ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, December 7, 2012

“መለስ ከመቃብራቸው እየገዙ ነው። ግን ይህ እስከመቼ ይዘልቅ ይሆን?..''መለስ በሌለበት ህዋሃት አንጎሉን አጥቷል'' - ሬኔ ለፎንት (ቃለ ምልልሱን ያዳምጡ)

ሬኔ ለፎንት በ 1960ዎቹ ጀምሮ ከ ሳሃራ በታች በተለይ ስለ አፍሪካ ቀንድ በመፃፍ የታወቁ ናቸው። በ እዚሁ የ አፍሪካ ቀንድ ጉዳይ ለ ታዋቂዎቹ የ ፈረንሳይ ጋዜጦች ''ለሞንድ''(Le Monde)፣''ለሞንድ ዲፕሎማቲክ'' (Le Monde diplomatique) እና ለ  ''ኖቭል ኦብሰርቫቱር ''(Le Nouvel Observateur) በ ሪፖርተርነት ሰርተዋል። በ 1975 ዓም ''Ethiopia: an heretical revolution'' የተሰኘ መፅሐፍ ፅፈዋል።
መፅሐፉን በ እዚህ ሊንክ ከ ''አማዞን'' ማዘዝ ይችላሉ።
(http://books.google.no/books?vid=ISBN0862321549&redir_esc=y)

ሬኔ ለፎንት ኢትዮጵያን በተመለከተ ለ አሜሪካ ድምፅ ራድዮ የ አማርኛው አገልግሎት  በ እዚህ ሳምንት  ጥልቅ ትንተና ሰጥተዋል።በ ኢትዮጵያ ጉዳይ ከ ሰላሳ አመት ሲያጠና የነበረ ሰው የሚናገራቸው ነገሮችን ማቃለል የሚቻል አይመስለኝም።ሬኔ ለፎንት በ እዚህ መግለጫቸው ''መለስ በሌለበት ህዋሃት አንጎሉን አጥቷል'' ብለዋል ።ስለ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች ሹመት፣ስለ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚ፣ስለ መጪው የ ኢትዮጵያ ፖለቲካ ወዘተ አንስተዋል።
 ከእዚህ: በታች ያለውን ሊንክተጭነው ቃለምልልሱን:ያዳምጡ።(ሁለቱን ቃለመጠይቆች ለማዳመጥ ሊንኩን ከከፈቱ በኋላ  ማጫወቻዎች በተራ ይጫኑ) :-

ክፍልአንድ
 http://amharic.voanews.com/content/meles-rules-from-beyond-the-grave-part-1-12-04-12/1558576.html

ክፍል ሁለት 
http://amharic.voanews.com/content/rene-lefort-voa-peter-heinlein-part-2/1559339.html

 


No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...