ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, May 29, 2012

ግንዛቤ ቁ. 1= በ አፍሪካ ልጆችን ለ ጉዲፈቻነት ከሚልኩት አስር ቀዳሚ ሃገራት ውስጥ የኢትዮጵያ የ ቀዳሚነት ስፍራ



ዛሬ ግንቦት 21/2004ዓም  በ አዲስ አበባ የተባበሩት መንግስታት ስብሰባ አዳራሽ  በተደረገ አምስተኛው የ አፍሪካ ህጻናት ፖሊሲ (የ ጉዲፈቻ ህጻናት ላይ ባተኮረ) ስብሰባ ላይ በ አፍሪካ  ልጆችን ለ ጉዲፈቻነት ከሚልኩት አስር ቀዳሚ ሃገራት ውስጥ ኢትዮጵያ የ ቀዳሚነት ስፍራ መያዟን ሪፖርቱ አመልክቷል።  ወ/ሮ ዘነቡ ታደለ የሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ሚንስትር ሲናገሩ:-
'' ኢትዮዽያ የጉዲፈቻ ህጻናትን ወደ ውጭ የምትልከው ብዛት በ 2009ዓም    6,000 ነበር:: ዛሬ ግን 2,000 ደርሰናል''ብለዋል።
  •   በስብሰባው ላይ እንደተጠቆመው በ አመት ከ ሁለት ሺ በላይ ህጻናት ''ኤክስፖርት''   ይደረጋሉ ማለት ነው።
  •  ከሚላኩት ህጻናት ከ እያንዳንዱ የሚገኝ ገንዘብ አለ- ለ መንግስት። 
  • ወላጅ በከፋ ችግር ውስጥ ካልሆነ እንዴት ልጁን ወደ አልታወቀ ምድር ይልካል? 
  • ይህ የሃገራችንን  የ ችግሩን ''ዲግሪ'' አያሳይም? 
  •  ምን ያህል በ ስነ -ልቦና የተጎዱ ልጆች በ ባህር ማዶ እያደጉ እንዳሉ ልብ እንበል።
  •  አዎን 'በሃገር ቤት በችግር ከሚያድጉ ወደ ባህር ማዶ ቢሄዱ ይሻላል' የምንል እንኖራለን። ሆኖም ግን ኢትዮጵያ በንጉሱ ዘመን  ልጆችን መንግስት በሃላፊነት ወስዶ ያሳድግ ነበር። ደርግ እንኳን ባቅሙ 'የ ህጻናት አምባ' የሚባል ተቋም አቋቁሞ ያሳድግ ነበር።ከሌላው የ አፍሪካ ሃገራት የእኛ ለምን ይህን ያህል ከፋ ? የሃገርን ችግር በሃገር ልጅ መፍታት እንጂ ገንዘብ እየተቀበሉ መላክ ሞራላዊ ስራ ነው? 
ቀዳማዊ አጼ ኃይለ ስላሤ በ አዳሪ ትምርት ቤት መመገብያ አዳራሽ በድንገት ደርሰው ሲቆጣጠሩ::






 ምንጭ:- የ አሜሪካ ራድዮ የ አማርኛ ክፍል ግንቦት21/2004ዓም   ዜና

1 comment:

Anonymous said...

Ene Dr. Abdul Mejid ye Somali kilil prezdant yetemarut be Hayleselase neber be Adari timirt bet behuala degmo England likew astemaru. Weyane simeta gin Haileslasen mesadeb jemeru.