ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, May 4, 2012

አርበኞቻችንን እናስታውስ።


                                           ሚያዝያ 27 የ ድል አደባባይ

ሚያዝያ 27  የ ኢትዮዽያ አርበኞች የፋሺሽት ኢጣልያን ያሸነፉበት ቀን። የ ኢትዮዽያ ሰንደቅ ዓላማ ዳግም የተሰቀለበት ቀን ።

የ ኢትዮዽያ ገበሬ ሚስቱን፣ልጁን፣ንብረቱን ትቶ ፋኖ ተሰማራ ብሎ ያቆያት ሃገር:- ኢትዮዽያ!

ሚያዝያ 27/1935 ዓ ም ግርማዊ ቀዳማዊ አጼ ሃይለስላሴ የ ኢትዮዽያን ሰንደቅ ዓላማ በ ቤተ መንግስት ከሰቀሉ በሁዋላ ለ መላው ዓለም ካስተላለፉት መልዕክት

የመልክቱ ግርድፍ ትርጉም
''አዲስ አበባ ከሚገኘው  ቤተ መንግስቴ  የ አትክልት ስፍራ ተገኝታችሁ ይህን ፊልም መቅረጻችሁ መልካም ነው :: በመላው ዓለም  ይህን የሚመለከቱ ሁሉ በ ዕምነት እና በጀግንነት አማካኝነት በ ሃያኛው ክፍለ ዘመንም ዳዊት ጎልድያን እንደመታ ይገነዘባሉ ።'' ሚያዝያ 27/1935 ዓ. ም. ግርማዊ ቀዳማዊ አጼ  ሃይለስላሴ::

                                                                 
                             አርበኞቻችንን እናስታውስ


ቁርጥ ቀን ባይመጣ ሁሉም ጀግና ነበር

ቁርጥ ቀን ባይመጣ ሁሉም ጀግና ነበር፣
የ ውሎ ገድሉን ሲኖር የሚናገር።
እስኪመጣ ድረስ ቁርጥ ቀን በቶሎ፣
ፈሪም ያውቅበታል መኖር ተመሳስሎ።
ጌታቸው በቀለ
ሚያዝያ 27/2004 ዓ.ም
ኦስሎ

2 comments:

Anonymous said...

cheers all!!!! Enquan aderesachihu!!!

Anonymous said...

I am happy with full confidence approach of Haileselassie I. Africa has missed such courage full leader.God bless Ethiopia