድግስ እያጠፋን ነው እና  የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! እባክህ በአንድነት ተነሳ እና ከስልጣን አውርደን?!

ምን ይሄ ብቻ ለህወሃት በዓል ማክበርያ የሱዳንና የሌሎች አካባቢ አገራት መሪዎች በአይሮፕላን የማንሸራሸር ወጪ ጨምሮ ከእዚች ድሃ አገር ላይ ብዙ መቶ ሚልዮን ብር አውጥተን አክብረናልና  የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! እባክህ በአንድነት ተነሳ እና ከስልጣን አውርደን!

እንግዲህ ነገርንህ።ምን አይነት የነቀዘ ሥራ እንደምንሰራ! እኔ በጠቅላይ ሚኒስትርነት የጠቀመጥኩት ሃይለማርያም ከእራሴ ጀምሮ ለምንም የምንረባ አደለንም ብዬ ነገርኩህ ስለሆነም የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! እባክህ በአንድነት ተነሳ እና ከስልጣን አውርደን! የጦር ሠራዊቱም ዝም አትበለን ተነስና አውርደን! እኛ ከተሰቀልንበት ለመውረድ ፈራን! አውርደን! አውርዱን! ጨክናችሁ ዝም አትበሉን። ሳናውቀው እላይ ተሰቅለን ቁልቁል ስናየው የመሬቱ እርቀት አስፈራን።የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ እባክህ በአንድነት ተነስና ቀስ ብለህ አውርደን!?


ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG
ህዳር 1/2008 ዓም (Nov.11/2015)
www.gudayachn.com 

No comments:

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።