ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, September 21, 2012

አቶ ኃይለማርያምን'' አቃቢ ግንቦት ሃያውያን'' ካስቸገሩዋቸው ዶ/ር ነጋሶ በ ሄዱበት መንገድ...

አቶ ኃይለማርያምን'' አቃቢ ግንቦት ሃያውያን'' ካስቸገሩዋቸው ዶ/ር ነጋሶ በ ሄዱበት መንገድ ወደ ኢህአዲግ ተቃዋሚነት መቀየራቸው ላይቀር ይችላል።(ቪድዮ፡ የዛሬውን የ አቶ ሃይለማርያም ቃለመሃላ እና ንግግር)
በዛሬው ዓርብ መስከረም 11/2005ዓም የ አቶ ሃይለ ማርያም የጠቅላይ ሚኒስትርነት ሹመት  ምክር ቤት (99.6% ኢህአዲግ በሆነበት ምክርቤት )  ቀርቦ ጸድቋል።የ አቶ ሃይለ ማርያም ደሳለኝ ጠቅላይ ሚኒስትርነትን ምክርቤቱ እንዲያጸድቅ አቶ አባ ዱላ የጠየቁት በማጨብጨብ ሲሆን የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነቱን የ አቶ መኮንንን ግን ድምጽ እንዲሰጥበት እጅ እንዲወጣ በመጠየቅ ነበር።
  • ህወሃት ከጠቅላይ ሚኒስትርነቱ ቦታ ታዋቂው የ ምጣኔ ሀብት ጠቢብ አዳም ስሚዝ ''የማይታዩ እጆች'' ብሎ እንደ ሚጠራው የ ምጣኔ ሃብት አካላት  በ እርግጥም ከ እይታ ተሰውረዋል።
  • አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ዛሬ በንግግራቸው  ደፈር ብለዋል፣
  • ባለፈው ቅዳሜ¨ምደባ¨ ያሉትን የጠቅላይ ሚኒስትርነት ስልጣንን ዛሬ ¨ታላቅ ዕድል¨ ብለውታል፣
  •  ኢትዮዽያን ሲጠሩዋትም  አምሮባቸዋል። ''ኢትዮዽያችን!'' ነው ያሉት።
  • የትምህርት ጥራት አንስተዋል። ከ ዩንቨርስቲ አካባቢ መምጣታቸው ስለ ዩንቨርስቲ፣ምርምር፣ሳይንሳዊ አሰራር ወዘተ ያስጨነቃቸው እና ሾላ ድፍን አሰራር እንዳስመረራቸው ያስታውቃሉ፣
  •  የ ኢንዱስትሪውን ወሳኝነት ተወስቷል።የ ከተሞች መሰረታዊ ችግርን ፣የ ቤት ችግር  መፈታት ያለበት መሆኑን፣የ መንገድ ስራው፣የ ሃይል ማመንጫ ወዘተ እንደሳቸው አገላለፅ  ¨ጥርሳችንን ነክሰን¨መፈጸም አለብን ብለዋል፣
  •  ሙስናን እና ኪራይ ሰብሳቢነት ትልቅ እንቅፋት ነው በተለይ ከ መሬት ጋር የተያያዘ ጉዳይ መታየት አለበት ብለዋል፣
  •  የፍህ ስርዓቱን በተመለከተ ¨የ ፖሊስ፣የ ፍትህ አካል ሁሉ በ አግባቡ አገልግሎት መስጠት ይገባቸዋል።በ አንዳንድ አካባቢዎች በ ሙስናና ብልሹ ስነ ምግባር አካባቢ የሚፈጠሩ ችግሮች መፈታት እንዳለባቸው ሊሰመርበት ይገባል¨ብለዋል፣
  • ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋርም ተባብረን እንሰራለን የሚል ቃል አክለዋል።
የዛሬው ክንውን በ ኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ ትልቅ ክስተት ባይባልም እንደ እኔ አመለካከት አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ:-

  • ምክንያታዊነትን(rational) ከ ፓርቲ አባልነት አስቀድመው ውሳኔ መስጠት ከቻሉ፣
  • ፍትህን ለማስፈን ቆርጠው ከተነሱ፣
  • የ አባትነት ባህሪ  የተላበሰ ሁሉን ዜጋ እኩል ማየትን ገንዘብ ካደረጉ፣
  • ሃይማኖታዊ ጉዳዮችን ለ ሃይማኖቱ ሰዎች ብቻ ከተዉ፣
  • ሙስናን በድፍረት ነቅለው ታሪክ መስራት ከቻሉ ፣
  • የ ነፃ ፕሬስን እና ተቃዋሚዎችን በጠላትነት ከመመልከት ይልቅ የ ተለየ ሃሳብ ያላቸው ነገር  ግን ለ ሀገራችን አስፈላጊ ዜጎች መሆናቸውን ይዘው መምራትን ከጀመሩ  የ ዛሬውን ቀን ''በ አቃቢ ግንቦት ሃያውያን'' እና በ እውነተኛ የፍትህ እና የልማት ሰዎች መሃከል ደቡብን ባሳተፈ መልክ ትግል ተጀመረ ማለት የሚቻል ይመስለኛል። አቶ ኃይለማርያምን'' አቃቢ ግንቦት ሃያውያን'' ካስቸገሩዋቸው  ዶ/ር ነጋሶ  በ ሄዱበት መንገድ ወደ ኢህአዲግ ተቃዋሚነት መቀየራቸው ላይቀር ይችላል። በ ጭፍን  ኢህአዴግ ያለው ሁሉ ትክክል ነው የሚል  አስተሳሰባቸውን ግን አቶ ሃይለማርያም ዛሬ መሃላቸውን እንደፈፀሙ  የሚያወልቁት ይመስለኛል። ምክንያቱም በሕዝብ እይታ እንደገቡ እና ስልጣኑ እንደፀደቀ ኢህአዲግ ኮስሶ ህዝቡ ገዝፎ ይታያቸዋል።ለመወደድ ደግሞ ምን ማድረግ እንዳለባቸው ያውቃሉ።ይህ እንግዲህ ከ'' አቃቢ ግንቦት ሃያውያን'' በሁሉ ሁሉ ከዳኑ ነው።
''አቃቢ ግንቦት ሃያውያን'' ብዬ የምጠራቸው ታሪክ ተቦክቶ፣ኩፍ ያለው፣ የተጋገረውም ሆነ የተበላው በ ግንቦት ሃያ ነው ብለው ለሚያስቡ ከ እዛ ቀን በፊት የ ነበረችውን  ኢትዮጵያ ከ ዛሬ ሁነት ጋር ማዛመድ ላቃታቸው  ወገኖች ሁሉ ነው።


 

No comments:

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።