ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, August 21, 2012

የ ማስታወሻ ደብተሬ ስለ አቶ መለስ


አቶ መለስ ዜናዊ እንደ ኢሳት ቴሌቭዥን ከ አንድ ወር በፊት እንደ ኢቲቪ ደግሞ ትናንት ነሃሴ 14/2004 ዓም ከምሽቱ(5:40) አምስት ሰዓት ከ አርባ ላይ አርፈዋል።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት መግለጫ ¨በ አቶ መለስ ዜናዊ አለጊዜው መሞት የ ኢፍድሪ መንግስ እና የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ እጅጉ ያዝናል¨  መግለጫው በመቀጠል ¨ የሃገራችን ህዝቦች የ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቲርን መታመም ከሰሙ በኋላ በ እየእምነታቸው በጸሎት መልካም ምኞታቸውን ሲገልጹ እንደቆዩ የሚኒስትሮች ምክር ቤት እና የ ኢፍድሪ መንግስት  በከፍተኛ አድናቆት ተገንዝቧል።¨ ብሏል።

እግዚአብሄር ነፍስ ይማር። ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን እንመኛለን።

አቶ መለስ በ በጎም ሆነ በጎ ባልሆነ መልክ በ ሃገራችን ላይ ብቸኛ ተጽኖ ፈጣሪ(influential) ሰው የነበሩ ለመሆናቸው አሌ የማይባል ሃቅ ነው።

እኔ ከተናገሩዋቸው ንግግሮች ሶስት ንግግሮችን ሳያብራሩልን ማለፋቸው ወይንም በ መጽሃፋቸው ላይ ሳይገልጹልን ማለፍ አልነበረባቸውም   እላለሁ።
እነኚህ ንግግሮች አንድ ቀን ከ ስልጣን ዘመናቸው በኋላ ያስረዳሉ ብየም እጠብቅ ነበር።ምናልባት ያልታተመ መጽሃፍ ካለ አንድ ቀን ታትሞ ለማንበብ ለታሪክ ተመራማሪዎችም የመረጃ ምንጭ ይሆናል ብየ አስባለሁ።
በተለያየ ጊዜ ከተናገሩት:-

፩ ¨እንደ ግለሰብ፣ እንደ መለስ በ አንድ ጉዳይ ላይ የማስበው ሃሳብ አለ ወደ ፓርቲዪ ስመጣ እንደ ኢህአዲግ የማስበው ሃሳብ አለ።''(ለ አዲስ አመት በ አል ላይ ከተናገሩት)
የትኞቹ ይሆኑ የ ፓርቲው ሃሳቦች? የትኞቹስ ይሆኑ የ እሳቸው ሃሳቦች ግን ፓርቲው ያልተቀበላቸው?
፪ ¨ወጣት ሳለሁ ሁሉን ነገር በ አንድ ቀን ካልሆነ፣ ካልተሰራ ብዬ አስብ ነበር። አሁን በ ጉልምስና ዘመኔ ላይ ሆኘ ስመለከተው ግን የተለየ አስተያየት አለኝ። እግዚአብሄርን መፍራት፤ ቆጠብ ማለት ከወጣትነት በኋላ የሚመጣ ስሜት ነው።¨ (በ አፍሪካ ህብረት ከ አፍሪካ ለተሰበሰቡ ወጣቶች በ እንግሊዝኛ  ከተናገሩት)
፫ ¨ አንድ ነገር ስታፈርሱ እያከበራችሁ ማፍረስ አለባችሁ በ አንድ ቀን ሁሉ ካልተቀየረ ማለት የለባችሁም እያከበሩ ማፍረስ ተማሩ!''  (በሚልንየም አዳራሽ ለ ደጋፊዎቻቸው የ ፓርቲው አባላት የተናገሩት)::

ከላይ የተነገሩት ንግ ግሮች አቶ መለስን በ ሚድያ ከምናውቀው ስብዕናቸው በተለየ አንድ ያልተነገረን  ግን በ ተለያዩ ሰዎችም ይሁን ሌሎች ሃይሎች ጣልቃ የገቡበት ጉዳዮች አሉ እንዴ? እላለሁ።
ከ ሶስቱ ያልተብራሩ ንግግሮች በተጨማሪ በደንብ ያልተብራራው እራሱ አብዮታዊ ዲሞክራሲ ነው።
የ አቶ መለስ ፖለቲካዊ ፍልስፍና ''አብዮታዊ ዲሞክራሲ¨ እራሱ በደንብ የገባው ሰው ኢህአዲግ ውስጥ ያለ አይመስለኘም። ምክንያት ብዙዎቹ የ ፓርቲው ሰዎች የ እሳቸውን የ መድረክ ንግግር እየመዘዙ ከ ማስተጋባት ያለፈ የ ፖለቲካውን መሰረታዊ ፍልስፍና ስለማያስረዱ። አሁንም የ እሳቸው በበለጠ ሳያብራሩት ቢያንስ በደንብ የሚያብራራ ሰው ሳይተኩ ማረፋቸው እንደገና አሁንም ¨አብዮታዊ ዲሞክራሲ¨ላልገባን በ ሚልዮን ለምንቆጠር ¨ጭቁን ህዝቦች¨ የ ፖለቲካው ፍልስፍና በደንብ እንዲከለስ ለመጠየቅ ግድ ይለናል።
ለ አቶ መለስ እረፍተ ነፍስን፤ ለ ቤተሰቦቻቸው መጽናናትን ይስጥልን።
አበቃሁ።

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...