ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, November 8, 2013

''የኢትዮጵያ ባንዲራ የት ሄደ?'' (ቪድዮ 1) እና አይዟችሁ ባይ የሌላቸው የኢትዮጵያ ታዳጊ ልጆች ስደት (ቪድዮ 2)

ቪድዮ 1


ቪድዮ 2

በሳውዲ ላለው የኢትዮጵያውያን አዲሱ ሰቆቃ ''የኢትዮጵያ መንግስት ምን ያድርግ?'' ለምትሉ

ህገ መንግስቱ አንቀጽ 33 ''የዜግነት መብቶች'' በሚለው አንቀፅ ስር

ተራ ቁጥር 2/ . ''ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ የኢትዮጵያ ዜግነት በሕግ የሚያስገኘውን መብት ጥበቃና ጥቅም የማግኘት መብት አለው'' ይላል።ይህ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚስዮኖች ኢትዮጵያውያንን በውጭ የሚያስተናግዱበት አንዱ እና መሪ ሕግ ነው።
በሳውዲ አረብያ መንግስት ሰሞኑን በሚፈፀመው ድርጊት ዙርያ መንግስት በትንሹ ሊያደርጋቸው የሚገቡ ሶስት ትንንሽ ስራዎች ነበሩ።

1/ ስለ ጉዳዩ ዝርዝር መረጃ ከስፍራው ለኢትዮጵያ ሕዝብ መግለፅ፣

2/ በአዲስ አበባ የሚገኘው የሳውዲ አምባሣደርን ጠርቶ ማብራርያ መጠየቅ እና

3/ ልዩ ልዑክ ወደ ሳውዲ ልኮ ከከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ተነጋግሮ ጊዝያዊ የማግባብያ ሃሳቦች አቅርቦ የዜጎቹን መብት ማክበር።አንዳቸውም አልተሰሩም።

አንድ መንግስት በሥራ ላይ ነው (functional) የሚባለው እኮ በመጀመርያ የሀገሩን ዜጎች መብት ማስከበር ሲችል ነው።ይህ የሉአላዊ ነትም ጥያቄ ነው።በጣም አሳፋሪ ነው።ማንም ሀገር ዜጋው በውጭ ሀገር በከፍተኛ ወንጀል ተከሶ ጥፋተኛነቱ ተረጋግጦም ቢሆን ፍርድ ቤትም ሄዶ አምባሳደሩ ከጎኑ ይገኛል። የሀገሮችን የዲፕሎማሲ ግንኙነት መሰረት የጣለው በፈረንጆቹ አቆጣጠር 1961 ዓም ቬና ኦስትሪያ ላይ የተፈረመው ''የቬና ኮንቬሽን'' (venna convention) ተብሎ የሚታወቀው ዓለም አቀፍ ሕግ በራሱ አንቀጽ 36 ላይ ''ማንኛውም የውጭ ሀገር ዜጋን የሌላ ሀገር ዜጋ በጥፋተኝነቱ ቢያስረው ለሀገሩ ቆንስላ ፖሊስ እራሱ የት እና ለምን እንዳሰረው ፋክስ ማድረግ አለበት'' ብሎ ያዛል።መንግስታችን ይህንን ሁሉ አሳልፎ ሰጠ ማለት ሉዓላውነቴን አላስከበረም ሥራ ላይ አይደለም ወደሚል ድምዳሜ ያደርሳል።እጅግ አሳዛኝ ሥራ እየተሰራ ነው።ያቃጥላል። የቬና ኮንቬንሽን አንቀጽ 36 የእንግሊዝኛውን ቃል ተመልከቱት Article 36. ''Foreign nationals who are arrested or detained be given notice "without delay" of their right to have their embassy or consulate notified of that arrest. If the detained foreign national so requests, the police must fax that notice to the embassy or consulate, which can then check up on the person. The notice to the consulate can be as simple as a fax, giving the person's name, the place of arrest, and, if possible, something about the reason for the arrest or detention.'' http://en.wikipedia.org/.


No comments:

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።