ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, May 23, 2014

ኤርትራ 23 የመከራ እና የፍዳ ዓመታት - አቶ ኢሳያስ በኤርትራውያን ''በነጠላ ጫማ የገባ ሌላ ደርግ'' የሚል ስም ተሰጥቷቸዋል።በሺህ ለሚቆጠሩ በግፍ ለታሰሩ ማሳያ የሆነችው ከአስር ዓመት በላይ ካለፍርድ በኤርትራ እስር ቤት የምትማቅቀው አስቴር ዮሐንስ ማን ነች? (ቪድዮ)

ኤርትራ የዛሬ 23 ዓመት ከኢትዮጵያ መነጠሏ ቢነገርም አዲስ የመከራ እና የስቃይ ዘመን እንጂ ለሕዝቡ አንዳች ለውጥ አለማግኘቱ የአደባባይ ምስጢር ነው። ቀድሞውንም ቢሆን የመገንጠል እና የብሔር ጥያቄን የችግሮች ሁሉ መፍትሄ አድርጎ የሚወስደው የአቶ ኢሳይስ እና አቶ መለስ የተሳሳተ የፖለቲካ እይታ ዛሬም ድረስ ለብዙ ሺዎች ስደት፣እስር እና ጉስቁልና ምክንያት ሆኗል። ጥቂት የስርዓቱ አቀንቃኞች ግን ዛሬም አስመራ እና አዲስ አበባ ላይ የግንቦት ወር በዓል ለማክበር ሽር ጉድ እያሉ ነው።

ፀጥ ለጥ አድርገው ለመግዛት የሚያስቡት አቶ ኢሳያስ አፈወርቅ ከደርዘን በላይ የሚሆኑ አብረዋቸው በረሃ የነበሩ ወዳጆቻቸውን እና  ሌሎች ሺዎችን በእስር ቤት አጉረው፣ በመቶ ሺዎችን ደግሞ በሊብያ፣በግብፅ፣በሱዳን እና በየመን ሀገር ጥለው እንዲሄዱ አድርገው፣ዛሬም የግንቦት 16 በዓል ሊያከብሩ አስመራ ላይ ሽር ጉድ እያሉ ነው።የኤርትራ እናቶች ግን አንድ ኩንታል ጤፍ 10 ሺህ ናቅፋ እየከፈሉ ልጆቻቸውን መመገብ አቅቷቸው ተቀምጠዋል።

በደርግ ዘመን ሻብያ አስመራን  በከበበት፣ህወሓት ትግራይን ከመላው ኢትዮጵያ ነጥሎ በያዘበት 1982 ዓም ምንም አይነት የመንገድ ትራንስፖርት ከመሃል ሀገር ወደ አስመራ ለመውሰድ የማይቻልበት ሁኔታ ነበር። የአስመራ ሕዝብ ግን ከመሰረታዊ የኑሮ ሸቀጥ ጀምሮ እስከ ጤፍ እና ልዩ ልዩ ጥራጥሬ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደሌሎች ሃገራት የሚያደርገውን ካርጎ በረራ እየሰረዘ  የአቅርቦት ዋጋው አስመራ ላይ  ከአዲስ አበባ ብዙም የተለየ እንዳይሆን ለማድረግ ትልቅ ወጪ የጠየቀ ሥራ ይሰራ እንደነበር በወቅቱ በአየር መንገዱ ሰራተኛ የተናገሩትን አስታውሳለሁ።ይህ ደግሞ የአንድ መንግስት ግዴታ ነው እና ደርግ አሁን አስመራ ካለው የኑሮ ውድነት በማይገናኝ መልኩ አቅርቦቱን በቀበሌ እንዲዳረስ ያደርግ ነበር። ዛሬ አቶ ኢሳያስ ይህንን ማድረግ አልቻሉም።የስሕተታቸው መሸፈኛ ማሰር፣መግደል እና ማሰደድ ሆኗል።
ዛሬ በኤርትራ መፃኢው ምን እንደሆነ የማያውቅ ግን በገዥው እንደ ህዝቡ አጠራር ''በነጠላ ጫማ የገባው ሌላው ደርግ'' አማካይነት ማንነቱን ያጣው ሕዝብ ዛሬም የሰሚ ያለህ እያለ ነው።ለእዚህ ሁሉ አብነት እናንሳ አስቴርን። በሺህ ለሚቆጠሩ በግፍ ለታሰሩ ማሳያ የሆነችው  ከአስር ዓመት በላይ ካለፍርድ በኤርትራ እስር ቤት የምትማቅቀው አስቴር ዮሐንስ ማን ነች? ቪድዮውን ይከታተሉ።



ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

No comments:

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።