ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Saturday, November 23, 2013

በዓለም ላይ በሳውዳረብያ በወገኖቻችን ላይ የደረሰውን ሰቆቃ ለመቃወም ሰልፍ የከለከለች ብቸኛ ሀገር-ኢትዮጵያ ነች። ይህ እንቅልፍ ያስወስዳል?

አዲስ አበባ ፌድራል ፖሊስ የሳውዲን መንግስት ለመቃወም ሰልፍ የወጡትን ሲደበድብ 

በዓለም ላይ በሳውዳረብያ በወገኖቻችን ላይ የደረሰውን ሰቆቃ ለመቃወም ሰልፍ የከለከለች ብቸኛ ሀገር-ኢትዮጵያ ነች።
ኢትዮጵያውያን በሳውዲ አረብያ በወገኖቻችን ላይ የደረሰውን ሰቆቃ አስመልክተው

ሰሜን አሜሪካ 

 - የተለያዩ ግዛቶች

 በአውሮፓ-

በጀርመን፣

እንግሊዝ፣

ጣልያን፣

ስዊድን፣

ኖርዌይ፣

 ካናዳ-

የተለያዩ ግዛቶች 

 አውስትራሊያ


መካከለኛው ምስራቅ 

- እስራኤል፣
- ቤሩት 

አፍሪካ 

 ደቡብ አፍሪካ፣

 ዑጋንዳ ፣

እስያ 

 ደቡብ ኮርያ፣

 በሚገኙ የሳውዳረብያ ኤምባሲ ፊት ለፊት ሰልፍ አድርገዋል።በለቅሶ በቁጭት እንባ ተራጭተዋል።ኤርትራውያን ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን አብረው ተሰልፈው ተላቅሰዋል ቁጣቸውን ገልፀዋል።

ቀሪ ሰልፎች ለምሳሌ በቤልጅየም ብራስልስ እና ሌሎችም ሀገሮች ይቀጥላሉ።
በዓለም ላይ የሳውዲን መንግስት ተቃውመው ዜጎች ሰልፍ እንዳይወጡ የከለከለች ብቸኛ ሀገር የጉዳዩ ባለቤት ኢትዮጵያ ብቻ ነች።ሌላ ማንም ሀገር አልከለከለም።

ኢትዮጵያ የሳውዲን ኢ-ሰብአዊ ድርጊት ተቃውመው ሰልፍ የወጡ እንቡጥ እና ለጋ ወጣቶችን፣አረጋውያንን፣አዛውንቶችን በፖሊስ እየደበደበች ብዙዎችን አካለ ስንኩል አደረገች።የቀሩትን  ሰልፉ የተደረገበት ቀን ሳትውል ሳታድር ወደ እስር ቤት ወረወረች።ይህንን የሚቀበል እንዴት አይነት ህሊና ነው?
ኢህአዲግ-ወያኔዎች ሆይ! ይህ ጠረንጴዛችሁ ላይ ያለ ያልተመለሰ ምን ጊዜም ልንረሳው የማንችለው ግን መልስ የሚሻ አጀንዳ ነው።

ጉዳያችን 

ህዳር/ 2006 ዓም 

No comments:

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።