ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, October 7, 2014

''እናመሰግናለን አሜሪካ!'' Thank you America! ኢትዮጵያውያን ዛሬ በዋሽግተን ዲሲ በሰልፍ ወጥተው ያሰሙት ድምፅ።(የጉዳያችን አጭር ጥንቅር)



ኢትዮጵያውያን ዛሬ መስከረም  27/2007 ዓም (ኦክቶበር 7/2014) ዋሽግተን ላይ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር (ስቴት ዲፓርትመንት ) ፊት ለፊት ተሰለፉ።ሰልፉ ባለፈው በዋሽግተን በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኢትዮጵያውያን ላይ የተኮሰውን የኤምባሲ ሰራተኛ ከሀገር በማስወጣቷ  አሜሪካንን ለማመስገን ሲሆን በሰልፉ ላይ ግለሰቡ የተኮሰበት ሽጉጥ አሁንም በኤምባሲው ውስጥ መገኘቱ እና ምርመራው ወደ አምባሳደር ግርማም እንዲዞር ይጠይቃል።በሌላ በኩል በወገኖቹ ላይ የተኮሰው ግለሰብን በመደገፍ እና ወደ ኤምባሲ የገቡትን ተቃዋሚዎች በመቃወም  የተሰለፉትን ከዋሽግተን አትዮጵያ ኤምባሲ እና ከሌሎች ቦታዎች የአውቶብስ ተከፍሎላቸው የመጡ ሰልፈኞች ታይተዋል።በተለይ የስርዓቱ ደጋፊዎች ተሰላፊዎች ለመፈክር መፃፍያ እና ለአውቶብስ ከ2000 ዶላር በላይ ወጪ መደረጉን መረጃ እንደደረሳቸው በተቃዋሚ በኩል ከተሰለፉ ኢትዮጵያውያን ለኢትዮጵያ ወቅታዊ የመወያያ መድረክ (ECADF) የቀጥታ ስርጭት ገልፀዋል።

በሰልፈኞች ላይ የተኮሰውን ደግፎ የሚሰለፍ የሰው ልጅ ይኖራል ብለው ያልገመቱት  የአሜሪካ የስቴት ዲፓርትመንት ሰራተኞች በወገኖቹ ላይ የተኮሰውን ግለሰብ በመደገፍ የወጡትን በመገረም ተመልክተዋቸዋል።
በአሜሪካ ሕግ ጠለላ ውስጥ ያለ ሰው እንዲህ በወገኖቹ ላይ የተኮሰ ሰውን ደግፎ ይወጣል  ብለው አሜሪካኖቹ ፈፅመው ያልገመቱት የስቴት ዲፓርትመንት ሰራተኞች ቢገረሙ አይገርምም።በነገራችን ላይ  በወገኖቹ ላይ የተኮሰው የኤምባሲ ሰራተኛ ላይ የአሜሪካ አቃቢ ሕግ የክስ ወረቀት ማውጣቱን ዛሬ ''ዘሀበሻ'' በድረ-ገፁ ገልጧል።

በመጨረሻም ሰልፈኞቹ በመጪው ቅዳሜ የዓለም ባንክ ፊት ለፊት ለሌላ ሰልፍ ለመገናኘት ተቀጣጥረው ተለያይተዋል።በዓለም ባንክ ፊት ለፊት በመጪው ቅዳሜ የሚደረገውን ሰልፍ ዓላማ ለኢትዮጵያ ወቅታዊ የመወያያ መድረክ (ECADF)  የገለፁት አንድ የሰልፉ አስተባባሪ እንደተናገሩት '' እኛ ለኢትዮጵያ ብድር አይሰጥ አንልም።ብድሩ ይሰጥ። ነገር ግን ወያኔ እጅ እንዳይገባ እና ለሙስና እንዳይጋለጥ ከፍተኛ ቁጥጥር ይደረግ'' የሚል ጥያቄ ነው ለዓለም ባንክ  የምናቀርበው ብለዋል።


ጉዳያችን
መስከረም  27/2007 ዓም (ኦክቶበር 7/2014)

No comments: